Get Mystery Box with random crypto!

Telkhis (هذه عقيدتنا)

የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا) T
የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا)
የሰርጥ አድራሻ: @telkhis
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.09K
የሰርጥ መግለጫ

((( @IbnusirajBot )))

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-23 08:15:33 ኢብኑ ሂዛም حفظه الله ፈትሁል ዐላም በተሰኘው የቡሉጝ ማብራሪያቸው ላይ

"ከእነዚህ አራት አቛሞች ሁሉ የተሻለውና ትክክለኛው አቋም ሴቶች ለራሳቸው ሶላቶች አዛንና ኢቃማ ማድረጋቸው #የሚወደድ ተግባር መሆኑ የተሻለ አሳማኝ ነው ይላሉ።

የብዙዎቻችን ችግር ያለው ደግሞ
ሴት አዛን ታድርግ ሲባል
1- ድምጿን ከፍ አድርጋ ጮሃ አዛን ታውጣ
2- ከመስጂድ አዛን ትበል
3- ለወንዶች አዛን ታድርግ እንደማለት አድርገን ማሰባችን ነው።
ይህ ሁሉ ስህተት ነው። ድምጿን አጅነብዮች በማይሰሙት መልኩ አዛን ማለቷ ይወደዳል ማለታቸው ነው።

ለ1,400 አመታት ያክል ያልተለመደና ያልተተገበረ ነው የሚሉ ካሉ የበዛ ስህተትን ተሳስተዋል። የሴት ልጅ አዛንና ኢቃማ ጉዳይ ከሶሀባዎች ጀምሮም ሲነሳ የነበረ ጉዳይ ነው።
ለእኛ አድስ ስለሆነ ብቻ ለምሁራኖቹ ሁሉ አድስ መስሎ አይታየን።

በርግጥ ኢብኑ ሂዛም ሴቷ የከተማውን አዛን ከሰማች አዛን ማውጣቷ አይወደድላትም የሚል እይታ አላቸው። ይህን ያሉበትን ምክንያት ግን አላስቀመጡም። ከተማው ላይ አዛን ስለሰማን ብቻ እኛ ከመስጂድ ውጭ ስንሰግድ አዛን ማለታችን አይወደድም ማለት በራሱ መረጃን የሚጠይቅ ጉዳይ ነው።

ታዋቂው ሶሃባ አነስ رضي الله عنه ከባልደረቦቹ ጋር መስጂድ ሲገባ ሶላት ተሰግዶ ተጠናቆ ስላገኘ አዛን አድርጉ ብሎ አዛን አስደርጎ እዚያው መስጂድ ውስጥ ሰግደዋል።

ባጭሩ ሴት ልጅ አዛን ማለት የለባትም ባዮቹ የሚያቀርቡት መረጃ የላቸውም። አይደለም ሀራም ነው ወይም ቢድዓ ነው ለማለትና የተጠላ ነው ለማለትም የሚያበቃ መከራከሪያ የለም።

ለበለጠ
ሰመሩል ሙስተጧብ ከተሰኘውን የሸይኽ አልባኒ رحمه الله ኪታብ ላይ ባቡል አዛንን አገላብጡ።

T.me/telkhis
865 views05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 20:22:34 ግልጽና ትክክለኛ ከልካይ መረጃ እስከሌለ ድረስ ማንኛውም ለወንዶች የተደነገገ አምልኮት ሁሉ ሴቶችንም ያካትታል።
ለወንዶች የተፈቀደ ነገር በሙሉ ሴቶችን እንደማያካትት የሚያስረዳ ግልጽ የሆነ የቁርአን መልእክት ወይም ትክክለኛና ግልጽ የሆነ ሀዲስ ከሌለ ለሴቶችም ይፈቀዳል።

T.me/telkhis
806 views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 13:43:03 አዛን ራሱን የቻለ ዚክር ነው። ትልቅ አጅርን የሚያስገኝ አምልኮት ነው። ታዲያ አዛንን እና ኢቃማን ለወንዶች ብቻ የተደነገገ ያደረገው ማን ነው?
ለማንኛውም አዛንም ኢቃማም እያደረጋችሁ ስገዱ። አዛን ግዴታ ድምጽን በጣም ከፍ አድርጎ መሆን አለበትም ማለት አይደለም።
በሴቶች ላይ አዛንም ይሁን ኢቃማ የማድረግ ግዴታ የለባቸውም በሚል የሚወራው ሀዲስም ትክክለኛ አይደለም ብለዋል ሊቃውንቶቻችን።

ዐኢሻ رضي الله عنها አዛን አድርጋ ትሰግድ ነበር።
ኢብኑ ዑመር رضي الله عنه ስለሴት ልጅ አዛን ተጠይቆ "እንዴት ከዚክር እከለክላቸዋለሁ" ብሏል።
አነስም رضي الله عنه ችግር የለውም የሚልን ምላሽ ሰጥቷል።
ከመዝሀብ መሪዎች አንጻር ደግሞ ኢማሙ ሻፍዒይና
ኢማሙ አህመድ አይቃወሙትም።
ከፊል የማሊኪያ ምሁራንም ኢቃማ ማድረጓ ጥሩ እንደሆነ ይናገራሉ።
ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን ብቻዋን ስትሰግድ ወይም ከሴቶች ጋር ስትሰግድ ነው።
ለወንዶች ሶላት አዛን ማድረግ አትችልም።

T.me/telkhis
1.0K viewsedited  10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 10:31:18 ምንም አይነት አሳማኝ መሰረት ከሌለው የከፊል ፉቀሃኦች እይታ ውስጥ
የሚስት ሃላፍትና እና ግዴታ ከአልጋ ጋር የሚያያዘው ጉዳይ ብቻና ብቻ ነው የሚለው ይገኝበታል። ይህ የቁርአንን እና የሀዲሶችን መረጃ የሚጻረር እንድሁም የቀደምት ሶሃባዎችን መንገድ ያልተከተለ አካሄድ ነው። ሚስት ቁጭ ብላ
ባለቤቷ ወጥ የመስራት፣ ፍራሽ የማንጠፍ፣ እንጀራ የመጋገር---- ግዴታ የለበትም።

ሸይኽ ሙሀመድ ዐሊ አደም #አልኢትዪቢይ

መተጋገዝ ግን መልካም ነው።
ነብዩ صلى الله عليه وسلم በቤት ውስጥ ባለቤቶቻቸውን በመንከባከብ ነበር የሚያሳልፉት። የተቀደደን ይሰፋሉ፣ጫማቸውን ይጠግናሉ፣ ጸጉራቸውን ያስተካክላሉ-----

T.me/telkhis
854 views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 13:40:48 #የዐስር_ሶላት_በዕዲያ

እናታችን ዐኢሻ رضي الله عنها እንደተናገረችው
"ነብዩ صلى الله عليه وسلم ከፈጂር በፊት ያሉትን ሁለት ረከዐዎችና ከዐስር በኋላ ያሉትን ሁለት ረከዐዎች አያሳልፉም ነበር።''

በሌላ ሀዲስ ላይም ስለነብዩ صلى الله عليه وسلم የሱንና ሶላት አሰጋገድ ሁኔታ ስትጠየቅ
ዙህርን ከሰገዱ በኋላ ሁለት ረከዐዎችን ይሰግዳሉ። ቀጥለውም ዐስርን ከሰገዱ በኋላ ሁለት ረከዐዎችን ይሰግዳሉ ብላ መልሳለች። በዚህ ሀዲስ መሰረት ከዐስር ሶላት በኋላ የሚሰግዷቸው ሁለት ረከዐዎች ቀዷእ እንዳልሆኑ መረዳት ይቻላል። ኡመርኮ رضي الله عنه ከዐስር ሶላት በኋላ ሱንናዎችን የሚሰግዱን ሰዎች ይመታቸው ነበር የሚል ተቃውሞ ሲቀርብባት ዑመር የከለከለው ሰዎች ከዐስር ጀምረው ጸሀይ እስከምትጠልቅ ድረስ እየሰገዱ ስላስቸገሩት ነው። በርግጥ ዑመር ይሄን ማድረጉ ትክክል ነው ብላለች ዐኢሻ رضي الله عنها

ይሄንን ሱንና በርካታ ሰለፎችም ይፈጽሙት እንደነበረ ኢብኑ አቢ ሸይባ በሙሰነፋቸው ላይ አስፍረዋል። ከነዚያም ውስጥ
ዐምር ቢን መይሙን
አቡ ቡርዳ
አስወድ ቢን የዚድ
አቡዋኢል
መስሩቅ
ሙሀመድ ቢን አል ሙንተሺር
ጧውስ

ከሰሀቦችም ውስጥ ዐኢሻ፣ ዐሊይ፣ አነስ ፣አቡ አዩብ እንድሁም ኢብኑ ዑመር ከዐስር ሶላት በኋላ ሁለት ረከዐ ሱንና መስገድ ሱንና እንደሆነ ይገልጻሉ። ከፊሎቹም ይሰግዳሉ።
ዐሊይ ባስተላለፈውና ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ላይም "ከዐስር ሰላት በኋላ ምንም አይነት ሶላትን አትስገዱ፣ ጸሀይዋ ከፍ እስካለች ድረስ ከሆነ እንጅ" ብለዋል።

ይህች ሱንና የነብዩ ብቻ መለያ ሱንና ነች የሚሉ ዘገባዎች ቢኖሩም ግን ለመረጃነት ብቁ አይደሉም። በተጨማሪም ብዙ ሰሀባዎች ይችን ሱንና በቋሚነት ያልፈጸሟትም ነብዩ صلى الله عليه وسلم አዘውትረው የሚሰግዷት ቤት ከመጡ በኋላ በመሆኑ ነው። እንዳውም ለምን የዐስርን በዕዲያ ሱንና መስጂድ እንደማይሰግዷት ሲጠየቁ ኡማዎቼ እንዳይከብዳቸው ከመስጋት ነው የሚል ይዘት ያለውን ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ እይታ የዘመናችን ምሁራኖች ያመጡት አዲስ እይታ ሳይሆን ጥንትም የነበረ ግን ደግሞ እኛ የተላመድናቸው መሻይኾች በግልጽ ያወጡት የፊቅህ እይታ ነው። እንጂማ ሀዲሶቹን አልባኒ ብቻም ሳይሆን ቀደም ያሉት የሀዲስ ሊቃውንቶች እንደ አል ኢራቂይ ኢብኑ ሀጀር ሶሂህ ብለዋቸዋል።

ከመዝሀብ መሪዎችም ውስጥ ኢማሙ አህመድ ይህችን ሱንና አይቃወሙም ነበር።

ስለዚህ ይሄን ሱንና መተግበር የተረሱ ሱንናዎችን ህያው ማድረግ ነው። ባይሆን ግን ይህ ሱንና የሚተገበረው ጸሀይዋ ቀለሟን ወደቢጫነት ከመቀየሯ በፊት ነው።

T.me/telkhis
993 views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 10:40:59 ሶላቱን የረሳ ወይም በእንቅልፍ ምክንያት የሶላት ጊዜው ያመለጠው ሰው የሶላቱ ማካካሻ እንዳስታወሰ #ወድያዉኑ_መስገዱ ነው ብለዋል ነብያችን عليه افضل الصلاة وأتم التسليم።

ሶላቱን የረሳ ሰው ማካካሻው ወዲያውኑ መስገድ ነው ሲባል
ሆን ብሎ ያሳለፈው ሰው ከተውበት ውጭ ምንም አይነት ማካካሻ የለውም የሚል መልእክት አለው ሀዲሱ ይላሉ ሸይኽ አልባኒ።
ቀዷእ የሚባል ነገር የለም ማለታቸው ነው።

T.me/telkhis
883 views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 00:48:39 ነብዩ صلى الله عليه وسلم የሆነን ጀናዛ በበቂዕ መቃብር ቀብረው ሲመለሱ
እናታችን ዐኢሻ رضي الله عنه
"ወይኔ ራሴን" እያለች ህመሟን ስትገልጽ ሰሟትና ኧረ የኔ ይብሳል በሚል ሁኔታ
"ኧረ ወይኔ ራሴ" ብለው መለሱላት። (ኢብኑ ሒባን የዘገቡትና ሸይኽ አልባኒ ሶሒህ ያሉት)

እናም ህመምን መግለጽ (ማንቋረር) ክልክል አይደለም/አይጠላምም። ተፈጥሯዊ ጉዳይም ነው። ሀራሙ መብሳጨትና የአላህን ዉሳኔ መቃወሙ ነው።

T.me/telkhis
1.0K views21:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 08:18:17 የጁሙዓ እለት ጥፍርን ማሳጠር እንድሁም የብብትን፣ የብልትንና የቀድሞ ቀመስን ጸጉር ማሳጠር ሱንና ስለመሆኑ የሚገልጽ አንድም ትክክለኛና ግልጽ የሆነ የነብዩ ሀዲስ صلى الله عليه وسلم የለም። እነዚህን ጉዳዮች የጁሙዓ ቀን መፈጸሙ ይወደዳል የሚል ይዘት ያላቸው ዘገባዎች በሙሉ ደካማ ወይም ደግሞ ቅጥፈት ናቸው ብለዋል ቀደምትና የዘመኑም የሀዲስ ሊቃውንቶች። ኧረ እንዳውም በሚታወቁት የሱነን፣ የሙስነድና የሙሰነፋት ኪታቦች ላይ ስለጉዳዩ ምንም የሰፈር ነገር የለም። ባይሆን ግን ከፊል አኢማዎች ይወደዳል ብለውታል። ኢብኑ ዑመርም ጁሙዓ ቀን ጥፍሩን ያሳጥር እንደነበረ ተወርቷል። እንደጥቅል ግን የጁሙዓ ቀን መተጣጠብ፣ አሪፍ ልብስ መልበስ፣ ሽቶ መቀባት፣ ሲዋክ መጠቀም እንጅ ጥፍር መቆረጥ፣ ቀድሞ ቀመስን ማሳጠር፣ የብብት ጽርጉርን መንጨት ሱንና ነው ብሎ መውሰድ ተገቢ አይደለም።

T.me/telkhis
1.1K views05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 15:03:41
https://t.me/telkhis/2352

https://t.me/telkhis/2352
850 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 13:36:18 ይህ የሸይኽ አልባኒን የፊቅህ ምርጫዎች የሚገልጸው አልሙለኸሱል ፊቅሂይ ሚን ዑልሙል ኢማሚል አልባኒይ የተሰኘው ኪታብ የመጀመሪያው ምእራፍ (ኪታቡጦ'ሀራህ) ትርጉም ነው።

እጂግ በጣም ወሳኝ ወሳኝ ነጥቦችን የሚዳስስ ኪታብ ነውና አውርዱና አንብቡት። ለሌሎችም በስፋት አሰራጩልኝ።
የአተረጓጎም ስህተት ካለው በመጽሀፏ መጨረሻ ላይ ባሰፈርኩት ሊንክ በመጠቀም አሳውቁኝ።

ጀዛኩሙሏሁ ኸይረን።

T.me/telkhis
1.1K viewsedited  10:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ