Get Mystery Box with random crypto!

Telkhis (هذه عقيدتنا)

የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا) T
የቴሌግራም ቻናል አርማ telkhis — Telkhis (هذه عقيدتنا)
የሰርጥ አድራሻ: @telkhis
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.09K
የሰርጥ መግለጫ

((( @IbnusirajBot )))

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-17 08:34:24 ጌታዬዋ ሶላትን በአግባቡ ሰጋጅ አድርገኝ። ዝርያዎቼንም እኔን በመልካም የሚከተሉ፣ በአግባቡ ሰጋጆችም አድርጋቸው።
ጌታዬ ሆይ ዱዓዬን ስማኝ፣አምልኮቶቼንም ሁሉ ተቀበለኝ።

{رَبِّ ٱجْعَلْنِى مُقِيمَ ٱلصَّلَوٰةِ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۚ رَبَّنَا وَتَقَبَّلْ دُعَآءِ----} إبراهيم 40

T.me/telkhis
828 views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 07:24:46 የሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን የቡሉጝ ማብራሪያቸው
فتح ذي الجلال والإكرام في شرح بلوغ المرام
ተደጋጋሚ ምሳሌዎች እንድሁም ከዋናው የኪታቡ ርእስ ወጣ ያሉ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት ጥልቅ ኪታብ ነው። የቡሉጝን የፊቅህ ጉዳዮች ብቻ አይዳስስም። እዚህም እዚያም ይነካካል። የሀሳብ ድግግሞሽም አለበት። አሁን ላይ ግን ይህን ችግሩን መሉ በሙሉ በቀረፈ መልኩ ሸይኽ ዐብዱለጢፍ አነጅዲይ የሸይኹን ሰፊ ማብራሪያ በጣም አሳጥረውና ከሀዲሱ ጋር የሚተሳሰሩ የፊቅህ ጉዳዮችን ብቻ አበጥረው አዘጋጅተውታል። ስሙንም
الدر الثمين باختصار شرح بلوغ المرام لإبن عثيمن
ብለውታል።

ኪታቡ ለንባብ በሚያመች አጻጻፍ በ2,800 ገጽ የተዋቀረ ነው። ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም አውርዳችሁ ማንበብ ትችላላችሁ።

https://t.me/ktbktb/223489

ወይም

http://www.moswarat.com/books_view_3730.html
403 views04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 17:29:11 ነብዩ صلى الله عليه وسلم ሚስታቸውን ሳም አድርገው ወደ ሶላት ያቀኑ ነበር። ዉዱእ ሳያደርጉ ያሰግዳሉም።

T.me/telkhis
295 views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 13:05:36 በነገራችሁ ላይ
የሰይጣን አንቀጾች የሚል ርእስ በመስጠት ቁርአንን የሚያጣጥል መጽሀፍን ያሳተመው የህንድ ተወላጁ፣ በዜግነት እንግሊዛዊዉ እና አሜሪካ ውስጥ የፖሊስ ጥበቃ የሚደረግለት ሰልማን ሩሽዲ ትናንት በሆነ መድረክ ላይ ንግግር እያደረገ ሳለ በ23 አመት ወጣት ሙስሊም ጥቃት ተፈጽሞበታል። አንገቱን፣ ሆዱን፣ እጁን እንድሁም ዐይኑን በጩቤ ተቦጫጭቀዋል። አሁን ላይ መናገር አይችልም። በህይወት ቢተርፍ ራሱ አንድ አይኑን እንደሚያጣ የህክምና ቡድኑ አሳውቋል። ሳንባውም ክፉኛ ተጎድቷል---

አላህ ይግደለው።

ሰልማን ሩሽዲ
የሰይጣን አንቀጾች የሚለውን መጽሀፍ በማሳተሙ ምክንያት በበርካታ ሙስሊም በዝ ሀገራት መግባት እንዳይችል እገዳ ተጥሎበታል።

እጅግ በጣም አናሳ ሙስሊም ዜጎች ያሏት #ደቡብ_አፍሪካም በግለሰቡ ላይ እገዳ ከጣሉ ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።

#ደቡባችን
559 views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 14:31:16 የዛሬው ኻጢባችንና ሶላቱ
651 viewsedited  11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 11:15:45 የተቀያየመ፣ ቅር የተባባለ፣ የሚፈላለግን ግን ደግሞ ያልተገናኘን ካወቃችሁ አሸማግሉ፣ አስታርቁ፣ አግባቡ። ነብዩ صلى الله عليه وسلم አስታራቂም ነበሩና ይህን ሱናቸውን ህያው አድርጉ። በሀዲሳቸውም "አሸማግሉ አጅርን ታገኛላችሁና" ብለዋል። ተሸማጋዮቹ እሺ አይሉንም ብላችሁ ተስፋ እንዳትቆርጡ ደግሞ "አላህም በነብዩ አንደበት ያሻውን ይፈርዳል" የሚልን ወሳኝ መልእክት ጨምረውበታል። እናንተ የምትችሉትን ያክል ታገሉ እንጅ የሽምግልናው ዉጤት አያሳስባችሁ ማለታቸው ነውኮ።

በሙእሚኖች መካከል ክፍተቶችን እየተመለከታችሁ ከርቀት ታዛቢ አትሁኑ። የሚተፋፈሩ ግን ደግሞ የሚፈላለጉን ካወቃችሁም ልክ እንደ አቡ ራፊዕ رضي الله عنه ሁኑ። አግባቢና መንገድ አመቻቺ።

T.me/telkhis
652 views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 05:38:27 "በሩ ተዘግቶብህ ብታገኘው ራሱ ዉጪ ላይ ቆመህ ተጠባበቅ። ከበሩ ፊትለፊት ቆመህ ጠይቅ፣ ለምን፣ ተማጸን። ባይሆን ፊትህን ወደበሩ አቅጣጫ አዙረህ ይሁን። እንደሚከፈትልህም ተስፈኛ ሁን። በሩ ከተዘጋብኝ ከዚህ ቦታ ምን አደርጋለሁ ብለህ ጀርባህን ሰጥተህ አትመለስ።"
"ኢብኑል ቀይም"
-----------------------------------------
ጌታችን ሆይ አሁንም ከዚያው ከደጃፍህ ላይ ቆመናል። ተማጽነንህ ስላደረግክልን ሁሉ እናመሰግንሃለን። እውን ስላልሆነው ዱዓችንም ጭምር ከልብ እናመሰግንሃለን።

اللهم لك الحمد حتى ترضى ،ولك الحمد إذا رضيت ،ولك الحمد بعد الرضا ،ولك الحمد على كل حال.

T.me/telkhis
673 viewsedited  02:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 17:25:26 ሙጚስ እና በሪራ رضي الله عنهما ሁለቱም ባሪያዎች ነበሩ። በትዳር ተጣምረው በፍቅር ተሳስረውም ይኖሩ ነበር። ኋላ ላይ ግን በሪራ ከባርነት ቀንበር ቀደም ብላ ነጻ ወጣች። እንደሚታወቀው ሁለት በባርነት ላይ ሳሉ የተጋቡ ባለትዳሮች አንዳቸው ቀድመው ከባርነት ነጻ ከወጡ ትዳራቸውን የማፍረስ መብት ተሰጥቷቸዋል። እናም በሪራ ቀድማ ነጻ ስትወጣ ሙጚስን አልፈልግህም አለቺው። ሙጚስ ደግሞ ልቡ ውልቅ እስከሚል ነበር በሪራን የሚያፈቅራት። ያለ የሌለን ሽማግሌ እየላከ አስለመናት። በሪራ ግን አሻፈረኝ አለች። ሽምግልናው ነብዩ صلى الله عليه وسلم ዘንድ ደረሰ። ነብዩም ለሙጚስ ሽማግሌ ሆነው ከበሪራ ዘንድ ሄዱ። አብራችሁ ኑሩ ብለው መከሯት። ያረሱለሏህ ትእዛዘዎ ነው? ብላ ጠየቀች። አይ ትእዛዝንኳ አይደለም። ሽምግልና ነው ብለው መለሱ። እንግዳውስ ሽምግልና ከሆነ ሙጚስን አልፈልገውም ብላ የነብዩንም ሽምግልና አሻፈረኝ አለች። ነብዩም صلى الله عليه وسلم ሽምግልናቸውን ስለመለሰች አልወቀሷትም። አልተቀየሙባትም።

ስለዚህ
1- ለምን እንደተወችው ሳታውቁ እንደዚያ የሚያፈቅትን ባሏን እርግፍ አድርጋ ተወችው፣ የእሷማ ግፍ የተለዬ ነው አትበሉ። ነብዩ በሪራን እንድህ እንስፍስፍስ ብሎ የሚያፈቅርሽን ባልሽን እንዴት ትተይዋለሽ ብለው መች ወቀሷት። ለምን እንደፈታት በትክክል ሳትረዱ (ብትረዱም ጭምር) እሷ አፈቅረዋለሁ ስላለች ብቻ እሱን አትውቀሱ።

2- ሽምግልና ሞክራችሁ ካልተሳካ ንቀውኝ ነው አይደል አትበሉ። የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሽምግልና መች ተሳካ። አንተ ከነብዩ በላይ የምትከበር ሰው ነህ እንዴ?

3- ለመለያየት መበዳደልን መናገር ግዴታ አድርጋችሁ አትውሰዱ። በሪራ ምን በደል ደርሶብኛል ብላ ተፈታች?

4- ሽምግልና ታላቅ ዒባዳ መሆኑን አትዘንጉ፣ አጅሩም ከሽምግልናው ዉጤት ጋር የተሳሰረ አይምሰላችሁ። ዉጤቱ ምንም ይሁን ምን ሞክሩ። አጅሩ አይቀርባችሁም።

5- ሸሪዐዊ ትእዛዝት በሙሉ የሚገድባቸው መረጃ እስካልተገኘ ድረስ መሰረታዊዉ መነሻ መርሃቸው ግዴታነት እንደሆነም እወቁ። በሪራ رضي الله عنها "ያረሱሉሏህ ትእዛዘዎ ነውን"?? ብላ ስትጠይቅ አዎ ትእዛዝ ነው ቢሏት ኖሮ ያለምንም ማንገራገር ቀጥ ብላ ከሙጚስ ጋር ልትኖር ነበርኮ።

(شرح خلاصة قواعد الأصولية)

እናንተም ጨማምሩበት።

T.me/telkhis
689 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 07:31:57 በሀዲስ እንደተነገረን "በሶላት ውስጥ ስንሆን ሸይጧን የብልታችንን ጫፍ ይነካና የሆነ እርጥበት ያጋጠመን ወይም ዉዱእ ያፈረስን ያክል እንድሰማን ያደርጋል። በዚህም ሶላታችንን ተረጋግተን እንዳንሰግድ ቀልባችንን ይሰርቀናል። ይህ ችግር እንዳያጋጥመን ኢስቲንጃእ እንዳደረግን ወይም ዉዱእ እንዳጠናቀቅን ከውስጥ ልብስ ውስጥ (ፓንት፣ቁምጣ) ዉሃ ረጨት ረጨት ማድረግ እጂግ በጣም አዋጩ መንገድ ነው። ነብዩ صلى الله عليه وسلم ያደርጉት ነበር። እንድናደርገውም መክረውናል። በተለይም በሶላት ውስጥ ዉዱኤ ፈረሰ አልፈረሰም በሚል ከራሳቸው ጋር የሚከራከሩ ሰዎች ከዚህ የተሻለ መፍትሄ አያገኙምና ሶላታቸውን በጥንቃቄ ይሰግዱ ዘንድ ይሄን ነብያዊ ምክር ሊተገብሩ ግድ ይላቸዋል።

T.me/telkhis
705 views04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 20:59:48 ቢሳካ ደስ የሚለን ብዙ እቅድ አለን። ያ ህልማችን፣ተስፋችን እውን እንድሆንም የሚቻለንን እንጥራለን። ባይሳካ ደግሞ አንበሳጭም። ምክንያቱም ጥበበኛው እንድሁ ለከንቱ አይደለምና የሚከለክለን። በጌታችን ላይ ያለን ተስፋ "የከለከለን የተሻለን ሊሰጠን ነው" የሚል እንጂ "እየቀጣን ነው" የሚል አይደለም።
وإني لأدعو الله حتى كأنني
أرى بجميل الظن ما الله صانع

T.me/telkhis
716 views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ