Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 70

2022-10-01 12:55:10
_______እንኳን ደስ አላችሁ________
የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የመጻሕፍተ ሐዲሳትና የመጻሕፍተ ሊቃውንት ምስክር ጉባኤ ቤት በዛሬው ዕለት ፳፩ ደቀመዛሙርትን አስተምሮ አስመርቋል። በዕለቱም የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ እና የቀድሞው የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ፣ የሀገረ ስብከት ሰራተኞች እንዲሁም የጎንደር አድባራት ሊቃውንት እና አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል። ቤተክርስቲያን ልጆቿን ካባ አልብሳ፣ ሑሩ ወመሀሩ ብላ መርቃቸዋለች። እንኳን ደስ አላችሁ። እንኳን ደስ አለን።

መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አጼ ፋሲል ያሰራት ስትሆን ከዚያው ከፋሲል ግቢ ውስጥ በምእራብ አቅጣጫ ትገኛለች። ግምጃ ቤት ማርያም ብዙ ጳጳሳት እንዲሁም ሊቃውንት ተምረው የወጡባት ታላቅ ደብር ናት። በደርቡሽ ሰማዕት የሆኑት ታላቁ መምህር ወልደ አብ ወልደ ሚካኤል ያስተማሩባት ደብር ናት። አሁን በማስተማር ላይ ያሉት የኔታ መጋቤ ሐዲስ ቃለ ሕይወት በዛ የሐዲሳትና የሊቃውንት ምስክር መምህር ናቸው።

የእለቱ ተመራቂዎች እንዲሁም ምእመናን በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ።
2.3K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 22:42:34
By the way we should have to know the difference between Mythology & History.
.
ታድያ ከጎጆ ጋር ምን አገናኘው ልትለኝ ባልሆነ!? እይውልህ ይችን ጎጆ የሰራት ኩሽ ነው። ኩሽ ደግሞ ጎጆዋን ከሰራት በኋላ ተወለደ። ዓይነት ንግግሮች ልብ ወለድ ናቸው። ወንድሜ ኩሽ አባቴ ነው ብለህማ አትመካ የእኔም ሴም አባቴ ቢሆንኮ ኩሽ አጎቴ ነው አትዘንጋ እንጂ። ከምንም በፊት አያታችንኮ ኖኅ ነው። ችግሩ እስኪ ዘርህ የካም ይሁን የሴም ቆጥረህ ንገረኝ ብልህ አታውቀውም። ዓለም ብዙ ጊዜ በተለያዩ ምክንያት አንዱ ወደ አንዱ እየፈለሰ ተደበላልቋል። ስለዚህ ቋንቋን መሰረት አድርገህ ኩሻዊ ነኝ ሴማዊ ነኝ እንዳታል ቋንቋን ማንም ተምሮ ይናገረዋል። ዘርን አይለይም። እኔ የያፌት ወይም የሴም ወይም የካም ዘር ነኝ እንዳትል በእናትህም በአባትህም ቆጥረህ አታውቀውም። እስከ ካም በሁሉም ጎን መቁጠር አታችልም። ስለዚህ ቆሻሻ ሰዎች በምናባቸው የፈጠሩትን ይዘህ አትጣላ። ይልቅስ በአንድ ሆነን የጋራ ምርጥ ኮሚዩኒቲ እንፍጠር። ታሪክን እና ተረትን እየለየን። ታሪክ ማስረጃ አለው። ተዋረዳዊነት አለው። ያም ሆኖ ፍጹም አይደለም። በየዘመኑ በተገኙ ማስረጃዎች ሊጨመርም ሊቀነስም ይችላል። ተረትን ከታሪክ ማስገባት ግን ነውር ነው።
2.8K views19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 20:50:18
_ሀገራዊ ውሸት___
ከ12 ሺ ዓመታት በፊት የሚባል ነገር የለም። በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ምርመራ ያውም ሉሲን ብቻ መሰረት አድርጎ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ እያሉ ያደነቆሩን አካላት አሁን ደግሞ ከ12ሺ ዓመታት በፊት የኩሽ ዘሮች ኢሬቻን ያከብሩ ነበር የሚል ውሸት መጣ። በነገራችን ላይ ራሱ ኩሽ የነበረበት ዘመን እንኳ ከ5000 እስከ 6000 ዓመታት ባሉት የተወሰነ ነው። ይህም ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ማን ማንን ወለደ በሚለው ቆጥረን ማግኘት ይቻላል።


ሀገር በውሸት አትከብርም። ውሸታም ሚዲያዎች ውሸታም ትውልድ ይፈጥራሉ። እውነተኛውን ታሪክ እየቀበራችሁ ውሸቱን ብትተነትኑት ትርፉ የራሳችሁ ቅሌት ነው። ትውልዱ ግን ከእንደነዚህ ዓይነት ሚዲያዎች ራሱን ያርቅ ወይም እኒህን ሚዲያዎች ያስተካክል።ሀገር በውሸት አትከብርም። ውሸታም ሚዲያዎች ውሸታም ትውልድ ይፈጥራሉ። እውነተኛውን ታሪክ እየቀበራችሁ ውሸቱን ብትተነትኑት ትርፉ የራሳችሁ ቅሌት ነው። ትውልዱ ግን ከእንደነዚህ ዓይነት ሚዲያዎች ራሱን ያርቅ ወይም እኒህን ሚዲያዎች ያስተካክል። ዓለም ከተፈጠረች ራሱ ገና 8000 ዓመት አልሞላትም። 7515 ዓመቷ ነው። ልብ ወለድ እውነት ሆኖ ይነገራል እንዴ? ተው እንጂ ጎበዝ።
2.8K viewsedited  17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 11:51:55
__የኢሬቻ በኣል__
ፋና እንደዘገበው ፈጣሪ የሚመሰገንበት በዓል ከሆነ "ውድ ክርስቲያኖች ከዚህ በኣል መገኘት የለባቸውም። ምክንያቱም የምሥጋና መሥዋዕት እና ጸሎት ለልዑል እግዚአብሔር የሚቀርብ ነው። ሲቀርብ ደግሞ የሚያምኑና የማያምኑት በአንድ ላይ ሆነው አይደለም። የሚያምንና የማያምን በአንድ ሀገር በአንድ ጎረቤት በፍቅር በማህበራዊ ሕይወት መኖር ይችላሉ። ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ማለትም ጸሎትን፣ ምስጋናን ግን በአንድነት ማክበር አልተፈቀደም። ኢትጸሊ ምስለ አርሲሳን ተብሏል። ሌላ ሃይማኖት ካላቸው ሰዎች ጋር አትጸልይ ተብሏልና። ስለዚህ ክርስቲያኖች ከእንደዚህ ዓይነት በኣላት ራሳቸውን አርቀው የራሳቸውን በዓል ሊያከብሩ ይገባል። ቅዳሜ መስከረም ፳፩ ብዙኃን ማርያም ናት። ሠለስቱ ምእት የአርዮስን የስህተት ትምህርት ለማውገዝ የተሰበሰቡበት ነው። ህዳር ፱ ቀንም አውግዘው የለዩበት ነው። ስለዚህ ምእመናን ከባዕድ አምልኮ መውጣት ይጠበቅባቸዋል።


ጥያቄ ካለ መጠየቅ ይቻላል። ኢአማኝ ከሆኑ ሰዎች ጋር የምስጋናን መሥዋእት ለፈጣሪ ማቅረብ ኃጢኣት ነው። ሃይማኖተ አበው ሕንጻ መነኮሳትንና ፍትሐ ነገሥትን ማየት ይቻላል። ብሄርተኝነትንና ሃይማኖትን ለመቀላቀል አትሞክሩ። ሃይማኖታዊ ጉዳይ ማለትም ጸሎት ምስጋና ወዘተ በሃይማኖታዊ ሥርዓት ይከናወናል። ብሄራዊ ጉዳይን እና ሃይማኖታዊ ጉዳይን እየለየን ጎበዝ።ኢሬቻ ባህላዊ ከሆነ ግን ማለትም የፈጣሪ ምስጋናን ጨምሮ ምንም ዓይነት ዓይማኖታዊ ሥርዓት የማይከናወንበት ከሆነ ግን እንደ ባህሉ መሰብሰብ መነጋገር ማህበራዊ ቀውሶችን መፍታት ይቻላል። ጉዳዩ ፈጣሪን ከማመስገን ጋር የሚገናኝ ከሆነ ግን ፍጹም ክርስቲያኖች ይህን በኣል ማክበር የለባቸውም።
4.0K viewsedited  08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 23:04:21 ገብርኤል ብሂል ብእሲ ወአምላክ። እምኀበ እግዚአብሔር ዘተፈነወ ላእክ።

መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ለዓለም የምስራችን ይዘህ የመጣህ አንተ ነህ። ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም የሚያስቡልን የሚንከባከቡን ከሰይጣን ወጥመድ የሚያድኑን ናቸው። የቅዱሱ መልአክ ተራዳኢነት አይለየን።
268 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 08:21:30 _ኒቁስጣኑ ኒቁስጣጣኑ_
በዓለመ መላእክት ሳጥናኤል ቅዱሳን መላእክትን በገጠማቸው ጊዜ ያሸነፉት በረቂቅ ክንፋቸው የነበረውን መስቀል አሳይተው በረድኤተ እግዚአብሔር ነበር። መስቀል የአሸናፊነት ምልክት ነው።

መስቀል በኋላም ክርስቶስ ሰይጣንን ከምድር ከፍ ከሰማይ ዝቅ አድርጎ ያሰቃየበት አደባባይ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም መዳን ደሙን ያፈሰሰበት መስቀል ነው። ቅዱስ ያሬድ በድጓው መስቀል ሞዐ ሞት ተሞዐ ብሏል። መስቀል አሸነፈ ሞት (ዲያብሎስ) ተሸነፈ ማለት ነው።

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በሰማይ ኒቁስጣኑ ኒቁስጣጣኑ ተብሎ ተጽፎ አየ። በእኛ ሀገር ትርጉም በዚህ መስቀል ጠላቶችህን ታሸንፋለህ ማለት ነው። ንጉሡም ከጦሩ የመስቀል ምልክትን አድርጎ ከመክስምያኖስ ጋር ጦርነት ቢገጥም መክስምያኖስን አሸንፎታል። ስለዚህ መስቀል አሸናፊ ነው።

ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀሉ ተአምር እያደረገ ስህተታቸውን ስለገለጠባቸው አይሁድ ቀበሩት። በኋላ ግን ንግሥት ዕሌኒ አረጋዊው ኪራኮስን (ኪሪያኮስን) አማክራ ከተቀበረበት ከ300 ዓመታት ገደማ በኋላ አውጥታዋለች። ደመራ አስደምራ በደመራው ዕጣን ጨምረችበት። ጢሱም ከፍ ከፍ ብሎ መስቀሉ የተቀበረበትን አሳየ። በዚህ መልኩ ተቆፍሮ ወጥቷል። ዘዕጣን አንጸረ ሰገደ ጢስ መባሉ ለዚያ ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ይቅር አለን። ነገረ መስቀሉን ሁልጊዜም እናስበው ዘንድ መሓሪ እግዚአብሔር ይርዳን።
1.1K views05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 08:18:32
እንኳን ለበዓለ መስቀል በሰላም አደረሳችሁ።
"መስቀል ሞዐ። ሞት ተሞዐ
መስቀል አሸነፈ። ሞት ተሸነፈ"
ቅዱስ ያሬድ
መስቀልን ስናስብ አሸናፊነትን፣ ይቅርታን፣ ፍቅርን፣ ትዕግሥትን፣ ትሕትናን፣ አርምሞን(ዝምታን)፣ መድኃኒትነትን እናስባለን።
1.1K views05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 21:22:07 እስካሁን የተማማርናቸው ስድስቱ ሕገጋተ ወንጌል እና አስሩ ትእዛዛት በአጭር በአጭሩ በፒዲኤፍ እነሆ። ፒዲኤፉን ያዘጋጀልኝ "ዲ/ን ዶ/ር ይታገሱ ሰይፉ" ነው። እግዚአብሔር ያክብርልኝ። ያንብቡ ይጠይቁ።
278 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 21:21:07 በሥርዓተ ቤተክርስቲያን ዙሪያ በስፋት የሚያስተምረን ፍትሐ ነገሥት ነው። በአጭር በአጭሩ የተማማርነውን ፍትሐ ነገሥት በዚህ መልኩ በፒዲኤፍ ስለተዘጋጀ ማንበብ ትችላላችሁ።
723 views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ