Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 77

2022-08-20 20:43:13 ስለ እጮኝነት ስለ ትዳር የተማማርነውን እነሆ በፒዲኤፍ
3.8K views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 15:57:43
#እረኛዬ #ኢየሱስ #ክርስቶስ እስኪ አስቡት ጥልን ለመቋጨት አንተ ሙተህ ለሌላው አንድነትን ፍቅርን መስጠት አያስገርምም ነው የምትሉ? አንድ ባለቅኔ የተቀኙት አንድ ቅኔ ትዝ አለኝ። ቅኔው ሚበዝኁ ይባላል። እና ምን ይላሉ መሰላችሁ "በይነ ጣዕዋሃ ሐንካስ ትትበላእ ላሕም አምስጦ ዘይትከሃላ" ብለው ይጀምራሉ። ትርጉሙ "ስለ አንካሳ ጥጃዋ ብላ ማምለጥ የምትችለው ላም (በአውሬ) ትበላለች" እንደማለት ነው። ላሚቱ አንካሳ ጥጃዋን ስለምትወድ ጥጃዋን ለማዳን እርሷ ትበላለች። እረኛዬ ይህንን ነው ያስተማረን ስለ ሕዝብ አንድነት እና ፍቅር ራስን እስከ ሞት ማድረስ ድንቅ ነው። በአሁኑ ዘመን ሌላውን መሥዋእት አድርጎ ራሱን ማዳን የሚፈልግ ትውልድ ነው ያለ። እረኛዬ ግን ራስን ለሌሎች መዳን ሲሉ አሳልፎ መስጠትን በተግባር አስተምሮናል።

እረኛዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በእርሱ ደም መፍሰስ ከፈጣሪው ተጣልቶ የነበረው አዳም ታረቀ። የፍቅር ትርጉሙ ራስን ለሌላው ሲሉ አሳልፎ መስጠት ነው። ዮሐ. ፲፣፲፬ "መልካም እረኛ እኔ ነኝ" ብሏል። የእረኛቸውን ሞት እያሰቡ ሰማእታት ራሳቸውን ለስለት አሳልፈው ሰጡ መነኮሳት ግርማ ሌሊቱን ድምጸ አራዊቱን ታግሠው ይኖራሉ። ምእመናን ጥረው ግረው ካገኙት እየመጸውቱ ይኖራሉ።ይልቁንም ዮሐንስ ወንጌላዊ እረኛው ተሰቅሎ ካየው በኋላ እስከ ዕለተ ሞቱ ፊቱ በኀዘን ተውጦ (ቊጹረ ገጽ ሆኖ) ይኖር ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ጥቅም ያለው እንባ እና ልቅሶ ሞተ ወልደ እግዚአብሔርን ግፍዐ ሰማእታትን አስቦ ማልቀስ ነው ብሏል። እንዲሁም ኃጢኣትን እያሰቡ ማልቀስ ጥቅም ያለው ልቅሶ ነው ብሏል።

ባለቅኔው ቀጥሎ ለይእቲ ላሕም መድኃኔዓለም ተመሰላ ብሏል። ይህችን ላምም መድኃኔዓለም መስሏታል ይላል መድኃኔዓለም አዳምን ለማዳን በመስቀል ተሰቅሏልና።
3.5K viewsedited  12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 11:20:28 -----------------ክፍል ፭----------------
#ሃይማኖተ #አበው #ዘዲዮናስዮስ
ምዕራፍ ፲:-የዲዮናስዮስ ታሪኩ እንዲህ ነው። በግሪክ አቴንስ የፍልስፍና መምህር ነበረ። የፍልስፍናውን ትምህርት እያስተማረ ሳለ በዕለተ ዓርብ ጌታ ሲሰቀል ፀሐይ ስትጨልም ጨረቃ ደም ስትሆን ከዋክብት ሲረግፉ ምድር ስትነዋወጥ አየ። ይህ ሁሉ የተደረገ በዓለም ሁሉ ነበርና። ወነሥአ አርስጣላበ ዘውእቱ መዳልወ አልባብ። እንደፀሐይ ዓለሙን
ሁሉ በሚያሳይ መነጽር ሲመለከት ጌታ በቀራንዮ በመስቀል ተሰቅሎ በመስቀሉ ራስ እልመክኑን ወረደ ኀበ እሊኣሁ ወእሊኣሁ ሰቀልዎ የሚል ጽሑፍ ተጽፎ ያያል። በዚህ ጊዜ ዲዮናስዮስ ከዙፋኑ ወርዶ አለቀሰ። ፍልስፍና የሚያስተምራቸው ደቀመዛሙርቱም አባታችን ነገሩ ምንድን ነው ንገረን አሉት። ኅቡዕ አምላክ ሰው ሆነ ወገኖቹ አናምንም ብለው ሰቀሉት ይህ ተአምራት የተደረገ በዚህ ምክንያት ነው አላቸው። ወዲያው በብረት ሰሌዳ ዘመኑን፣ ወሩን፣ ዕለቱን ሰዓቱን ቀርጸው አኖሩት። ይህ በሆነ በ14ኛው ዓመት ጳውሎስ ወደ አቴንስ ሄዶ ስለጌታ አስተማረ። ስለ ስቅለቱም አስተማረ። ይህን ጊዜ ዲዮናስዮስ የጻፈው ዕለት ጳውሎስ ከነገረው ጋር አንድ ሆኖ አገኘው። አምኖ ተጠመቀ። ቅዱስ ጳውሎስም የአርዮስ ፋጎስ ኤጲስ ቆጶስ አድርጎ ሾመው። አርዮስ ፋጎስ አቴና ውስጥ ያለች ቦታ ናት። አርዮስ ፋጎስ ማለት የፍርድ ቦታ፣ የሊቃውንት መሰብሰቢያ፣ የጥበብ ቦታ ማለት ነው።


+√ ወደፈጣሪ እንጸልይ። ይህን ጊዜ ከአምላካውያት መጻሕፍት ምሥጢር ይገለጥልናል።

+√ ፍጥረታትን ሁሉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጡ የፈጠሩ ሥላሴ ናቸው። ፍጥረትን ሁሉ የሚያኖሩና የሚመግቡ የሚያስተዳድሩ ሥላሴ ናቸው።

+√ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ የሚያመሰግኑ ምእመናን አማልክት ዘበጸጋ ይባላሉ።

+√ ሥላሴ በገጽ፣ በመልክ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ በመለኮት አንድ ናቸው። እኒህም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ።

+√ የወልድ ከአብ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ ከአብ መሥረጽ ይደነቃል እንጂ አይነገርም። (ከሰው አእምሮ በላይ ነው ለማለት ነው። አብ የወልድ ቃልነት የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት ሳይለየው ወልድን መንፈስ ቅዱስን አስገኘ ማለት ለሕሊና ረቂቅ ነውና)።

+√ በአባቱ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ወልድ ሰው ሆነ (ሥጋን ተዋሐደ) ከድንግል ማርያምም በድንቅ ምሥጢር ተወለደ። ይህ ሲሆን ከመለኮቱ አልጎደለም።


----ሃይማኖተ አበው ዘአግናጥዮስ---
#ምዕራፍ #፲፩
አግናጥዮስ ለባሴ እግዚአብሔር እየተባለም ይጠራል። ሦስተኛው የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ ነው። የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ተማሪ ነው። ጌታ ትሕትናን ለሐዋርያት ያስተማረበት ብላቴና ነው።

+√ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ በድንግል ማኅፀን ተጸነሰ።

+√ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ፣ ወልድም በአብ በመንፈስቅዱስ፣ መንፈስ ቅዱስም በአብ በወልድ እንዳለ እናምናለን። አብ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አይሆንም። ወልድም መንፈስ ቅዱስን አብን አይሆንም። መንፈስቅዱስም አብን ወልድን አይሆንም።

+√ ለሥላሴ አንዲት አገዛዝ፣ አንዲት ፈቃድ፣ አንዲት ኃይል፣ አንዲት መንግሥት፣ አንዲት ምክር፣ አለቻቸው። በአንድ ምስጋና ይመሰገናሉ።

+√ መለኮት ሦስትነት ከእርሱ የሚገኝ አንድ ብርሃን ነው። አንድም ከሦስትነት የሚገኝ አንድ ብርሃን ነው። በዓለሙ ሁሉ ምሉእ ነው።

+√ ክርስቶስ ሰው እንደመሆኑ በሥጋ እንደታመመ በመለኮቱ እንዳልታመመ እናምናለን።

+√ ሰው ከነፍስና ከሥጋ የተገኘ አንድ እንደሆነ ሁሉ ኢየሱስም ከቃል እና ከሥጋ የተገኘ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው።

+√ መለኮት ሞት የምትል ከሆነ ሥሉስ ቅዱስ ሞቱ ያሰኛልና አይባልም። (መለኮት በሥጋ ሞተ ግን ይባላል)።

+√ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍስ የለውም በነፍሱ ምትክ መለኮት ነው የሚሉ ከኃድያን ክርስቶስ በወንጌል ነፍሴ ተከዘች ባለው ቃል ይረታሉ።

#ምዕራፍ #፲፪
+√ ኢየሱስ ክርስቶስ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ በእውነት በላ በእውነት ተሰቀለ በእውነት ታመመ። ምትሐት ግን አይታመምም።

+√ ከተዋሕዶ በኋላ አንዱን ክርስቶስ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉ ከሰቀሉት አይሁድ ጋር ይቆጠራሉ።

ክፍል ፮ ይቀጥላል።
4.1K viewsedited  08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 11:15:00
4.2K views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 11:14:32 #የፍቅር #ትርጓሜ
ፍቅር የአንዱን ድካም አንዱ ሲሸከም ነው። ሰማዕትነት የሌለበት ፍቅር ፍቅር አይባልም። በአፍ ብቻ እወድሃለሁ እወድሻለሁ ማለት ውሸት ነው። ይህንንስ ባላገሩ "የአፍ ዘመድ ከገበያም አይገድ" ብሎ ተርቶበታል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. ፲፭፣፲፫ "ነፍሱን ስለወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም" ብሎ የፍቅርን ትርጓሜ አስተማረን። ፍቅር በአፍ የሚናገሩት ብቻ አይደለም በሕይወት የሚኖሩትም ነው እንጂ። ለዚያም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በቃል ከተናገረ በኋላ በተግባር ደግሞ አዳምን ለማዳን በመስቀል የተሰቀለ። መስቀል ፍቅር በተግባር የተገለጠበት አደባባይ ነው። ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት ብሎ ሊቁ የገለጠው ይህንን ነው። ፍቅር ራሱ እግዚአብሔር ነው። ፩ኛ ዮሐ.፬፣፰-፳ "ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም እግዚአብሔር ፍቅር ነውና----ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው" ይላል። ይህ የሚነግረን በፍቅር ጥላቻ እንደሌለ ነው። ፍቅር ሌላውን እንደ ራስ መውደድ ነው። ማቴ. ፯፣፲፪ "ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው" ተብሎ እንደተጻፈ ሰውን መውደድ በእኛ ሊደረግብን የማንፈልገውን በሌላውም እንዲደረግ አለመፈለግ ሲሆን እግዚአብሔርን መውደድ ደግሞ ትእዛዙን በመፈጸም ይገለጣል።ዮሐ. ፲፬፣፳፩ "ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው" እንዲል።
√√√
√√√
ማቴ. ፯፣፳፩-፳፫ "በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። በዚያ ቀን ብዙዎች ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን ይሉኛል። የዚያን ጊዜም ከቶ አላወቅኋችሁም እናንተ አመፀኞች ከእኔ ራቁ ብየ እመሰክርባቸዋለሁ" እንዲል የጌታን ስም ብዙ ጊዜ ብትጠራ፣ በስሙ ተአምራትን ብታደርግ፣ በስሙ ትንቢትን ብትናገር፣ በስሙ አጋንንትን ብታወጣ ይህ የፍቅር ምልክት ተደርጎ አይያዝም። እግዚአብሔርን የመውደድ ዋናው ምልክቱ ፈቃዱን መፈጸም ነው። ፈቃዱ ምንድን ነው ከተባለ ዘጸ. ፳፣፩ ጀምሮ ያሉ አስሩን ሕግጋት መፈጸም ነው። ማቴ. ፲፱፣፲፯ "ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ" እንዳለ። ዮሐ. ፲፪፣፶ "ትእዛዙም የዘለዓለም ሕይወት እንደሆነች አውቃለሁ"እንዲል።
√√√
√√√
ቅዱስ ጳውሎስ ፍቅርን ጠቅለል አድርጎ ሲያቀርበው እንዲህ ብሎታል። ፩ኛ ቆሮ. ፲፫፣፪-፰ " ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድኾችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ፍቅር ይታገሣል፣ ቸርነትንም ያደርጋል፣ ፍቅር አይቀናም፣ ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፣ የማይገባውን አያደርግም፣ የራሱንም አይፈልግም፣ አይበሳጭም፣ በደልን አይቆጥርም፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለዓመፃ ደስ አይለውም። ሁሉን ይታገሣል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ በሁሉ ይጸናል። ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም" ብሎ ገልጾታል።
4.4K viewsedited  08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 07:38:56 _ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል ፫_
ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ማለት ነው። ራሱ መድኃኒት ነው። እንጂ ለማዳን አብን የሚለምን አይደለም። በሥልጣን አብና ወልድ አንድ ናቸውና። ዮሐ. ፲፣፴ "እኔ እና አብ አንድ ነን" ይላልና። ስለዚህ ኢየሱስ ራሱ መድኃኒት ነው እንጂ ለማዳን ከአብ የሚለምን በሥልጣን የአብ ተወራጅ የሆነ አይደለም። ታድያ እንዲያ ከሆነ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. ፲፬፣፳፰ "ከእኔ አብ ይበልጣል" ለምን አለ ከተባለ የሚራብ የሚጠማ ሥጋን በመዋሐዱ እንዲያ አለ። በዚህ ምክንያት ዕብ. ፪፣፯ "ከመላእክት ጥቂት አሳነስከውም" ተብሏል። መላእክት የሚራብ የሚጠማ ሥጋ የላቸውምና በዚህ ምክንያት። በክብር ከመላእክት እንደሚበልጥ ዕብ. ፩፣፬-፮ "ከመላእክት ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ስምን በወረሰ መጠን እንዲሁ ከእነርሱ አብዝቶ ይበልጣል---የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉም ለእርሱ ይስገዱ" ተብሏል።
+
+
ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነ አምላክ አምላክ የሆነ ሰው ነው ብለናል። ስለዚህ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውነትንም የአምላክነትንም ሥራ ይሰራል። ቅድመ ዓለም ነበረ ዓለምን ፈጠረ የምንለውም በኋላ ከድንግል ማርያም ተወለደ የምንለውም ያው አንዱን ነው። ቅዱሳት መጻሕፍት ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው እንደሆነ እንደሚነግሩን ሁሉ አምላክ እንደሆነም ይነግሩናል። ሃይማኖተ አበው ዘሄሬኔዎስ ምዕራፍ ፯ ቁጥር ፲፱ "በከመ ይነግራነ መጻሕፍት ቅዱሳት ከመ ክርስቶስ ሰብእ ከማሁ እሙንቱ ይነግራነ ከመ ውእቱ አምላክ" እንዲል። ኢየሱስ ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ተብሏል ማቴ. ፩፣፩። የዳዊት ጌታም ተብሏል። አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ የአምላክነትንም የሰውነትንም ሥራ ይሰራል። ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ለእኛ አርዓያ ለመሆን የሰራው ሥራ አለ፣ አምላክነቱን ለማሳወቅ የሰራው ሥራ አለ፣ ሰውነቱን ለማስረዳት የሰራው ሥራ የተናገረው ነገር አለ፣ ለቤዛነት የሰራው ሥራ አለ።ለእኛ አርዓያነት የሰራቸው ሥራዎች መጾሙ፣ መጸለዩ፣ መጠመቁ እና የመሳሰሉ ሥራዎች ናቸው። ማቴ. ፲፩፣፳፱ "ከእኔም ተማሩ" ብሎናልና። እሱ በመጾሙ በመጸለዩ በመጠመቁ የተጨመረለት ክብር የለም እርሱ በባሕርይው ክቡር ነውና። የአምላክነት ሥራ ሲሰራ ያዩት አምላክ ብቻ ነው ሰውነት የለውም ሰው አይደለም የሚሉ ነበሩና ሰውነቱን ለማስረዳት ራሱን ሲጠራ ብዙ ጊዜ የሰው ልጅ እያለ ይጠራ ነበር። ማቴ. ፲፩፣፲፱ "የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጣ" ተብሏል። መራቡ፣ መጠማቱ፣ መድከሙ፣ መሰቀሉ ሁሉ ሰው ስለሆነ የሆነው ነው። ከኃጢአት በስተቀር የሰውን
ሥራ ሁሉ ሰርቷል። ይህን አይተው ሰው ብቻ (ዕሩቅ ብእሲ) ለመሰላቸው ደግሞ አብርሃም ከመወለዱ በፊት አለሁ ብሎ በመናገር የአምላክነትን ሥራ ማለትም በደረቅ ግንባር ዓይን መፍጠር እና የመሳሰሉ ሥራዎችን ሰርቷል። ማቴ. ፲፪፣፰ "የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና" ተብሏል። ሌላው ለቤዛነት (ለካሣ) ነው። የአዳምን በደል ይቅር ለማለት አዳም ሊያደርገው የሚገባውን ሁሉ አድርጓል። አምላክ ሆኖ ሳለ "አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ" ብሏል። ተሰቅሏል። ተቀብሯል። በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል። መሥዋእት ወልድ በመስቀል ተሰቅሎ ራሱ ሊቀ ካህናት መሥዋእት አቅራቢ ሆኖ አዳምን ከአብ፣ ከራሱ፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አስታርቆታል (ታርቆታል)። አዳምም ድኅነትን ስላገኘ ወደ ገነት ገብቷል።
+
+
ሥጋ ደካማ ነው። በቦታ የተወሰነ ነው። በጊዜ ተዋሕዶ ቃልን በመዋሐዱ የቃልን ርስት ወረሰ ማለትም የቃልን ገንዘቦች ረቂቅነትን፣ በሁሉ ቦታ መኖርን ገንዘብ አደረገ በዚህም ምክንያት ስለ ሥጋ እንግድነት ዮሐ. ፭፣፳፯ "የሰው ልጅም ስለሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው" ተባለ። ማቴ. ፳፰፣፲፰ "ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ" ብሏል። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በሥልጣን አንድ ናቸው። አንዱን ብቻ ቢጠራ አድሎ መናገሩ ነው። ለምሳሌ ትንሣኤውን በተመለከተ ራሱ ወልድ በራሴ ሥልጣን ተነሳሁ ይላል። በሌላ ቦታ አብ አስነሳው ይላል። ሁለቱም አንድ ነው። በአንዲት ግብረ ባሕርይ ሦስቱም ይጠሩባታልና ነው።
+
+
ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስንናገር ራሱ ስለራሱ የነገርንን እና እርሱ ያስተማራቸው ሐዋርያት ስለእርሱ የተናገሩትን መሰረት አድርገን ነው። ክርስቶስ ያልሆነውን ኩነት ነው ማለት እና የሌለውን ማንነት መስጠት ግን ሰይጣናዊ ሥራ ነው። ወተት ነጭ ሆኖ ሳለ የሌለውን ማንነት በልብ ወለድ ወይም በውሸት ጥቁር ነው ማለት የሰይጣን የግብር ልጆቹ ሥራ ነው። ቅዱሳት መጻሕፍትን በመሰለኝ እየተረጎሙ ከተጻፉበት ዓውድ አያወጡ እየተረጎሙ ብዙውን ዓለም እያታለሉ ያሉ የሰይጣን የግብር ልጆች አሉ። የእግዚአብሔር ቃል እግዚአብሔር ራሱ ቃሉን ባስተላለፈበት ዓውድ ይነገራል እንጂ ቃሉን እኛ በተረዳንበት ልክ ብቻ አይነገርም። የሰው ልጅ በእውቀት የተወሰነ ስለሆነ ማለት ነው። ፪ኛ ጴጥ. ፫፣፲፮ "ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ" እንደተባለው ራሳቸው ለፈጠሩት ግላዊ አመለካከት ብለው የመጻሕፍትን ቃል የሚያጣምሙ ሰዎች በዝተዋል። በዋናነት ግን የሚጎዱት ራሳቸውን ነው። ምክንያቱም ሕይወትም መድኃኒትም ከሆነው ኢየሱስ ራሳቸውን አግልለው ራሳቸው በሕሊናቸው ለፈጠሩትና ማንነት ለሰጡት ነገር ይገዛሉና።

ክፍል ፬ ይቀጥላል ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
3.9K views04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 18:04:03 ትምህርቱን ሼር በማድረግ ያዳርሱ።
------የካቶሊክና የኦርቶዶክስ ልዩነት-----
_ኢየሱስ ማን ነው? ክፍል ፪_
ከካቶሊክ ጋር ያለን ልዩነት በዋናነት በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ካቶሊኮቹ ክርስቶስ አንድ አካል ሁለት ባሕርይ ነው ይላሉ። እኛ ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው እንላለን። መጀመሪያ ኦርቶዶክስ የሚለው ስያሜ የተሰጠን በ325 ዓ. ም በኒቅያ ነው። ቀጥ ያለ ትክክለኛ እምነት ማለት ነው። በሐዋርያት ዘመን ደቀመዛሙርት እንባል ነበር። የሐዋ. 11፣26 "ደቀመዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ" ይላል። ክርስቲያን የተባሉት ቀድመው ደቀመዛሙርት ይባሉ የነበሩት ናቸው። በኋላም ኦርቶዶክስ የተባሉት ቀድሞ ክርስቲያን የተባሉት ናቸው። በ431 ዓ. ም ደግሞ ተዋሕዶ ተብለናል።
+
+
በአካል አንድ በባሕርይ አንድ ከማለታችን በፊት አካል ምንድን ነው? ባሕርይስ ምንድን ነው? የሚለውን መተርጎም ያስፈልጋል። አካል ባሕርይ ያልሆነ ነገር ግን የባሕርይ መገለጫ የሆነ ነው። በግሡ ከሄድን አከለ-በቃ ካለው የሚወጣ ዘመድ ዘር ነው። መብቃትን ያመለክታል። መብቃት ደግሞ በሁለት ይተረጎማል ወሰን ያለው መብቃት እና ወሰን የሌለው መብቃት ነው። ለምሳሌ በእንስራ ውሃ እያደረግን ሲሞላ በቃ እንላለን ወሰን እንዳለበት ለማመልከት ነው። አካል ስንል በሌላ መንገድ መብቃትን ማለትም ምንም እንከን የለሽ መሆንን ያመለክታል። አካል ለእግዚአብሔር ሲነገር ወሰን የለሽ ፍጹም መሆንን ያመለክታል። ስለዚህ አካለ ሥላሴ ሦስት ነው። አብ የራሱ የሆነ በዓለም የመላ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ አለው። የወልድም የመንፈስ ቅዱስም እንዲሁ ነው። በአካል ሲኖሩም አንዱ ካለበት ቦታ ሁሉ በህልውና ሌላኛው አለ። ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. 14፣10 "እኔ በአብ አለሁ አብም በእኔ አለ" ያለው ይህንን ነው። ባሕርይ ማለት ደግሞ መሠረት ተብሎ ይተረጎማል። አካል ያልሆነ ነገር ግን በአካል ያለ አካል የገለጠው ባለቤት ነው። ሌላው ባሕርይ የሚባለው ሦስቱ አካላት አብ ወልድ መንፈስቅዱስ በከዊን (በመሆን) ቃል ልብ እስትንፋስ ናቸው። የኩነታት በሕልውና መገናዘብ ባሕርይ ይባላል። አንዲት ባሕርየ ሥላሴ ሦስት ኩነታት አላት መባሏም በዚህ መሰረት ነው። ወልድ ቃል ነው። ዮሐ. 1፣1 "በመጀመሪያ ቃል ነበር" እንዲል። አብ ልብ ነው መንፈስቅዱስ እስትንፋስ ነው። አንዲት ባሕርየ ሥላሴ በኩነት ትለያለች።
+
+
ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ የሆነ ነው ስንል ሁለት አካል የተባሉ አካለ ሥጋና አካለ ወልድ ናቸው። አካለ ቃል በዓለም የመላ ረቂቅ ነው። አካለ ሥጋ በሦስት ክንድ ከስንዝር የተወሰነ ግዙፍ ነው። ሁለቱ በተዋሕዶ አንድ ሆኑ ማለት ነው። አንድ ሲሆኑ ግን ከተዋሕዶ በፊት ያላቸውን ማንነት ለውጠው ወይም አጥፍተው አይደለም። መምህረ ዓለም ቅዱስ ቄርሎስ "እንተኣሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ወእንቲኣሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል" ቅድመ ተዋሕዶ የቃል ገንዘብ የሆኑት ሁሉ ማለትም ረቂቅነት በሁሉ ቦታ መኖር ለሥጋ ገንዘቡ ሆኑ። ይህም ሲሆን በተዓቅቦ ነው። ተዐቅቦ ማለትም ሥጋ ረቂቅ የሆነው ግዙፍነቱን ሳይለቅ ነው። ቃልም የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ አደረገ ማለትም ረቂቅነቱን በሁሉ ቦታ መኖርን እንደያዘ ግዙፍነትንና በድንግል ማኅጸን መወሰንን ገንዘብ አደረገ። ክርስቶስ በአካል አንድ ነው ማለት ይህ ነው። በባሕርይ አንድ የምንለው ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆነ ማለታችን ነው። ሁለት ባሕርይ የተባሉት አሐቲ ባሕርየ ሥላሴ እና ባሕርየ ትስብእት ናቸው። ባሕርየ ሥላሴ በግብረ ባሕርይ ትገለጣለች። ይኽውም ሁሉን ቻይነት፣ ፈጣሪነት፣ ቀዳማዊነት፣ አለመራብ፣ አለመጠማት የመሳሰሉት ናቸው። ባሕርየ ሰብእ የሚባለውም በመገለጫ የሚራብ፣ የሚጠማ፣ የሚታመም፣ እና የመሳሰለው ነው። ሃይማኖተ አበው ዘሱኑትዩ "ኢይትረከብ ህላዌ ዘእንበለ አካል ወኢአካል ዘእንበለ ህላዌ" አካል ያለ ባሕርይ ባሕርይ ያለ አካል አይገኝም ብሏል። የባሕርይ ምንታዌ ስለሌለ የማይሞተው ሞተ ተባለ። ይህም የሆነው መዋቲን በመዋሐዱ ነው። መዋቲው ሕያው ተባለ ይህም የማይሞተውን በመዋሐዱ ነው። ስለዚህ ክርስቶስ አምላክ የሆነ ሰው ሰው የሆነ አምላክ ነው። ሰው እንደመሆኑ በምራቁ ጭቃን ለወሰ ለመለኮት ምራቅ የለውምና። አምላክ እንደመሆኑ በምራቁ አፈርን ለውሶ ዓይንን አበራ።
+
+
ካቶሊኮቹ የሚያነሱት ሐሳብ ባሕርየ ሥላሴ አንዲት ከሆነች እርሷ የሰውን ባሕርይ ከተዋሐደች አብና መንፈስ ቅዱስ ሰው ሆኑ ያሰኛል የሚል ነው። ነገር ግን ባሕርየ ሥላሴ ባሕርየ ሰብእን በቃልነቷ ከዊን ተዋሐደች የሚል መልስ ነው ያለን። ለዚህም ማስረጃ የሚሆነው ዮሐ. ፩፣፲፬ "ቃል ሥጋ ኮነ" በማለቱ ነው። አካል ብቻ ቢዋሐድ ኖሮስ በአካል ስሙ ወልድ ሥጋ ኮነ ባለ ነበር። ቃል ሥጋ ኮነ በማለቱ ግን የካቶሊካውያንን ነገር አፈረሰው። ሮሜ ፭፣፲ "ጠላቶቹ ስንሆን እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን" እንዲል የአብ ልጅ የማርያም ልጅ ነው። ወልደ አብ ወልደ ማርያም አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በአካል አንድ ነዉ በባሕርይም አንድ ነው። አንድ ስለሆነም ዮሐ. ፫፣፲፮ "አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ዓለሙን እንዲሁ ወዷልና" ተብሏል። ቅዱሳት መጻሕፍትም ክርስቶስን ሁለት ያሉበት ቦታ የለም። እኛና ካቶሊኮች "በመንፈስ ቅዱስ መሥረጽ ጉዳይ" ያለንን ልዩነት በቀጣይ ክፍል አቀርባለሁ።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
(ሃይማኖት በአደባባይ የሚነገር ስለሆነ ጥያቄ ያለው ካለ ይምጣ በአደባባይ እንጠያየቅ)
3.9K views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 11:18:13 የተማማርነውን ባሕረ ሐሳብ በፒዲኤፍ ማንበብ ለምትፈልጉ እነሆ
3.8K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 14:28:54 _በትእግስት ያንብቡ_
ኢየሱስ ማን ነው ክፍል ፩?
Who is Jesus part 1?
ሙስሊሞችም፣ ፕሮቴስታንቶችም፣ ካቶሊኮችም ካላችሁ በነጻነት እስከመጨረሻው መወያየት እንችላለን ኑ።
+
ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረ በኋላም ዓለምን ለማዳን ሥጋ ሰብእን የተዋሐደ አምላክ ነው። ሮሜ ፱፣፭ "ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ ተወለደ እርሱም ከሁሉ በላይ የሆነ የዘላለም ቡሩክ አምላክ ነው" እንዲል። ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለም ከመፈጠሯ በፊት ነበረ ስንል ግን በቃል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ዮሐ. ፩፣፩ "በመጀመሪያ ቃል ነበር፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር፣ ሁሉም በእርሱ ሆነ ከሆነውም ሁሉ ያለ እርሱ ምንም የሆነ የለም" ። መሐመዳውያን ፈጣሪ በአካል አንድ ነው ቃሉ የዚያው የአንዱ ስለሆነ ልክ እንደሰው ነው ለምሳሌ እኛ አንድ ሰው ነን። ነገር ግን ቃል አለን። ቃል ስላለን ብለን ግን በአካል ሁለት ነን አንልም ይላሉ። ነገር ግን ሰውና ፈጣሪ በባሕርይ የተለዩ ስለሆኑ የእግዚአብሔር ቃል እንደሰው ቃል ስላልሆነ ቃሉን የአካሉ ዝርው ንባብ አድርገን መውሰድ አንችልም። ምክንያቱም ለምሳሌ የእኛን የሰዎችን ቃል ብንመለከት እኛ ሰው ነን። ቃላችን ግን የሰው እንጂ ሰው አይደለም። በመሆኑም ቃላችን ሌላ አካል እኛ ሌላ አካል ተብለን ሁለት አንባልም። አንድ አካል እንባላለን እንጂ። የእግዚአብሔር ግን ከዚህ የተለየ ነው። ምክንያቱም በመጀመሪያ ቃል ነበር ካለ በኋላ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር ካለ በኋላ ቃል ራሱ እግዚአብሔር ነው ይላል። እኛ ሰው ነን። ቃላችን ግን ሰው አይደለም። ስለ እግዚአብሔር ስንናገር ግን አብ እግዚአብሔር ነው ቃሉም እግዚአብሔር ነው። በዚህ ቃል መሐመዳውያን ይረታሉ። ሌላው ኢየሱስ ክርስቶስን ነቢይ ነው። ፍጡር ብቻ ነው ይሉታል። ነገር ግን ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. ፰፣፶፰ "አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ" ብሏል። በሌላ ቦታ ደግሞ በማቴ. ፩፣፩ "የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ" ብሎ በመናገር ኢየሱስ ክርስቶስ የአብርሃም ልጅ መሆኑን ተናገረ። ሁለቱም ልክ ነው። በቃል ከአብርሃም በፊት የነበረ የአብርሃም ፈጣሪ በሥጋ ከአብርሃም ዘር ተወለደ ስለዚህም የአብርሃም ልጅ ተባለ። ጥያቄ ለመሐመዳውያን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰው ብቻ ነው ፈጣሪ አይደለም ካላችሁ ከአባቱ በፊት የነበረ ልጅ አለ ወይ?። የለም በፍጡራን ዘንድ ከአባቱ ቀድሞ የነበረ ልጅ የለም። የዘካርያስ ልጅ መጥምቁ ዮሐንስ በሥጋ በመወለድ ከክርስቶስ ይቀድማል። ሉቃ. ፩፣፭-፹ ይመልከቱ። ነገር ግን ዮሐንስ ስለጌታ ሲናገር ዮሐ. ፩፣፳፮ "እኔ በውሃ አጠምቃችኋለሁ ነገር ግን እናንተ የምታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ በፊት የነበረው" ብሎታል። ይህም በቃል ይቀድመዋል። ድንግል ማርያም የወለደችው ዮሐ. ፩፣፫ ላይ ሁሉ በእርሱ ሆነ የተባለውን እሷን የፈጠራትን ወልድን ነው። አፈ በረከት ኤፍሬም በሃይ. አበ. ፵፯፣፪ "ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱን ፈጠረ" ይላል። አስቀድሞ "ቃል" የተባለውና ሰማይና ምድርን አጠቃላይ ፍጥረታትን የፈጠረው እርሱ አዳም በተሳሳተ ጊዜ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለሁ ብሎት ነበርና ሰውን ለማዳን ረቂቅ ኃያል በሁሉ ቦታ ያለ አምላክ በሁሉ ቦታ መኖሩን ሳይለቅ በድንግል ማኅፀን ተወሰነ፣ ረቂቁ እና የማይታየው የማይዳሰሰው አምላክ አለመዳሰስን ርቀትን እንደያዘ መዳሰስን ግዘፍን ገንዘብ አደረገ። ኃያሉ አምላክ ኃያልነቱን ሳይለቅ ድኩም ሥጋን ተዋሐደ። መዝ. 101፣27 አንተ ግን ያው አንተ ነህ ስለተባለ እግዚአብሔር መለዋወጥ የለበትምና። ለእኛ ያለውን ፍቅር ለእኛ ለማሳየት እኛ ባጠፋን እርሱ ስለእኛ ተሰቀለ። በኪሩቤል ጀርባ እንዳለ በተዋሐደው ሥጋ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ታየ። አዳም እፀ በለስን ከበላ የሞት ሞት እንደሚፈረድበት ዘፍ. ፪፣፲፯ "ከእርሱ (እፀበለስ) በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ" ብሎታል። አዳም ግን ትእዛዙን ተላልፎ ዘፍ. ፫፣፮ ላይ እንደተጻፈው በላ። ስለዚህ አዳም ሞተ ነፍስ አገኘው ከእግዚአብሔር ተለየ። ስለዚህ እንዴት አዳነው ስንል ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገባለት።ገላ. ፬፣፬ "ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ" ይላል። ስለዚህ አዳምን ለማዳን እግዚአብሔርነቱን ሳይለቅ ሰው ሆኖ ተወለደ። ሳይሰቀል ማዳን አይችልም ወይ ከተባለ ይችላል። ታድያ ለምን ተሰቀለ ከተባለ እኛ ልንከፍለው የሚገባንን እዳ እርሱ ከፍሎ ሲያድነን ለእርሱ ያለን ፍቅር ይጸና ዘንድ ነው። እንዲሁ ሳይሰቀል ኃጢአታችንን ይቅር አይለንም ነበር ወይ ከተባለ ደግሞ እግዚአብሔር በእውነት ፈራጅ ነው። መዝ. 50፣6 "እግዚአብሔር ፈራጅ ነው" እንዲል። አዳም ላጠፋው ጥፋት ፍርዱ ሞት ነው። እግዚአብሔር መሓሪም ስለሆነ የአዳምን እዳ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ከፈለለት።
+
ታድያ ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው? ሰው ብቻ ነውን ቢሉ መልሳችን አምላክም ሰውም የሆነ ነው ነው እንላለን።

ክፍል ፪ ይቀጥላል።
5.9K viewsedited  11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ