Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 71

2022-09-24 21:19:57 በደንብ በጉልህ ተሻሽሎ የወጣሁ እስካሁን የተማማርነው የግእዝ ትምህርት ነው። ለሚፈልግ አካል ሼር አድርጉለት።

ግእዝ እንማር
158 views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 19:03:57 እስካሁን የተማማርናቸው ስድስቱ ሕገጋተ ወንጌል እና አስሩ ትእዛዛት በአጭር በአጭሩ በፒዲኤፍ እነሆ። ፒዲኤፉን ያዘጋጀልኝ "ዲ/ን ዶ/ር ይታገሱ ሰይፉ" ነው። እግዚአብሔር ያክብርልኝ። ያንብቡ ይጠይቁ።
580 views16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 15:37:13 --------የፈጣሪ ትእዛዝ ክፍል ፲------
ከአስሩ ትእዛዛት የመጨረሻው ሌላውን ሰው እንደ ራስ መውደድ ነው። ለራሳችን የምናስበውን መልካም ሐሳብ ለሌሎችም መመኘት፣ ለእኛ ሊደረግልን የምንፈልገውን ለሌላውም እንዲደረግ መፈለግና ማድረግ ናቸው። በእኛ ሊሆንብን የማንፈልገውን በሌላውም እንዳይሆን መመኘት ነው። ባልንጀራውን እንደራሱ የሚወድ ሰው በሰዎች ደስታ ይደሰታል በሰዎች ኀዘን ደግሞ ያዝናል። ለሁሉም ሰው መልካም አሳቢ ነው። የማንንም መጥፋት አይፈልግም። አንድ ሰው አጥፍቶ ቢገኝ እንኳ ለንሥሓ እንዲያበቃው ይመኛል እንጂ ጥላቻ የለበትም። ይህንን ሕግ የሚፈጽም ሰው ዘረኝነትን አያውቀውም። ሰው ዘረኛ የሚሆነው ባልንጀራውን እንደራሱ አለመውደድ ሲጀምር ነው። ኦርቶዶክሳዊው ሕይወት ግልጽና ውብ ነው። ሰው ከኦርቶዶክሳዊው ሕይወት እየራቀ ሲሄድ እየከፋ ይሄዳል። አንድ ሰው ጥሩ ነው የሚባለው ኦርቶዶክሳዊ ሲሆን ነው። ኦርቶዶክሳዊነት እውነትን ከጥበብ፣ ፍቅርን ከፍትሕ፣ ትሕትናን ከሙሉ ሰብእና ጋር አጣምሮ የያዘ ማንነት ነው። ኦርቶዶክሳዊው ሕይወት ራስ ወዳድነት የለበትም። አንዱ ለሁሉ ያስባል። ሁሉም ለአንዱ ያስባል። የኦርቶዶክሳዊነት ማዕከሉ ክርስቶስ ነው።

ዘሌ. ፲፱፣፲፰ "አትበቀልም፥ በሕዝብህም ልጆች ቂም አትያዝ፥ ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ"።

አነሳስቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስፈጸመን ልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይገባል።
968 views12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 13:07:43 --------ትእዛዘ ፈጣሪ ክፍል ፱-------
እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ሰው የሰጠው ጸጋ ልዩ ልዩ ስለሆነ አንዱ በሌላው መመቅኘት፣ መቅናት እንዲሁም መፈካከር አይገባውም። ምክንያቱም ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ምቀኝነት፣ ቅንዐትና ፉክክር የሥጋ ፍሬዎች ናቸው። እኛን ወደሲኦል የሚመሩን ክፉ መንገዶች ናቸው። ገላ. ፭፣፳። ሰው ራሱን ከማንም ጋር ማወዳደር አይገባውም። ራሱንም መለካት ያለበት ከእግዚአብሔር ሕግ አንጻር ነው እንጂ ከሰው አንጻር አይደለም። እግዚአብሔርም ዋጋ የሚሰጠን ከሰዎች ምን ያህል ተሽላችኋል በሚለው ሳይሆን ሕጌን ትእዛዜን ምን ያህል ጠብቃችኋል ብሎ ነው። የሌላ ሰው ንብረት የሌላ ነው። እኛ ልንመኘው አይገባንም። እኛ በራሳችን ሰርተን ያን የመሰለ ልናፈራ እንችላለን እንጂ ያንኑ ራሱን መመኘት ኃጢዓት ነው። ሁሉም በተሰጠው ጸጋ ያመስግን እንጂ አንዱ በአንዱ መቅናት አይገባውም። አንዱ የአንዱን አይመኝ።

ዘፀ. ፳፣፲፯ "የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፤ የባልንጀራህን ሚስት ሎሌውንም ገረዱንም በሬውንም አህያውንም ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ"።
1.1K views10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 11:18:05 -------የፈጣሪ ትእዛዝ ክፍል ፰------
በቀድሞ ዘመን በሐሰት የመሰከረ ሰው ምላሱ ይቆረጥ ነበር። ሌላውም ይህንን እያየ አይዋሽም ነበር። ውሸት እያደር ያቀላል። ውሸት ያልተደረገውን እንደተደረገ የተደረገውን እንዳልተደረገ መናገር ነው። ውሸት የሆነውን እንዳልሆነ ያልሆነውን እንደሆነ አድርጎ መናገር ነው። ውሸት የአንደበት ኃጢዓት ነው። በንግግር ሊገለጽ ይችላል። በጽሑፍ ሊገለጽ ይችላል። የውሸት ተቃራኒ እውነት ነው። በሐሰት መመስከር ትልቅ በደል ነው። ክርስቲያን እውነቱን እውነት ሐሰትን ሐሰት የሚል ነው። ለእውነት ትልቅ ክብር አለው። ቅዱሳን ሰማእታት እውነትን ተናግረው ለእውነት ሞቱ። በውሸት ከመኖር በእውነት መሞት ይበልጣልና። ትልቅ ክብር አለውና። ዋሾ ሰው ለራሱ፣ ለጓደኛው፣ ለዘመድ፣ ለቤተሰብ፣ ለሀገር አይታመንም። ውሸትን መታገል ይገባል። ሰው ለተርእዮ፣ ለመከበር፣ ለሥጋዊ ጥቅም ሊዋሽ ይችላል። ነገር ግን የውሸት እድሜዋ አጭር ስለሆነ በኋላ ከሚያፍር እውነቱን ተናግሮ ቢኖር ይሻለዋል። ሰው እውነት መናገር ቢያቅተውንኳ ውሸት ላለመናገር ዝም ማለት አለበት።

ዘፀ. ፳፣፲፮ "በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር"።
1.2K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 09:48:24 -------የፈጣሪ ትእዛዝ ክፍል ፯------
ስርቆት ያልለፉበትን ገንዘብ ለራስ ማድረግ ነው። ስርቆት ሌሎች የለፉበትን ገንዘብ በውንብድና፣ በማጭበርበር፣ በተንኮል፣ በዝርፊያ መቀማት ነው። የሌላውን ገንዘብ የእኔ ነው ማለት ሌብነት ነው። በቀድሞ ዘመን ሌባ ሲሰርቅ ከተገኘ እጁን ይቆረጥ ነበር። ሌላውም ያንን እያየ አይሰርቅም ነበር። በስርቆት ምክንያት እናት ከልጅ ሳትገናኝ ትቀራለች። የብዙ ሰዎች ሕይወት ምስቅልቅል ይላል። ክርስቲያን ወጥቶ ወርዶ ሰርቶ ባገኘው ገንዘብ መኖር አለበት እንጂ አይሰርቅም። በክርስትና መስራት የማይችል ሰው ቢኖር እንኳ ይለምን እና ይብላ ይላል እንጂ ይስረቅ አይልም። ያጣ ይለምን ነው የተባለ። ጉቦ፣ ሙስና የስርቆት ዓይነቶች ናቸው። ሰው በብቃቱ ተወዳድሮ ሀገርን መጥቀም ሲገባው ብቁ ሰዎች እየተገፉ ደካማ ሰዎችን በዝምድና፣ በጉቦ፣ በዘር፣ በቋንቋ መቅጠር ሀገራችንን በጠቅላላው ዓለማችንን እየበጠበጣት ይገኛል። ሁሉም ከተንኮል ወጥቶ በሚችለው ተከባብሮ እየሰራ ሀገሩን ማሳደግ ይኖርበታል። እግዚአብሔር ለሁላችንም ልዩ ልዩ ጸጋ ሰጥቶናል። በተሰጠን ጸጋ ሳንኮራ አንድም ሳናፍር በትሕትና መስራት ከስርቆት ያድናል። ብዙ ሰው ወደ ስርቆት የሚሄድ ዝቅ ብሎ እንዳይሰራ ወይም እንዳይለምን ኩራት ይዞት ነው። ነገር ግን ኩራት የሥጋ ሥራ ነው። ገላ. ፭፣፳። ሲጀምር ከእግዚአብሔር ባገኘነው ጸጋ ማፈርም መኩራትም አይገባም። ኩራት የአላዋቂዎች ሥራ ነው። ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሥራ እድል ማመቻቸት ከመንግሥት ይጠበቃል። ነገር ግን ሥርዓተ መንግሥቱም ለሌብነት የተስማማ ከሆነ ትልቅ አደጋ ነው። አትስረቅ ብሎ ማስተማር አንድ ነገር ነው። በተጨማሪም አትስረቅ ላልነው አካል ሥራ መፍጠር ግዴታ ነው። በዋናነት ችግሩን ብቻ ሳይሆን የችግሩን ምንጭም ማጥፋት ወሳኝ ነገር ነውና። ሌላው አስራትን አለማውጣትም ሌላኛው የስርቆት ዓይነት ነው። አስራት የሚሰጠው ደግሞ ለቤተክርስቲያን ነው። አስራት ለግለሰብ አይሰጥም ነውር ነው።

ዘጸ. ፳፣፲፭ አትስረቅ።
1.1K views06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 08:33:51 -------የፈጣሪ ትእዛዝ ክፍል ፮------
ሴት ልጅ/ ወንድ ልጅ ሌላውን በዝሙት ለመሳብ የሚለብሱት ልብስ፣ የሚያደርጉት ጌጥ የምንዝር ጌጥ ይባላል። ይህን ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ የሥጋ ሥራ ብሎታል። ገላ. ፭፣፳፩ "ይህንን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግሥት አያይም ተብሏል"። አንድ ሰው ሌላውን ለዝሙት የሚያነሳሳ አለባበስ ማለትም ሰውነትን ጥብቅ አድርጎ የሚያሳይ አለባበስ ወይም ራቁትን የሚያጋልጥ ልብስ መልበስ አይገባውም። ቅዱስ ጳውሎስ ቀጥሎም መዳራትን የሥጋ ሥራ ብሎታል። መዳራት የሚባለው የእጅ ጉንተላ፣ የዓይን ጥቅሻ፣ የነገር ጉሰማን የሚያጠቃልል ቃል ነው። እኒህ ነገሮች ሁሉ ወደ ዝሙት የሚስቡ ነገሮች ስለሆኑ ሰው ከእነዚህ መራቅ አለበት። ማግባት ቢፈልግ እንኳ በሥርዓት ጠይቆ፣ በሥርዓት ቆይቶ መሆን አለበት። ገና እጮኛማቾች ነን ተብሎ ፍትወት ቀስቃሽ ንግግር፣ እንዲሁም አካላዊ ንክኪ ማድረግ አይገባም። የሰው አካሉ ክቡር ነው። ስለዚህም አካሉንም ሕሊናውንም በንጽሕና ማቆየት ይጠበቅበታል። ሰውነትን ማርከስ አይገባም። ርኩሰት የሥጋ ስራ ነው ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ ነግሮናልና። ማንኛውም ሰው የእርሱ/የእርሷ ካልሆነች/ካልሆነ ሴት/ወንድ ጋር ግንኙነት ከፈጸመ/ከፈጸመች ዝሙት ሰራ/ሰራች ይባላል። አታመንዝር ያለውን ሕግ መሻር ስለሆነ በነፍስም በሥጋም ቅጣትን ያመጣል። ማንኛችንም ሰዎች ራሳችንን በብዙ ረገድ በንጽሕና መጠበቅ ይገባናል። ገላ. ፭፣፲፱-፳

ዘፀ. ፳፣፲፬ "አታመንዝር"።
1.1K views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 19:52:15 _ትእዛዝ ፈጣሪ ክፍል ፭____
የሰው ልጅ የእግዚአብሔር አምሳል ነው። ዘፍ. ፩፣፳፮ "ሰውን በአርያችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር" ተብሎ እንደተጻፈ። ሰው እግዚአብሔርን የምናይበት የእግዚአብሔር አርዓያ እና ምሳሌ ነው። ስለዚህም ከሌሎች ፍጥረታት የከበረ ነው። በተለይም የክርስቲያን ሰውነት የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተብሏል። መግደል የእግዚአብሔርን አርዓያ ወይም ምስል ማጥፋት ነው። መግደል የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ማፍረስ ነው። ሰው ሰውን ማክበር አለበት። ተከባብሮ ተዋዶ መኖር የሰውነት ትክክለኛ ትርጉሙ ነው። አለመግባባትን ያለ ደላላ ቀጥታ በመወያየት መፍታት ልዩነቶችን ያጠባል። በሀገራችን እየሆነ ያለው ጥላቻ መገዳደል ባለጉዳዮች ፊት ለፊት ከመነጋገር ይልቅ በየራሳቸው መሄዳቸው ነው። በመካከል ደላሎች እውነተኛውን ጥያቄ እና ችግር አደብዝዘው የሌለ ፈጥረው፣ ያለውን አስፍተው በማቅረባቸው ነው። አንዳንድ ጉዳዮች ሊያስቆጡን ይችላሉ። ነገር ግን ቁጣችንን በትዕግሥት አብርደን ጥልን በዕርቅ እና በይቅርታ ማፍረስ ይገባናል። ምክንያቱም። ቁጣ፣ ጥል እና መግደል ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው የሥጋ ፍሬዎች ናቸውና። ፍጻሜያቸውም እኛን ወደ ሲኦል ማስገባት ነው።ገላ. ፭፣፳ ። ባንገዳደልምኮ መሞታችን አይቀርም። ስለዚህ መሞታችን ካልቀረ ተስማምቶ፣ ይቅር ተባብሎ፣ በአንድነት መንፈስ ብንኖር እንጠቀማለን። ለልጆቻችን ለወንድሞቻችን የመገዳደል ታሪክ አናውርሳቸው። ይቅር ተባብለን። ሰላምን እናውርስ።

ዘፀ. ፳፣፲፫ "አትግደል"።
954 views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ