Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 75

2022-09-06 18:55:29 #ግእዝ #ክፍል #፷፪
-----------ነገረ ግሥ ወአገባብ ክፍል ፩ -----------
#መሣግር:- መሣግር የሚባለው በዝርዝር ጊዜ ካልዓይ አንቀጹን የቀተለን በቀደሰ፣ የቀደሰን በቀተለ፣ የገብረን በሰብሐ፣ የሰብሐን ወደ ገብረ፣ የክህለን ወደ ቀደሰ እየለዋወጠ የሚዘረዝር ማለት ነው። መሣግር የሚሆኑ ፊደላት "ሀ፣ ረ፣ አ፣ ወ፣ ዘ" ናቸው።
_
"ሀ":- የሰብሐን ወደ ገብረ ሲያሠግር ገንሐ ብሎ ካልዓዩ ይገንሕ ይላል። "ሀ" የቀተለን ወደ ቀደሰ ሲያሠግር መሀረ አስተማረ ብሎ ይሜህር ያስተምራል ይላል።
_
"ረ":- የቀደሰን ወደ ቀተለ ሲያሠግር ጠፈረ ብሎ ካልዓዩ ይጠፍር ይላል።
_
"አ":- የክህለን ወደ ቀደሰ ሲያሠግር ርእየ አየ ብሎ ይሬኢ ያያል ይላል።
_
"ወ":- የቀተለን ወደ ቀደሰ ሲያሠግር ወጠነ ጀመረ ብሎ ይዌጥን ይጀምራል ይላል።
_
"ዘ":- የቀተለን ወደ ቀደሰ ሲያሠግር ነዘረ ብሎ ይኔዝር ይላል። የክህለን ወደ ቀደሰ ሲያሠግር ተዝኅረ ብሎ ይዜኀር ይላል።

+
#ሕርመት:-በቀዳማይ መልተው በካልዓይ የሚጎድሉ ግሦች ሁለት ናቸው። እነዚህም ወሀበ እና ክህለ ናቸው። እኒህም ግሦች ሕርመት ይባላሉ። አወራረዳቸውም ወሀበ-ሰጠ ብሎ ይሁብ-ይሰጣል፣ የሀብ-ይሰጥ ዘንድ፣ የሀብ-ይስጥ ይላል። ክህለ-ቻለ ብሎ ይክል-ይችላል፣ ይክሀል-ይችል ዘንድ፣ ይክሀል-ይቻል ይላል። እነዚህ ግን በአራቱ አዕማድ ሲገቡ ያጎደሉትን ቀለም ያስገኛሉ። ይኽውም ተውህበ

+
#የቆመ ቤቶች ሳድስ ቅጽላቸው በመካከል ሳድስ " ው"ን አምጥተው ይወጣሉ። ይህም ከሌሎች የተለየ ነው። ለምሳሌ የቀደሰ ሳድስ ቅጽል ቅዱስ ነው። "ዱ" ካዕብ ነው። ቆመ ብሎ ቅውም ሲል ግን "ው" ሳድስ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።

+
'ኀሠሠ' የመሰሉ ግሦች በብዙ በካልዓት በዘንድ እና በትእዛዝ አንቀጽ፣ በአንድ ወንድና በአንድ ሴት ዝርዝር ያጎድላል። ለምሳሌ "ነበበ-ተናገረ" ይላል። በብዙ ነበብክሙ-ተናገራችሁ ይላል። በካልዓይ "ትነቡ-ትናገራላችሁ" ይላል ማለት ነው። በትእዛዝ አንቀጽ ደግሞ "ንቡ-ተናገሩ" ይላል። ተጨማሪ ምሳሌ "ኀሠሠ" ን ብንመለከት። በብዙ "ኀሠሥክሙ-ፈለጋችሁ" ይልና። በትእዛዝ አንቀጽ "ኅሡ-ፈልጉ" ይላል። 'ኀሠሡ-ፈለጉ' ይልና በትእዛዝ "ይኅሡ-ይፈልጉ" ይላል። በአንዲት ሴት ደግሞ በዝርዝር ኀሠሠቶ-ፈለገችው ብሎ በካልዓይ አንቀጽ "ተኀሦ-ትፈልገዋለች" ይላል።
1.6K views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 16:54:51 New Life Principle for New year. New Hope, New Mind set.በአዲሱ ዓመት ምን እናድርግ? ፲ ሐሳቦች:-
፩ኛ) ካህናትን፣ ጳጳሳትን፣ አባቶቻችንን፣ መምህራንን ማክበር መውደድ። ይህ ካልተቻለ ቢያንስ በአደባባይ አለመስደብ መቻል አለብን። የቤተክርስቲያን ተቆርቋሪ መስሎ አባቶቻችንን የሚሳደብ አይኑር። ባመሰገንበት አንደበት አንሳደብበት።

፪ኛ) የሰው ተከታይ አንሁን። ፍጽምት እና የማትሳሳት የክርስቶስ ሙሽራ ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት። ስለዚህ ላልሞተ ሰው ጥብቅና አትቁም። አርዓያ ማድረግ ካለብህም በተጋድሎ ዓለምን አሽነፈው ያለፉ ቅዱሳንን አብነት አድርግ።

፫ኛ) በሰው ከመፍረድህ በፊት ጠይቅ። የእኛ እውቀት በዘመን በቦታ የተገደበ ነው። እኛ የማናውቀው ጉዳይ ብዙ ነው። ስለዚህ ለማወቅ በትሕትና ሆነን ማንበብ፣ መጠየቅ አለብን።

፬ኛ) እውነት ይምራን። ግላዊነትን አጥፍተን አንድነት ላይ እናተኩር። ልዩነቶቻችንን ፊት ለፊት እየተወያየን እያጠበብን የጋራ ዓላማዎቻችን ውጤት እንዲያመጡ የየበኩላችንን እንወጣ።

፭ኛ) የሰው ልጅ በማወቅም ባለማወቅም ፈጣሪንም ሰውንም ይበድላል። ስለዚህ ለበደላችን በንሥሓ ይቅርታ እንጠይቅበት።

፮ኛ) ለሕይወታችን ሕይወት የሆነውን የክርስቶስን ሥጋና ደም ንሥሓ እየገባን እንቀበል።

፯ኛ) ራሳችንን ችለን እናስብ። ለሁላችንም ነጻ አእምሮ ስላለን በመንጋነት ሳይሆን በራሳችን ኅሊና እናስብ። የሰው አምላኪ አንሁን። ሕሊናችንን ለሰዎች ግላዊ ምልከታ ባሪያ አናድርገው። ማንኛውንም ነገር እንመርምረው።

፰ኛ) ቤተክርስቲያን የሕይወት ምንጭ ናት። ሕይወት የሆነው ቃለ እግዚአብሔር የሚሰጥባት ናት። ስለዚህ ትምህርቷን ቀርበን እንማር።

፱ኛ) የሰው ሁሉ አባቱ አንድ አዳም ነው። ዝቅ ሲልም አንድ ኖኅ ነው። ስለዚህ በቋንቋ፣ በብሔር ወዘተ ዘረኝነት ሊኖረን አይገባም። ዘረኝነትን ከአእምሯችን እናጽዳ። ሁልጊዜም እግዚአብሔራዊውን ሐሳብ እንያዝ።

፲ኛ) ስሜታችንን የምንገዛ እንሁን እንጂ ስሜት የሚገዛን አንሁን። ትሑት ሰብእና፣ ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ እግዚአብሔር አይለየን።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
2.3K views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 17:50:39
#በጎ #ሰው
በእርግጥ ክፉና በጎውን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው። በእኔ ሚጢጢ እውቀት በራሴ መስፈርት የዓመቱ በጎ ሰው "ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ" ናቸው። ንግግራቸው እርጋታቸው አስታራቂነታቸው ሁሉ ነገራቸው ልዩ ናቸው። እንግዲህ እግዚአብሔር እስከመጨረሻው እድሜያቸው በመልካም ሥራ ያቆይልን።
1.2K views14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 18:18:02 አማራም የትውልድ ቦታየ ነው። "ከተኳሾቹም አሉ በልዩ መሐል አገዳ የሚለያዩ የተባሉ ወፍ አርግፍ ጀግኖች አሉበት። አሁንም በሁሉም ግንባር ወንድሞቼ እየተዋጉ ነው። በጦሩ የሞቱ ወንድሞቼ አሉ። ብዙ የገደሉ ወንድሞቼም አሉ። እኔም ወደ ግንባር ያልሄድኩ የቤተክህነት ሰው ስለሆንኩ ነው። ትግራይም ብንሄድ የራስ አሉላ ልጆች ጀግና ተዋጊዎች ናቸው። ይህንን ባለፉት ጊዜያት አይተናል። ትግራይ ጀግኖችም ምሁራንም ቅዱሳንም የሚፈልቁባት ናት ። ግን እኒህ ጀግኖች የእኛም የእነርሱም አንድ ሆነው ለኢትዮጵያ ቢቆሙ ይበልጠናል። ኦሮምያም፣ ደቡብም፣ ሌላውም ክልል ጀግና ተዋጊዎች አሉ ነበሩ። ስለዚህ በስሑት ፖለቲካ ከምንተላለቅ እርቁ ይሻላል።
----------የድሃ ልጅ ለምን ያልቃል?--------
"ብዙ የድሃ ልጅ በጦርነቱ ካለቀ በኋላ፣ ብዙ መሠረተ ልማቶች በጦርነት ከወደሙ በኋላ መጨረሻ በእርቅ ይደመደማል" ። ሰላምን ስታወራ አሁን ላይ ሰው አይወድም። የትግራይ ሕዝብ እየተጎዳብን ነው ተው ስንል "ወያኔ" ናችሁ እንባላለን። እንደገና ወያኔ ጦሯን ሰብስባ አማራ ክልልን ስትወር እረ ተው ሰላም ይሻላል ስንል "ብልጽግና" ናችሁ ይሉናል። በነገራችን ላይ በጦርነት የሚፈታ ምንም ዓይነት ችግር የለም። ምናልባት በጦር አሸንፈህ የሆነን ቦታ ልትይዝ ትችላለህ። ነገር ግን በሰላም ካልሆነ የያዝከው ቦታ እየቆየ የሚፈነዳ ቦንብ ነው።

የኢትዮጵያ እጅግ ወራዳው ታሪክ በየዘመኑ የምናፍርበት ታሪክ ከ50 ዓመት በፊት ጀምሮ እስካሁን ያለው ታሪክ ነው። ኢትዮጵያ አሸናፊ የምትሆነው እርስ በእርስ የሚናከሱ ልጆቿ ታርቀው በፍቅር ሲኖሩ ነው። እንጂ እኛው ገዳይ እኛው ሟች በሆንበት ታሪክ ጀግናም የለም አሸናፊም የለም። ፖለቲከኞች እውነት ህዝብን ለማገልገል ከሆነ ሥልጣን የያዛችሁት ታርቃችሁ በንግግር ችግሮችን ፍቱልን። በነገራችን ላይ በብልጽግናም በወያኔም መካከል የርእዮተ ዓለም ልዩነት የለም። ሁለቱም ለኢትዮጵያ የሚመጥኑ አይደሉም። እያገዳደለን ያለ የመሬት እና የሥልጣን ጉዳይ ነው። ይህንን ደግሞ መለወጥ የሚቻለው የተሳሳተውን ሕገ መንግሥት በመለወጥ ነው። በነገራችን ላይ የአሁኑን ሕገ መንግሥት የሰራችው ደግሞ ወያኔ ብቻዋን አይደለም። የቀድሞው ብአዴን፣ የቀድሞው ኦህዴድ የአሁኑ ብልጽግናም ጭምር ናቸው።

የኢትዮጵያ መሬት ባለቤትነቱ ለሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቢሆን ኖሮ የመሬት ጠብ አይኖርም ነበር። ነገር ግን በክልል ሸንሽነው የየክልሉን መሬት ባለቤትነቱን ለየክልሉ አደረጉት። በዚህ ምክንያት በአንዷ ኢትዮጵያ ውስጥ አንዱ አሳዳጅ አንዱ ተሳዳጅ ሆነው ይኖራሉ። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ተዘዋውሮ ሰርቶ መኖር የማይችል ሆነ። ኢትዮጵያዊነት ጠፍቶ ክልላዊነት ስለጎለበተ የአንዱ ጉዳት ለሌላው የማይሰማው ሆነ። ይህ የሆነው ደግሞ በሕገ መንግሥቱ ምክንያት ነው። ስለዚህ ከመገዳደሉ በፊት ሕገ መንግሥቱን ቀይሩት። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በፍቅር ይኑር። ሁሉ ለሁሉ እንዲያስብ ሥሩ። ባሕርዳር ዩንቨርስቲ ሲያስመርቅ ወንድሜን ለማስመረቅ ሄጄ ነበር። እና ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በቪድዮ ኮል የሰጡት አስተያየት ድንቅ ነበር። በጦርነቱ ማንም አትራፊ አይሆንም። እርቁ ይሻለናል። እባካችሁ ታረቁ ነበር ያሉት። አለበለዚያ ግን ከሁለቱም ወገን እሳት የላሰ እሳት የላሰ ጀግና ስላለ ትርፉ መተላለቅ እንጂ መሸናነፍ አይኖርም። ትልልቅ ባለስልጣን ሰዎች ይህን እንደምታነቡት አውቃለሁ። እስኪ በእናንተ ምክንያት እየሞተ ያለውን ሕዝብ ታርቃችሁ እረፍት ስጡት።

ነጻ ውይይት ነው በሐሳብ መከራከር መሟገት ይቻላል ኑ።
1.3K views15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 12:35:05
#ውለዱ #ምድርንም #ሙሏት
አንዳንዱ ሰው እኛን የሚያኖረን ልጅንም የሚያሳድግ እግዚአብሔር መሆኑን ረስቶ ወልጄ ማሳደግ ከሚያቅተኝ እንዳልወልድ የወሊድ መቆጣጠሪያ ልጠቀም ብሎ ከፈጣሪ ጋር ይጣላል። የወሊድ መቆጣጠሪያ በክርስትና ትልቅ ኃጢኣት ነው። ፈጽሞ አይፈቀድም። ሰው መጨነቅ የሚጀምረው ከእግዚአብሔር በላይ ካላሰብኩ ሲል ነው። ክርስቲያን አንድን ነገር ለማድረግ የራሱን ድርሻ ይወጣል። ከዚያ ሲያገኝ ፈጣሪውን ያመሰግናል። ሲያጣም ለበጎ ነው ብሎ ፈጣሪውን ያመሰግናል። ፈጣሪን በንጽሕና ሆነን እናምልከው። በደላችንንም ይቅር እንዲለን ንሥሓ እየገባን ሥጋውን ደሙን እንቀበል።

ማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ ሰርቆ ሳይሆን ወጥሮ ሰርቶ ይብላ። በየሙያው ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ከፈጣሪ የማያጣላ ሙያ ከሆነ በደስታ በወኔ በፍቅር ሥሩ። ስንፍና የኃጢኣት መሠረት ስለሆነ አትስነፉ። በየተሰማራችሁበት ጎበዞች ጀግኖች ሁኑ።
1.9K views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:40:43
ታላቁ ሊቅ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ በአንድ መወድስ ቅኔያቸው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እረኝነት ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ። ክፉ እረኛ የበጎቹን ሥጋና ጸጉር ብቻ ይፈልጋል። በጎቹን ግን ወደለመለመ መስክ አያሰማራም። በእኛ በሰዎች ልማድ መልካም እረኛ የሚባለው በጎቹን ተንከባክቦ ወደለመለመ መስክ የሚያሰማራ ነው። ነገር ግን እንዲህ አድርጎ ቢንከባከባቸውም መጨረሻ ላይ አርዶ ይበላቸዋል። ወይም አርዶ ለሚበላ ይሸጣቸዋል። ኢየሱስ ክርስቶስን እረኛችን ጠባቂያችን ስንለው ግን ስንደክም ስንታመም እንፈወስ ዘንድ ሥጋውን ቆርሶ እንኩ ብሉ ደሙን አፍስሶ እንኩ ጠጡ የሚል ነው። ስለዚህ ቸር እረኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ፍቅሩን ሁልጊዜም እናስበው። ሁልጊዜም ንሥሓ እየገባን ሕይወት የሚሆነንን ፈውስ የሚሆነንን ሥጋውን ደሙን እንቀበል።

"በለኒ መሐርኩከ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም።
እስመ አልቦ ዘእንበሌከ ዘይሜህር ቃለ መድኃኔዓለም"።
1.4K viewsedited  14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:24:38
ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት።
ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት።
ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ሙሽራ ናት።
ቤተክርስቲያን አንዲት ናት።

የሰው ተከታይ ከምንሆን የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ እንወቅ። የቤተክርስቲያን ትምህርት ፍጻሜው ሕይወት ነው። ለዘላለማዊ የደስታ ሕይወት ዋናው እርሱ ነው። ክርስትናን በወሬ ብቻ ሳይሆን በተግባርም እንኑረው።
247 views20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:32:16 #እይውልህ #ወንድማለም
ለቤተክርስቲያን አሳቢ አንተ ብቻ እንደሆንክ አታስብ። ቤተክርስቲያን ራሷ ክርስቶስ ነው። መላእክት ጠባቂዎቿ ናቸው። እልፍ አእላፋት ሊቃውንት በጸሎትም በትምህርትም ሲጠብቋት ኖረዋል። እየጠበቋትም ነው። ሲጠብቋትም ይኖራሉ። አንተን እንደተቆርቋሪ ቆጥረህ ጳጳሳትን፣ መምህራንን፣ አስተዳዳሪዎችን፣ መነኮሳትን፣ ምእመናንን እንደማያስቡ አድርገህ አታቅርብ። በምሥጢርም በጽሑፍም በትምህርትም እየደከሙ ያሉ ብዙ ሊቃውንት ነበሩን። አሉን። ይኖሩናል።

በእርግጥ በየዘመኑ ክፉ ካህናት፣ ክፉ ጳጳሳት፣ ክፉ መምህራን ቤተክርስቲያንን ፈትነዋታል። አሁንም እየፈተኗት ያሉ ካሉ ሙሉ መረጃ ማስረጃ ይዞ ማስወገዝ ይቻላል። በመሰለኝና በሐሜት መኖር አይገባም። ታድያ የእኔ ድርሻ ምን ይሁን ካልከኝ ለጥፋቶች መንሥኤ እገሌ ነው እገሌ ነው እያልክ ጣትህን ከምትቀስርና ከማሳበብ የራስህን መንፈሳዊ ድርሻ ተወጣ። ሁሉም የድርሻውን ነው የሚጠየቅ። ድርሻህ ላይ ትኩረት አድርግ። እንዲሁም ከሊቃውንቱ ከምእመናን ከመንፈሳዊ ማኅበራቱ ጋር እየተናበብክ ችግሮችን ለመፍታት ጣር።

ክብር ለተርእዮ ለገንዘብ ለዝና ሳይሆን የቤተክርስቲያንን ክብር ለመግለጥ ለኖሩ እና እየኖሩ ላሉ ሊቃውንት እንዲሁም ምእመናን ይሁን።

ሰላም ለክሙ አፍላገ ወንጌሉ (ማኅበራኒሁ) ለክርስቶስ ሰላም ለክሙ። ወትረ ሐውጽዋ ወትረ ሐውጽዋ ለቤተክርስቲያን።
523 views19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:45:47 #ሃይማኖተ #አበው #ክፍል #ስድስት
--------ዘጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት-------
+
=> ምዕራፍ ፲፫:- ጎርጎርዮስ ማለት ንቁ የተጠበቀ /ዕቁብ ንቁሕ ማለት ነው።
=> ጎርጎርዮስ ብዙ ተአምራትን ያደርግ ስለነበረ ገባሬ መንክራት ተብሏል።
=> ቦርፎሪኮን የሚባለው ነቢያት ከእግዚአብሔር የሰሙት ዝርው ቃል ነው። አአትሪኮን የእኛ የሰዎች ቃል ሲሆን ዝርው ነው። አተርጋዎን የሚባለው ቃልም ዝርው ቃል ነው። (ወልድን ቃል ስንለው ግን አካላዊ ቃል መሆኑን መረዳት አለብን። ክርስቶስ ራሱ አካላዊ ቃል ነው። ክርስቶስ ለሐዋርያት ሲያስተምራቸው ከአንደበቱ ይወጣው የነበረው ቃል ግን ዝርው ቃል ነው። ይኽውም ከቦርፎሪኮን ጋር ይመሳሰላል)።
+
=> የወልድ ከአብ የተወለደው ልደቱ አይፈጸምም። (ይህም ማለት ሁልጊዜ ሲወለድ ይኖራል ማለት አይደለም። ወልድ ወልድ ሲባል ይኖራል ማለት ነው። አያልቅም ማለቱ እናት ልጇን ስትወልድ ከማኅጸኗ የነበረው ይወጣል። ወልድ ከአብ ተወለደ ስንል ግን በዘመን ሳይቀድም ከህልውናውም ሳይለይ ስለሆነ ተመትሮ የለበትም ለማለት ነው)።
=> ለአንድ ሰው ልብ ቃል እስትንፋስ እንዳለው ሥላሴም በአንድ ልብ አስበው በአንድ ቃል ተናግረው በአንድ እስትንፋስ ሕያዋን ሆነው ይኖራሉ።
=> ሥላሴ በአካል ሦስት በመለኮት አንድ ናቸው።
=> ክርስቶስ ከሁለት አንድ የሆነ ነው።
=> የወልድ ከአብ መወለድ እንዴት እንደሆነ አይመረመርም። ይኽውም ከሰው መረዳት በላይ ስለሆነ ነው።
=> ምዕራፍ ፲፬:- በባህርይው የማይታይ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በሥጋ ታየ። ይኽም ሲሆን በመለኮቱ ፍጹም ነው። እግዚአብሔር እኛን ለማዳን እግዚአብሔርነቱን ሳይለቅ ሰው ሆነ።
+
---------ዘጎርጎርዮስ ዘአርማንያ--------
ምዕራፍ ፲፭:- ይህ ጎርጎርዮስ ሰማዕት ዘእንበለ ደም እየተባለ ይጠራል። የአርማንያው ንጉሥ ድርጣድስ በሃይማኖት ምሰለኝ ቢለው ጎርጎርዮስ ሃይማኖቴን አለቅም በማለቱ ከአዘቅተ ኩስሕ (ሽንት ቤት) አስጥሎታል። በዚያም ሲጣል ያየች ሴት ምግቡን በገመድ አስራ እያላከችለት ፲፭ ዓመት ኖረ። በኋላ ንጉሡ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ ብሎ ቅድስቲቱ ደግሞ እምቢ ብትለው አስገደላት። ከዚያ በኋላ መልኳን እያሰበ አእምሮውን ነስቶት እያለ ለአደን እንደሄደ እሪያ ሆኖ ቀረ። ደግ እህት ነበረችው ማን ባዳነልኝ ስትል መልአክ መጥቶ ጎርጎርዮስ ነው የሚያድንልሽ አላት። እርሷም ጎርጎርዮስማ የዛሬ ፲፭ ዓመት ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ ሞቶ የለምን አለች። እንዳልሞተ ነገራት። ከጉድጓዱ ሄዳ አስወጣችው። መልኩ ከሰል መስሎ ወጣ። ድርጣድስንም አሳምኖ አስጠምቆታል። ንጉሡም ጎርጎርዮስን ኤጲስ ቆጶስነት እንዲሾም አመልክቶ ማመልከቻው ተቀባይነት አግኝቷል።
=> ኢየሱስ ክርስቶስ ያለወንድ ዘር ከድንግል ማርያም ተወለደ።
=> እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሲሆን መለኮትነቱ ወደ ሰውነት አልተለወጠም። ሥጋን ስለተዋሐደም ሕጸጽ አላገኘውም።
=> ጣዖት ቀርጸው ያመልኩ ለነበሩት (የጣዖትን ከንቱነት አሳይቶ) ለጌትነቱ ሥራ ይገዙ ዘንድ (እነርሱ በሚያስቡትና ሊያዩት በሚፈልጉት) በሰው ባሕርይ ተገኘ።
916 views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 23:23:00
ለዓለም ምስቅልቅል ቤተክርስትያን ተጠያቂ አትሆንም። ቤተክርስቲያን ሰላምን፣ አንድነትን፣ ፍቅርን፣ ይቅርታን ከዓመት እስከ ዓመት ታስተምራለችና። ጥሪዋን ትምህርቷን አልሰማም ብሎ ብዙ ችግር ካደረሰ በኋላ ቤተክርስቲያንን ተጠያቂ ማድረግ ነውር ነው። ለዓለም ምስቅልቅል ዋና ተጠያቂዎች ስግብግብ እና ራስ ወዳድ እንዲሁም ዘረኛ ሰዎች ናቸው። ቤተክርስቲያንን እንሰማለን መፍትሄውን ትስጠን የሚል ካለ ግን መፍትሄው በእጇ ነው። ነገር ግን እስራኤላውያን መድኃኒታቸውን እንዳሳደዱት የእኛም ሀገር አንዳንድ ፖለቲከኞች መድኃኒታቸውን ቅድስት ቤተክርስቲያንን አሳደዷት። ልጅ ቢሮጥ አባቱን አይቀድምምና ብዙ ጥፋት ከደረሰ በኋላም የመጨረሻው መቋጫ ያለው እና ሰላም ይሁን፣ አንድ እንሁን፣ ይቅርታ እንባባል የሚለው የቤተክርስቲያኒቱ ትምህርት ነው። እንግዲህ ከአቅማችን በላይ የሆነውን ጉዳይ እግዚአብሔር ይፍታው ብለን ዝም ብለናል። በደላችንን ሳያስብ የኢትዮጵያን ሰላም ያቅርብልን። አንድነታችንን ይመልስልን። እስኪ የቤተክርስቲያንን ትምህርት ተቀብለን ተግባራዊ እናድርገው። እንግዲህ ከቤተክርስቲያን ትምህርት ውጭ ሄጄ መፍትሄ አመጣለሁ። ያዋጣኛል ካልክ ሞክር። ነገር ግን ጊዜያዊ ማስታገሻ መሳይ ወይም ጉዳት እንጂ ምንም ዘላቂ መፍትሄ ወይም ውጤት እንደማታመጣ ስነግርህ በእርግጠኝነት ነው።
2.0K views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ