Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-21 13:06:23
መበሻሸቁን ተውትና
ዶሮ ግን ስንት ገባ?!

ወንጌሉ ሲያልቅብን ኩሽና ለኩሽና መሄዱ ጥሩ ነወይ?
2.0K views10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 11:13:14 አንድ ጊዜ ጅማ ዩንቨርስቲ ዋናው ግቢ ጉባኤ ግእዝ ቋንቋ ስንማር የተፈተናት ፈተና ትዝ አለችኝ። ፈተናው
"ብየ አክሊል ዲበ ርእስየ
መዓልተ እውዕል ታኅተ ሰብእ
ወሶበ በጽሐ ጊዜሁ ለምሴት አኀድር ላዕለ ሰብእ
መኑ አነ"
የሚል ነበር። "በራሴ ላይ አክሊል አለኝ፣ ቀን ቀን ከሰው በታች እውላለሁ፣ በምሽት ጊዜ ደግሞ ከሰው በላይ አድራለሁ። እኔ ማን ነኝ" የሚል እንቆቅልሽ ተጠይቆ። አንዱ ጓደኛችን ሲመልስ "ሱሪ" ነው አለ። ገረመንና አክሊሉ ምንድን ነዋ? ስንለው "ቀበቶው ነዋ" ብሎን አረፈ። ነገር ግን መልሱ አውራ ዶሮ ነበር። ዶሮ ቆጥ ላይ ስለሚያድር ማታ ከሰው በላይ ያድራል።

በይሁዳ ራስ ስለዞረው ዶሮ የሚናገር እና በጸሎተ ኃሙስ ስለታረደው ዶሮ የሚናገር መጽሐፍ መጽሐፈ ዶርሆ የሚባል አለ። ነገር ግን ያንን ሳነበው ፲፪ቱ ብልት የ፲፪ቱ ሐዋርያት ምሳሌ የሚል አላገኘሁም። ብቻ ያው ዶሮ ወጥ በፍስክ ሲበሉት ደስ ይላል። እንቁላልም ገንቢ ምግብ እንደሆነ ሐኪሞች ይነግሩናል። ከዚህ ውጭ የማውቀው ነገር እንደሌለኝ ስነግራችሁ በደስታ ነው።

መጋቤ ዶርሆ ወእንቁላል በትርሽ
2.2K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 10:45:45 የመዓርግ ስም ግን በሙያ ቢሆን ምን አለበት? በዚህ አያያዛችን በቅርብ አንዱ
"ሊቀ ሊቃነ ሊቃውንት"
መባሉ የሚቀር አይመስለኝም።
2.1K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 10:33:59
ኔትዎርክ ዝግ ስለሆነ ማታ ማታ በቴሌግራም ላይቭ የምንማማረውን ትምህርት ለመማር አልቻልንም። ስለዚህ ኔትዎርኩ እስኪከፈት ድረስ ጽሑፉን ብቻ በፌስቡክ ገጼና በቴሌግራም ቻናሌ እለቀዋለሁ። ከዚያ ይከታተሉ። ይጠይቁ። ይህንንኳ የጻፍኩት ዋይፋይ ቤት ገብቼ እንደሆነ ይታወቅልኝ።
የfacebook ገጼ https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://www.youtube.com/@edenawizechristos ነው።

የቴሌግራም ቻናሌ ደግሞ https://t.me/betremariyamabebaw ነው።
2.2K viewsedited  07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 07:18:55 ተግሣጽ & ስድብ
ንድ ወቅት በአንድ ቤት ብዙ ሰዎች ተኝተው ሳለ አንዱ ፈርቶ ሌሎች የተኙ ሰዎች ሳይሰሙ ከዚያው ከቤት ይጸዳዳል። በኋላ ሲያስበው ሰው ሊስቅበት ነው። ከዚያ ሰገራውን በእጁ ይዞ የሁሉንም ልብስ እንደተኙ ይቀባዋል። እርሱም እጁን አባብሶ መልሶ ይተኛል። እነዚያ የተኙት ሰዎች በኋላ ነቅተው ወደ ውጭ ወጣ ብለው ሳሉ ልብሳቸውን ቢያዩት ሰገራ በሰገራ ሆኗል። ሰው እንዳይስቅብን ብለው እነርሱ እንዳላደረጉት እያወቁ ጠፍተው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ ይባላል። ያ አራም ግን በሰላም ከቤት ተኝቶ አደረ ይባላል።

አሁን እየሆነ ያለው ነገር ይህን ይመስላል። አራሞች በሰላም እየኖሩ ንጹሓን የሚሸማቀቁበት ክፉ ዘመን ነው። ነውረኞች ተወደው በሰላም እየኖሩ ነውረኞች ነውራቸውን የቀቧቸው ንጹሓን ሰዎች እየተሰደቡ ይኖራሉ። ምሁራን ዝም ብለው ተሳዳቢዎች ተናጋሪ የሆኑበት ዘመን ነው። ስድብና ተግሣጽ ይለያያል። ገሠጸ ተቆጣ፣ መታ፣ ደበደበ፣ አስተማረ ከሚለው የግእዝ ቃል ተግሣጽ የሚል ባዕድ ዘር ይወጣል። ትርጉሙ ቁጣ፣ ትምህርት ማለት ነው። መምህር ወመገሥጽ ዘኢያደሉ ለገጽ በሚልበት ጊዜ መገሥጽ የሚያስተምር ተብሎ ይተረጎማል እንጂ የሚሳደብ ተብሎ አይተረጎምም። ስድብ ጸዐለ ሰደበ ከሚለው የግእዝ ቃል የሚወጣ ሲሆን "ጽዕለት" መስደብ፣ መሰደብ ስድብ ይላል። ለምሳሌ ሕፃናትን መገሠጽ ይገባል ሲባል ትምህርት ሲገድፉ እና አልማር ሲሉ መቆጣት ይገባል ማለት ነው። እየቀጡ እየመቱ ማረም ይገባል ማለት ነው። ስንማታ ግን ሕይወታቸው እንዳያልፍብን ባለፈው በፍትሐ ነገሥት እንደተማርነው የምንማታበትን ኃይል በራሳችን ጉልበት ፈትነን አማትበን ሊሆን ይገባል። የሞት ብዙ ምክንያት አለውና ተብሎ ተገልጿል።

የተግሣጽ ትርጓሜ ይህ ነው። ከዚያ ውጭ ጥርግርግ እያደረጉ እየተሳደቡ ያሉ ሰዎችን መምህር ወመገሥጽ ማለት ትልቅ ነውር ነው። ንስሓ እንዳይገቡም መሰናክል መሆን ነው። እየተሳደበ የሚያስተምር ሰው መምህር ወመገሥጽ ሳይሆን መምህር ወመጽዕል ነው የሚባለው። ለቤተክርስቲያን ትልቅ ሸክም እየሆኑ ያሉት እነዚህ ናቸው። እናርማለን ይላሉ። ነገር ግን እነርሱ ተሳስተው ስታርማቸው ተሳዳቢ መንጋቸውን ይለቁብሃል። ደግሞ መንጋን መፍራት ተገቢ አይደለም። ማንኛውም መምህር በቀዳሚነት ሊፈራው የሚገባው እግዚአብሔርን ነው። ሁሉም ሰው በእግዚአብሔር ዳኝነት በመላእክትና በሰው ሁሉ ፊት ይቀርባል። ይህንን ነው ማሰብ። በክፉዎች መሰደብ ለመምህራን ክብር ነው። ከታገሡት ሐዋርያዊ ክብርን ያሰጣቸዋልና።

ስለዚህ ተሳዳቢነትን እንተው። ተምረን እናስተምር። ሳይማሩ ማስተማር ጥፋት ይኖረዋልና። ከተሳሳትን ይቅርታ እንጠይቅ። ሰው አምላኪ አንሁን። የሰውን መልካምነቱን ብቻ እንውሰድ። ክፉ ነገሩን አብነት ማድረግ አይገባም።

በትረማርያም አበባው
555 viewsedited  04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 06:02:17 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፳__
አንቀጽ ፳፰ ስለውሰት ይናገራል።
፩) ውሰት በታወቀ ዕለት በታወቀ ቦታ ዋጋ ሳይሰጡ ወይም ሳይቀበሉ ጥቅም የሚገኝበትን ገንዘብ መዋስ ነው። አንድም ማዋስ ነው።
_
፪) እስከዚህ ቦታ ብሎ ከብት የተዋሰ ሰው ቢኖርና ከቦታው አልፎ ሄዶ ከብቱ ቢሞት መክፈል ይገባዋል። ቦታውን አልፎ ሳይሄድ ነገር ግን በራሱ ቸልተኝነት ከሞተበትም መክፈል ይገባዋል። ከገደል አፋፍ ሆና ስትበላ አይቶ ዝም ቢልና ብትሞትም ይከፍላል። ጌታው አብሮ ካለ ግን አይከፍልም።
_
፫) በዋጋ የተዋሰ ከብት ቢኖርና ቢጠፋ የተዋሰው ዋጋውን ይከፍላል። ከተወሰነው ቦታ አልፎ የሄደ ቢሆን ላዋሰው ሰው አልፎ የሄደበትን ጨምሮ ይስጥ።
_
፬) ያዋሰ ሰው በወደደው ጊዜ መልስልኝ ማለት ይገባዋል። የተዋሰ ሰውም እንዲሁ በወደደው ጊዜ መመለስ ይገባዋል።

አንቀጽ ፳፱
ይህ አንቀጽ ስለ አደራ ይናገራል።
፩) አደራ ጠባቂ ለአስጠባቂ የሚሰጣት ገንዘብ ናት። ይህችውም አስጠባቂ ከጠባቂ ዘንድ አምኖ የሚያኖራት ገንዘብ ናት። የተቀበላትም ሰው እንደገንዘቡ አድርጎ በፍጹም ትጋት መጠበቅ ይገባዋል። ተግቶ እየጠበቃት ብትጠፋ ዕዳ የለበትም።
_
፪) አደራ አስጠባቂው ብዙ ዘመን ኖሮ ቢጠፋ አደራ ጠባቂው ለአደራ አስጠባቂው ወራሾች አደራውን ይስጥ። ወራሾች ባይኖሩት ለመሥዋዕት ይሁን።
_
፫) የሰው አደራ የተቀበለ ሰው ለእገሌ ስጥልኝ ቢለው ስጥልኝ ላለው መስጠት ይገባዋል።
_
፬) አደራ ጠብቆ መመለስ ለለመደ ነው እንጂ ላልለመደ መስጠት አይገባም። አደራ ያኖሩበት ሰው ቢሞት አደራ ይቀራል።
_
፭) አደራ የተቀበለ ሰው ጠባቂ አስጠባቂ በኃይል ሰርቆ ቀምቶ እንዳመጣው እያወቀ አደራ ቢያኖር እጥፍ ሊያስከፍሉት ይገባል። የሌባ ዋሻ የቀማኛ ጋሻ ሆኗልና።

አንቀጽ ፴
ይህ አንቀጽ ስለሹመት ይናገራል።
፩) ግብሩን ጠባዩን ያሳመረ ሰው፣ የሹመትን ሥርዓቷን ያወቀ የጠነቀቀ መሾም ይገባዋል። ለጌታው ገንዘብ ከፍሎ ይሾማል።
_
፪) የጌታው ገንዘብ ያለተንኮል ያለስንፍና በሹሙ እጅ ቢጠፋ መክፈል አይገባውም።
_
፫) ሿሚና ተሿሚው ምስክር የሌለው ጠብ ቢጣሉ ሿሚው ምሎ በተናገረው ይሁን። በገንዘቡ አምኖ ሹሞታልና።
_
፬) ሹም በተሾመበት ገንዘብ እንደራሴ መሾም አይገባውም። ጌታው ሹም ብሎ ቢፈቅድለት ነው እንጂ።
_
አንቀጽ ፴፪
ይህም የሹመትን ነገር ይናገራል። ከአንቀጽ ፴ የሚለየው ይህ አንቀጽ ፴፪ የሐፃኒ የመጋቢ ነው። አንቀጽ ፴ የቤተ መንግሥት ነው።
፩) ለሽማግሌ፣ ለሕፃን፣ ለእብድ፣ ለታማሚ ጽኑ ሹም ሊሾሙላቸው ይገባል።
_
፪) አገልጋይ በጌታው ትእዛዝ ማዘዝ መሠልጠን ይገባዋል። ተሿሚዎች ገንዘብ ቢያጠፉ መክፈል ይገባቸዋል። [ሐተታ:- ጥንቱን መሾማቸው ሊጠብቁ ነውና]።
_
አንቀጽ ፴፩
ይህ አንቀጽ አገልጋይ ስለመግዛትና አገልጋይን ነጻ ስለማውጣት ይናገራል።
፩) ሰው ሁሉ ከአንድ ከአዳም በመገኘት ባለመገዛት አንድ ነው። ነገር ግን ጦርነትና ሌሎችም ምክንያቶች አንዱ ለአንዱ ይገዛ ዘንድ መገዛትን ታመጣባቸዋለች። ድል የተነሡት ድል ለነሡት እንዲገዙ ታደርጋለች
_
፪) አማኒ አገልጋይን ላላመነ ሰው መሸጥ አይገባም። የአገልጋይ ልጆች ለጌታቸው ይገዙ። አንድም ለአባታቸው ጌታ ይገዙ።
_
፫) አገልጋይን ነፃ ማውጣት ከትሩፋት ሥራ ወገን ናት። አገልጋይን ሁሉ ነጻ ማውጣት ይገባል።
_
፬) አገልጋይ በሚከተሉት ምክንያቶች ነጻ ሊወጣ ይችላል።
√ ከጌታው ዘመድ አንዱ ቀድሞ ገዝቶት ከነበረ፣
√ ጌታው ክርስትና ቢያነሣው፣
√ በጌታው ፈቃድ ክህነት ከተሾመ፣ ከመነኮሰ
√ ጌታው ፈቅዶ ባርያው ዘማች ከሆነ/ከዘመተ
√ ጌታውን ከሞት ቢያድነው (ተዋግቶ/መክሮ)
√ ጌታው ቢሞት
√ አገልጋዩ በጠላቱ እጅ ከተያዘ በኋላ ከድቶ ወደ ጌታው ቢመለስ ነጻ መውጣት ይገባዋል።
_
፭) ነጻ የወጣች አገልጋይ ነጻ ያልወጣውን አገልጋይ ማግባት አይገባትም።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፳፩ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
683 views03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 12:34:00 በቀድሞ ዘመን የላይ ቤትና የታች ቤት መተርጉማን በምሳሌ ምክንያት አይግባቡም ነበር ይባላል። ወንጌላውያን ለምን አራት ሆኑ ለሚለው ሐተታ ሲሰጡ አራት ወቅት፣ አራት ኪሩቤል፣ አራት ባሕርያት____ እያሉ ከሰጡ በኋላ አራትነት ያለውን ነገር ሁሉ ካልመሰልን ይላሉ። ይህን የተመለከተ አንድ ሊቅ ወደ ቤቱ ሲገባ ከግርግሙ ላይ አራት አሞሌ ጨው ተሰቅሎ ያያል። እና ሚስቱን ጠርቶ "እኒያ ሰዎች የአራቱ ወንጌላውያን ምሳሌ እንዳያደርጉት ደብቂው" አሉ ይባላል። ምሳሌ ሲሰጥ መጽሐፍን ሳይለቁ ነው። እንጂ ጥቂት መመሳሰል ያለውን ነገር ሁሉ ምሳሌ ካላደረግነው አይባልም።

ሊቃውንት አባቶቻችን ምሥጢረ ሥላሴን በፀሐይ ሲመስሉ በውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ የሚለውን የመዝሙረ ዳዊት ክፍል አብነት አድርገው ነው። ጽላሎት የአካል ምሳሌ ነውና። ሰውን የምሥጢረ ሥጋዌ ምሳሌ ያደረጉት ንግበር ሰብአ በአርአያነ ወበአምሳሊነ የሚለውን የኦሪት ዘልደት ቃል መሠረት አድርገው ነው። አርአያ በቁሙ ምሳሌ ነውና። ምሥጢረ ሥላሴን በእሳት ሲመስሉት በቀሌምንጦስ አቡየ እሳት ወአነ ብርሃኑ ወመንፈስቅዱስ ዋዕዩ የሚለውን ኃይለ ቃል መሠረት አድርገው ነው። ምሳሌያትን ሁሉ ብንመለከት መጽሐፋዊ መሠረት ያላቸው ናቸው። ስለዚህ ከአበው ትምህርት፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረትነት ባንወጣ መልካም ነው።

አንዱ ምሳሌ ለሁለት ተቃራኒ ነገሮች የሚመሰልበት ወቅትም አለ። ምሳሌ ኮከብ የቅዱሳን ምሳሌም ይሆናል። ለአብርሃም አበዝኆ ለዘርዕከ ከመ ኮከበ ሰማይ ወከመ ኆፃ ዘድንጋገ ባሕር ሲል ኮከብ የቅዱሳን ኆፃ የኀጥአን ምሳሌ ሆኗል። ሲታተትም ኮከብ ብሩህ እንዲሆነ ጻድቃንም ብሩሃነ አእምሮ ናቸውና ይላል። የሰይጣን ምሳሌም ሆኗል። እፎ ወድቀ ኮከበ ጽባሕ ሲል ኮከበ ጽባሕ ያለው ሰይጣንን ነው። ለሁሉም ግን መጽሐፋዊ መሠረት አለው። መቼም ሁሉም ምሳሌ ዘየኀፅፅ ነው በማለት ሁሉን ለሁሉ ምሳሌ ላድርግህ ማለት አይገባም። ሕፀፁ እንዳይጎላብን መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

መ/ር በትረማርያም አበባው
2.1K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 07:03:43 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፱_
አንቀጽ ፳፮ ስለ ስጦታ ይናገራል።
፩) ገንዘብ ላለው፣ ለባለጸጋ የሚሰጡት ስጦታ ሀብት ይባላል። ገንዘብ ለሌለው ለድሃ የሚሰጡት ስጦታ ምጽዋት ይባላል።
_
፪) ሀብት የትሩፋት ሥራ ናት። ስጦታ ነውር ቢገኝበት ይመለሳል። ምጽዋት ግን አይመለስም።
_
፫) ስጦታ የተቀበለ ሰው ስጦታውን ከተቀበለ በኋላ በስጦታው ማዘዝ መሰልጠን ይገባዋል።
_
፬) ስጦታ የሚሰጥ ሰው አካለ መጠን ያደረሰ፣ አዋቂ፣ ራሱን የቻለ ደልዳላ ካልሆነ ስጦታው አይጸናም።
_
፭) ስጦታን ሰጪው መልሱልኝ ካለ ሊመለስ ይችላል።
_
፮) ስጦታ ለባዕድ ከሆነ በደብዳቤ፣ ለዘመድ ከሆነ በቃል ያለ ደብዳቤ ትጸናለች።
_
፯) ገንዘብ ላለው ነው እንጂ ገንዘብ ለሌለው ሰው የሰጡት ስጦታ አይጸናም።
_
፰) አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ስጦታ ቢሰጥና በኋላ ቢወልድ እንደገና ያንን ስጦታ ለልጁ መስጠት ቢፈልግ ቀድሞ ከሰጠው ተቀብሎ ለልጁ ይስጠው።
_
፱) ሰጭ ልቡናው ድል የሚነሳበትን ገንዘብ መስጠት አይገባውም። በስጦታው እንዳይጸጸት።
_
አንቀጽ ፳፯
ይህ አንቀጽ ስለ ብድር ይናገራል።
፩) ብድር ከምጽዋት ወገን ናት። [በረኃብ ዘመን በዓይነታው ማበደር ከምጽዋት ቁጥር ነውና]
_
፪) ከአንተ ሊበደር የወደደውን አትከልክለው። ተበዳሪም ብድሩን ለመክፈል ማሰብ መትጋት ይገባዋል።
_
፫) የሚከፍለውን እስኪያገኝ ድረስ አበዳሪ ተበዳሪን መታገሥ ይገባል።
_
፬) በመያዣ፣ በገንዘብ ዋስ፣ በእጅ ዋስ፣ በደብዳቤ ማበደርና መበደር ይገባል። ደብዳቤው ሲጻፍ ምስክሮች ሊኖሩ ይገባል።
_
፭) ብድርን በቀነ ቀጠሮው መመለስ ይገባል። ተበዳሪ ባላገኝ መያዣውን አስቀር ያለ ቢሆን አበዳሪ መያዣውን መውሰድ ይገባዋል።
_
፮) ተበዳሪ የምከፍለውን ገንዘብ አጣሁ ቢል አበዳሪ ከተበዳሪ ገንዘብ በዳኛ ትእዛዝ ያገኘውን መውሰድ ይገባል።
_
፯) ተበዳሪ በእርሱ ላይ ያለውን ዕዳ ቢክድ፣ ከካደ በኋላ አበዳሪ የያዘው ደብዳቤ ቢመሰክርበት ሙሉውን ይክፈል። ተበዳሪው ክዶ ቢምል፣ ከማለ በኋላ ምስክሮች ቢመሰክሩበት በሐሰት ስለማለ እጥፍ ይክፈል። ከካደ በኋላ ማል ሲሉት ፈርቶ ቢያምን እጥፍ ከመክፈል ይድናል።
_
፰) በመያዣ የሄደ ገንዘብ ቢኖርና ገንዘቡ ቢጠፋ መያዣው ትርፍ ካለው ትርፉን መልሰው ዓይነታውን (ተገምቶ) ይውሰዱ። ብድሩን ከባለዕዳው የተቀበለ አበዳሪ መያዣውን ለባለቤቱ መመለስ ይገባዋል።
_
፱) አበዳሪ ከተበዳሪ የተቀበለውን መያዣውን እንደገንዘቡ አድርጎ ሳይጠብቀው ቀርቶ ቢጠፋና ባይገኝ መሰሉን መክፈል ይገባዋል። በተወሰነ ሥርዓት እስከዚህ ቀን ድረስ ባገኝ ብድርህን እሰጥሀለሁ ባላገኝ መያዣውን ታስቀራለህ ተባብለው ቢሆን ዳኛ ይፍረድ። መያዣው ከብድሩ ጋር እኩል ከሆነ ሁለቱም ነጻ ናቸው። መያዣው ቢበዛ ብድሩ ቢያንስ አበዳሪ በብድር ልክ አስቀርቶ የመያዣውን ትርፍ መመለስ ይገባዋል። ብድሩ ቢበዛ መያዣው ቢያንስ ተበዳሪ ቀኑ ሲደርስ የብድሩን ትርፍ መመለስ ይገባዋል።
_
፲) ሊሸጡት የማይገባውን መያዣ አድርጎ መቀበል አይገባም። ብድሩ ከሚከፈልበት ቀን አስቀድሞ ፈጥኖ ብል የሚበላውን ልብስ ነቀዝ የሚበላውን እህል መያዣ አድርጎ መቀበል አይገባም።
_
፲፩) ከሰው ዘንድ ገንዘብ ያለው ሰው እስከ ሠላሳ ዘመን ስጠኝ ባይለው ከዚያ በኋላ ተመልሶ ስጠኝ ማለት አይገባውም። ማንኛውም ሕጋዊ ጉዳይ ከሠላሳ ዓመት በላይ ከሆነ አይጠየቅም።
_
፲፪) አባት እርሱ አዞት የተበደረ ካልሆነ በልጁ ብድር መያዝ አይገባውም። ልጅም በእናቱ በአባቱ ብድር መያዝ አይገባውም። [ሐተታ:-አባት እርሱ አዞት የገደለ ካልሆነ በልጁ ደም መያዝ አይገባውም።ወንድምም በወንድሙ ደም መያዝ አይገባውም። አብሮ የመከረ የገደለ ቢሆን ነው እንጂ]።
_
፲፫) የእጅ ዋስ (የሰው ዋስ) አድኅኖ ይባላል። የእጅ ዋስ የሆነ ሰው እጁን ማቅረብ ይገባዋል። የእጅ ዋስ ሲዋስ እገሌን ላቀርብ ተውሻለሁ ይበል። ቀን ወስኖ ቢዋስ የተዋሰውን ሰው አቅርብልን ሲሉት ማቅረብ ይገባዋል። ሰውየውን ካቀረበ በኋላ የእጅ ዋስ አይጠየቅም። ሰውየውን ማቅረብ ካልቻለ ግን ይጠየቃል። እርሱ ይከፍላል። የገንዘብ ዋስ ተሐብዮ ይባላል። ገንዘቡ ለታወቀ ይከፍላል ለሚሉት ሰው መዋስ ይገባል። አበዳሪ አስቀድሞ ተበዳሪን ይጠይቀው። ባይከፍለው ሄዶ ዋሱን ይያዝ። ተበዳሪ ሩቅ ሀገር ቢሄድ ለዋሱ ዳኛ ቀን ይስጠው። ዳኛ በሰጠው ቀን ባያገኘው ዋሱ ይክፈል።
_
፲፬) ለዋስ ዋስ የሚሆን ሰው የጠለፋ ዋስ ይባላል። ዋስ ባይገኝ የጠለፋ ዋስ ይያዛል። ካህን አንዱንድንኳ በጭዋ ዳኛ ቁሞ መዋስ ማዋስ፣ መያዣ መያዝ ማስያዝ አይገባውም።
_
፲፭) ሴት የእጅ ዋስ የገንዘብ ዋስ መሆን አይገባትም።
_
፲፮) መያዣ ልብስን መያዝ አይገባም። ተበዳሪው እንዲራቆት መፍረድ አይገባምና።
_
አንቀጽ ፴፰
ይህም አንቀጽ ስለብድር ይናገራል። አንቀጽ ፳፯ የእጅ ብድርን ይናገራል። ይህኛው አንቀጽ ደግሞ ትርፍ የጋራ ስለሆነ ብድር ይናገራል። ባለሀብቱ ገንዘብ ችሎ ንግዱን ሥራውን ደግሞ ተቀጣሪው ይሠራና ትርፉን መካፈል ነው።
፩) ከትርፉ በስፍር በቁጥር በታወቀ ገንዘብ ነው እንጂ ባልታወቀ ገንዘብ መዋዋል አይገባም።
_
፪) በእኩሌታው በተገኘው ትርፍ አንዱ ለራሱ ሥራ ሊሠራበት አይገባም። ባለቤት በወደደው ጊዜ ውሉን ማፍረስ ይገባዋል። ነጋዴም በወደደው ጊዜ ውሉን ማፍረስ ይገባዋል።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፳ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
946 views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 12:14:52 _
፷፩) ጥምቀት የተነሣ ልጅ ያላቸው አባትና እናት በፊት ሁለት ቀን በኋላ ሁለት ቀን ከመገናኘት (ሩካቤ) መከልከል ይገባቸዋል።
_
፷፪) ሩካቤ የሚከለከልባቸው ጊዜያት
√ ሴት በወር አበባዋና በአራስነቷ ጊዜ
√ በጾም ወቅት፣ በሰሙነ ሕማማት
፷፫) በጾም ሩካቤ መከልከሉ ስለጾም የሚሆን ፈቃደ ነፍስ ይፈጸም ዘንድ ነው። ከሰሙነ ሕማማት ውጭ ባሉ አጽዋማት በፍትወት ጾር ድል የተነሣ ሰው ቢኖር የፈቲውን ጾር ማራቅ ይገባዋል። [ሩካቤ ይፈቀዳል። ይህ ግን ላልተቻለው ነው እንጂ ለተቻለውስ ሁሉንም አጽዋማት መታቀብ መልካም ነው]።
_
፷፬) ከሴት ማኅፀን አውጥቶ ከውጭ ዘርዕን መዝራት አይገባም።
_
፷፭) ላለመፀነስ ወይንም የተፀነሰውን ለማስወረድ መድኃኒት መጠቀም አይገባም።
_
፷፮) ሚስቱ እንደሰሰነች የነገሩት ሰው ቢኖርና ድርስ ነገሩን ባያውቅ፣ ድርስ ነገሩን ሊያውቅ ቢወድ ወደ ቤተክርስቲያን ዳኛ ወደ ኤጲስ ቆጶሱ ይውሰዳት። ከታቦቱ ፊት ያቁማት። ካህኑ መንቀል አንስቶ ይያዝ። ከርቤ ይጨምርበት። ከሐመደ ምሥዋዑ ከውሃው ይጨምሩበት። ከዚያ ይህንን በእጁ ይዞ። ክንብንብሽን አውርጂ ይበላት። በእግዚአብሔር ያምላት። ሌላ ሰው አልደረሰብኝም ብትል ባልሽ ከጠረጠረው ነገር የነጻሽ ከሆነ ይህን ውሃ ጠጪ ይበላት። በሐሰት ብትምዪ ግን ይህ የምትጠጪው ውሃ ሥጋሽን ያሳብጠው ይበላት። ሴትዮዋም አሜን አሜን ወአሜን ትበል። በታቦቱ ፊት ሆና ውሃውን ትጠጣ። ንጹሕ ከሆነች ደስ የምትሰኝበትን ልጅ ትወልዳለች።
_
፷፯) ማግባት ርኵስ ነው ብሎ ከጋብቻ የተከለከለ ሰው ኃጥዕ ነውና ከቤተክርስቲያን ይለይ።
_
፷፰) ሴት ልጅ በወር አበባዋ ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን አትግባ። የደሟ ወራት እስኪፈጸም ድረስም አትቁረብ።
_
፷፱) ወንድ የወለደች ሴትም ከወለደች ጀምሮ 40 ቀን ከቤተክርስቲያን ውጭ ትቆይ። ሴት ከወለደች 80 ቀን ትቆይ።
_
፸) [ቁጥር ፱፻፴፮] አዋላጆች ወንድ ካዋለዱ 20 ቀን፣ ሴት ካዋለዱ 40 ቀን እስኪሆናቸው ድረስ ሥጋውን ደሙን አይቀበሉ።
_
፸፩) ባል ያላት ሴት ብትሰስንና ባሏ ባያውቅ ለብቻዋ ንስሓ መቀበል ይገባታል። ባሏ እያወቀ ሊፈታት ባይወድ ግን ሁለቱም ከምእመናን ይለዩ።
_
፸፪) የቄስ ሚስት ባሏ ከሞተ በኋላ ሌላ ብታገባ ንስሓ ይገባታል። በታች መቆም በኋላ መቀበል ይገባታል።
_
፸፫) ጋብቻ በሚከተሉት ነገሮች ይፈርሳል።
√ ባልና ሚስት ተመካክረው ከመነኮሱ
√ አንዱ የአንዱን ፈቃድ አልፈጽምም ቢል
√ አንዱ የአንዱን ሰውነት ሊያጠፋ ቢወድ
√ ባል ከሚስቱ ጋር መገናኘት (ሩካቤ) ካልቻለ
√ ሚስት ከባል ጋር መገናኘት ካልቻለች
(አፈ ማኅፀኗ ጠባብ ሆኖ ለሩካቤ ቢከለክል)
፸፭) ባል ሚስቱን ጋኔን ሲጥላት ቢያገኛት፣ ይህ ሁኔታ ካገባት በኋላ ያገኛት ከሆነ እርሱ መርዳት መታገሥ ይገባዋል። እርሱንም እንዲህ ያለ ነገር ቢያገኘው እርሷ መርዳት መታገሥ ይገባታል። ከማግባቷ በፊትም እያመማት ሳለ ደብቀው ቢያጋቡትና ቆይቶ ቢያውቅ መፍታት ይችላል።
_
፸፮) ከተጋቡ በኋላ ከሁለቱ አንዱን ደዌ ሥጋ ቢይዘው አንዱ ከአንዱ ሊለይ ቢወድ መለያየት አይገባውም። ሊፈታት ቢወድ ግን ትልወቷን ማጫዋን ሁሉ መስጠት ይገባዋል።
_
፸፯) ሰው በእሥራት ሳለ ወይም ባልታወቀ ምክንያት ቢጠፋ ግቢው ይፍረስ አንልም። መፈታትና አለመፈታቱ እስኪታወቅ ድረስ ባልና ሚስት ሆነው ይኑሩ እንጂ።ከአምስት ዓመት በኋላ ግን እንደ ፈቃዳቸው ይሆናል።
_
፸፰) ባል ዘማች ቢሆን እስከ ሁለት ዓመት ሚስቱ ትጠብቀው። ሚስት ስለ ባሏ ህልውና ምንም ዓይነት ዜና ካልሰማች፣ መሞቱንም ከመኳንንት ካልሰማች አታግባ። ሌሎች ሰዎች ሞቷል ብለው ቢናገሩ ለምስክርነት በመካከላቸው ወንጌል ያኑሩና ያምሏቸው። ድርስ ነገሩ ከታወቀ ከዚህ በኋላ ዳዊት እያስደገመች ቁርባን እያስቆረበች አንድ ዓመት ትጠብቅ። ከዚያ በኋላ ማግባት ትችላለች። ምስክሮች በሐሰት ሞቷል ብለው ቢመሰክሩ አሥር ወቄት ወርቅ ይክፈሉ። ሞተ ብለው ያወሩበት ወታደርም ከወደደ ሚስቱን መልሶ ወደ ቤቱ ያግባት።
_
፸፱) ባሏ ሳይፈቅድላት ከሌላ ወንድ ጋር ብትጠጣ፣ ወደ መሸታ ቤት ገብታ ብትስቅ ብትጫወት፣ ከቤቷ ወጥታ ከውጭ ከባዕድ ቤት ብታድር ይፍታት።
_
፹) ሚስት ባሏን ለመግደል ብትሞክር ወይም ሌለች ሊገድሉት እንደሆነ እያወቀች ዝም ካለችው ጋብቻቸው ይፈርሳል።
_
፹፩) ሚስት ያገባ ሰው በእርሱና በሚስቱ መካከል ክፉ ነገር ቢገኝ፣ ከምክንያት ወገን ማናቸውም ምክንያት ቢኖርበት ይታገሣት። ከክፋት ወደ በጎነት እስክትመለስ ድረስ ይምከራት ያስመክራት። መክሯት አስማክሯት ባትመለስ ወደ ደግ ቄስ ይውሰዳት። ቄሱም በመካከላቸው ሆኖ ያስታርቃቸው። ቄሱን አይሆንም ብትለው ኤጲስ ቆጶሱ አብረሽ ኑሪ ብሎ ይፍረድባት። ለኤጲስ ቆጶሱም ባትታዘዝ ባሏን ጥላ ብትሄድ ሁለተኛ አባብሎ ይመልሳት። በእምቢተኝነቷ ከጸናች ባሏ የወደደውን ማድረግ ይገባዋል። ሌላ ሊያገባ ቢወድ ያግባ። በንጽሕና መኖር ከፈለገ ይመንኩስ። እርሱ ገፊዋ ጠላቷ እንደሆነ ከታወቀና የቤት ቀጋ የሜዳ አልጋ ቢሆንባት ቃሉን አይቀበሉት። ግድ አብረህ ኑር ብለው ይፍረዱበት።
_
፹፪) ባል ከሚስቱ ሌላ ሴት ጋር ሲዘሙት ቢገኝ (ሴትም ከባሏ ሌላ ወንድ ጋር ስትዘሙት ብትገኝ) ዝሙቱን ባይተው ጋብቻው ይፈርሳል። ባልና ሚስት የሆኑ ዘማውያንን አያፋቷቸው። ካህናት ቀኖና ሰጥተው ያስታርቋቸው እንጂ።

አንቀጽ ፳፭
ይህ አንቀጽ እቁባት ማኖር እንደማይገባ ይናገራል።
፩) በኦሪት ነበር እንጂ በወንጌልስ እቁባት ማኖር አይገባም [የተከለከለ ነው]። ዕቁባት ማኖር ዝሙት ነው።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፱ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
423 views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 12:14:52 _
፳፭) እብድ ማግባት አይገባውም።
_
፳፮) አካላትን የሚቆራርጥ ደዌ ሥጋ ያለባቸው ሰዎች ማግባት አይገባቸውም።
_
፳፯) ስትሰስን ተገኝታ የተፈታችውን ሴት ንስሓ መግባቷ እስኪታወቅ ድረስ፣ ጎረቤቶቿ መመለሷን እስኪመሰክሩላት ድረስ። ከተመሰከረለት በኋላ ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞላት ታግባ።
_
፳፰) ሚስት ባሏ ከሞተ ከ፲ ወር በፊት ሌላ ማግባት አይገባትም። በዚህ በ፲ ወር ውስጥ መተጫጨት ግን ይቻላል።
_
፳፱) ከሐፃኒ ከመጋቢ በታች ያለ ሕፃን ሐፃኒ መጋቢ ሳይፈቅድለት ማጨት አይገባውም። በባልና በሚስት ፈቃድ ነው እንጂ ያለሁለቱ ፈቃድ ጋብቻ አይጸናም አይፈጸምም።
_
፴) አካለ መጠን ያልደረሰችን ሴት ማግባት አይገባም። ከመተጫጨት ግን አይከለክልም።
_
፴፩) ያጨ ሙሽራ ማጫ ከሰጠ በኋላ ሊመነኩስ ቢወድ ለሙሽራይቱ የሰጠውን ማጫ መቀበል ይገባዋል።
_
፴፪) ለማግባት አስቀድሞ መተጫጨትና ቃል መጋባት በፍጹም ምክር በፍጹም ፈቃድ ይፈጸም ዘንድ ነው። መልኩን ግብሩን ጸባዩን አጥንቱን ለመመርመር ነው። ለሠርግ የሚያስፈልገውን ለማዘጋጀት ነው።
_
፴፫) ባልና ሚስት እርሱም ሌላይቱን እርሷም ሌላውን ሳያውቁ የተጋቡ እንደሆነ ፍቅር ይጸናል።
_
፴፬) መነኵሴን ማግባት አይገባም። ከስልሳ ዓመት በላይ የሆናትን ሴት ማግባትም አይገባም።
_
፴፭) ማጨት ቃል ኪዳን መጋባት ነው። ከጋብቻ አስቀድሞ የሚሆን አለኝታ ነው። በደብዳቤም ያለ ደብዳቤም ይሆናል። በእጮኝነት ጊዜ ካህናት እጅ ለእጅ አያይዘው፣ አንድ የሚያደርጋቸውን መስቀል አስጨብጠው፣ አንድ ቀለበት አድርገው በደብዳቤ ይወስኑላቸው።
_
፴፮) ያለ ትልወት፣ ያለ ማጫ ማግባትም ይገባል [ይቻላል]።
_
፴፯) ሰባት ዓመት ላልሞላው ሕፃን ማጨት አይገባም።
_
፴፰) አጭቶ ለማግባት ቀን ያልወሰነ ሰው በሀገር ያለ ቢሆን ሁለት ዓመት ይጠብቁት። ሩቅ ሀገር የሄደ ቢሆን ሦስት ዓመት መጠበቅ ይገባል። በታወቀ ምክንያት የቀረ ቢሆን አራት ዓመት መጠበቅ ይገባል። ከዚህ ያለፈ ቢሆን ግን ለሌላ ማጋባት ይገባል።
_
፴፱) በፈቃዷ የምትኖር ሴት የፈለገችውን መርጣ ማግባት ትችላለች። በእናት በአባቷ ቤት ያለች ከሆነች ግን በቤተሰቦቿ ፈቃድ ይሁን።
_
፵) የሚጋቡ ሰዎች አካለ መጠን ያላደረሱ እናት አባት አሳዳጊ የሌላቸው ድኆች ቢሆኑ ፲፭ ዓመት እስኪሆናቸው ይጠብቁ። ከዚያ የፈቀዱትን ያድርጉ።
_
፵፩) አንዲትን ሴት ከታጨች በኋላ ሌላ ወንበዴ አስገድዶ ቢደፍራት እና ያጫት አልቀጥልም ካለ አስገድዶ የደፈራት ሚስት የሌለው ከሆነ ከወደደችው ሊያገባት ይገባል።
_
፵፪) ወንዶች ፈጽመው አካለ መጠን የሚያደርሱበት 20 ዓመት ነው። ይህም ባይሆን 25 ዓመት ነው። ሴቶች ደግሞ 12 ዓመት ነው። ይህም ባይሆን 15 ዓመት ነው።
_
፵፫) ከተጫጩ በኋላ የአንደኛው ግብሩ ጠባዩ የከፋ መሆኑን ተረድቶ እምቢ ቢል ይችላል። እምቢ ያለች ሴቲቱ ከሆነች ዓረቦኑን እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች። ከሰጠ በኋላ አላገባም ያለ ወንዱ ከሆነ ዓረቦኑ ይቀርበታል።
_
፵፬) ልጁ በንጽሕና እኖራለሁ ካለ አባት ግድ አግባ ማለት አይገባውም።
_
፵፭) 25 ዓመት በላይ የሆናት ሴት ብትኖር አባት እናቷ ከማጋባት ቸል ቢሏት እርሷ ወደ ዳኞች አቤት ማለት ይገባታል። ራሷን የቻለች ከሆነች ግን ራሷ ማግባት ይገባታል።
_
፵፮) ጋብቻ ያለቁርባን አይጸናም።
_
፵፯) ለተጋቢዎች አንድ ልብስ ያለብሷቸዋል፣ ከጣታቸው አንድ ቀለበት ያገቡላቸዋል ጠባብ ከሆነ ፊት እርሱ አግብቶ ለእርሷ ይሰጣታል፣ አንድ መስቀል ያስጨብጧቸዋል። አንድ ዘውድ ይደፉላቸዋል እርሱ ደፍቶ ለእርሷ ይሰጣታል። ከዚያ እርሱ ቆርቦ ልብሱን ለእርሷ ይልክላትና ትቆርባለች። እሷም ከእናት ከአባቷ ቤት እርሱም ከእናት ከአባቱ ቤት ይቆያል። እንዲህ እያሉ ፵ ቀን ከኖሩ በኋላ ሠርግ ያደርጉላቸዋል። ልብስ የልጅነት፣ ቀለበት የሃይማኖት፣ ዘውድ የክብራቸው፣ መስቀል የመከራቸው ምሳሌ ነው።
_
፵፰) ሁለተኛ የሚያገቡ ካህናት ቢሆኑ ከሹመታቸው ይሻሩ። ከዚያ በኋላ ሦስተኛ ካገቡ ግን ርኩሳን ይሆናሉ።
_
፵፱) ሴት ስልሳ ዘመን ከሆናት በኋላ ተመልሳ አገባለሁ ብትል ከምእመናን ትለይ።
_
፶) ንጽሕ ጠብቀን ከሴት ርቀን እንኖራለን ብለው ከተሳሉ በኋላ ዳግመኛ የሚያገቡ ሰዎች ሕግ አፍራሾች ናቸው።
_
፶፩) አግብቶ ለፈታ ሰው መጽሐፈ ተክሊል ማድረስ አይገባም። ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞለት በቁርባን ያገባል እንጂ።
_
፶፪) [ቁጥር ፱፻፮] ከሚጋቡት ሰዎች አንዱ ድንግል ቢሆን ለብቻው ተክሊል ያድርሱለት።
_
፶፫) ከሦስተኛ ጊዜ በላይ ማግባት የታወቀ ዝሙት ነው። ከአራተኛ ግቢ የተወለዱ ልጆች ለክህነት ለርስት አይገቡም።
_
፶፬) ብዙ ሴት ማግባት ዝሙት መውደድ ነው። በአንድ ጊዜ ሁለት ሴት ማኖር ለማንም አይገባውም። ይህን ያደረገ ካለ ግን ሁለተኛይቱን እስኪፈታት ድረስ ሥጋውን ደሙን ከመቀበል ቤተክርስቲያን ከመግባት ይከልከል።
_
፶፭) በሚስቱ ላይ ዕቁባት ያኖረ ካህን ቢሆን ከሹመቱ ይሻር፣ ጨዋ ቢሆን ከምእመናን አንድነት ይለዩት።
_
፶፮) ያመነች ሴት ያላመነውን ወንድ ብታገባ ከምእመናን ትለይ። ከእርሱ ተለይታ ንስሓ ብትገባ ግን ይቀበሏት። ልጁን ለኢአማኒ የዳረ ቢኖር ከምእመናን ይለይ።
_
፶፯) ወንድ ሚስቱ ከሞተች ጀምሮ አንድ ዓመት ሳይሆነው ማግባት አይገባውም። ዓመት ሳይሆነው ቢያገባ ግን ሚስቱ ከተወችው ሊወርሰው ከሚገባ ገንዘብ ሁሉ ይከልከል።
_
፶፰) ሴትም ባሏ ከሞተ ጀምሮ አሥር ወር ሳይሆናት ባል ብታገባ ከገንዘቡ ምንም ምን አትውረስ።
_
፶፱) ሳትሰስንበት ሰነፈች ደረቀች ብሎ ሚስቱን የፈታ ሰው ኃጥዕ ተብሎ ይፈረድበታል። በነውር የተፈታችውንም ንስሓ ሳትገባ ያገባት ሰው ቢኖር ኃጥዕ ተብሎ ይፈረድበታል።
_
፷) ባል ለሚስቱ የሚገባውን ፍቅር ያድርግላት፣ ሴትም ለባሏ የሚገባውን ፍቅር ታድርግለት።
407 views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ