Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-04-03 14:11:00 ፩) ሴት ልጅ ወንዶች ባሉበት በዓውደ ምሕረት መዘመር አትችልም። ይህንን ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ነግሮናል። 1ኛ ቆሮ. ፲፬፣ ፴፬ "ሴቶችም በቤተክርስቲያን ዝም ይበሉ። ሊታዘዙ እንጂ ሊናገሩ አልተፈቀደምና። ኦሪትም እንዲህ ብሏልና። ለሴት በቤተክርስቲያን መናገር ክልክል ነው" እንዲል። በተጨማሪም 1ኛ ጢሞ. 2፣11 "ሴት ግን በጸጥታ ትኑር እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ እንድትሰለጥን አንፈቅድም" እንዲል። የሙሴ እኅት ማርያም እንኳ በሴቶች መካከል ዘመረች ይላል እንጂ በወንዶች መካከል አልዘመረችም። ዘጸ. ፲፭፣፳ "የአሮን እኅት ነቢይቱ ማርያምም ከበሮ በእጇ ወሰደች። ሴቶችም ሁሉ በከበሮና በዝማሬ በኋላዋ ወጡ። ማርያምም አስቀድማ ለእግዚአብሔር እንዘምር አለች" እንዲል። ሴት ሴቶችን ማስተማር ትችላለች። ቲቶ ፪፣፫ "ባልቴቶችም___በጎ የሆነውንም ትምህርት ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ለሴቶች ያስተምሩ" እንዲል። ሴቶች ዘማርያት ሆነው በዓውደ ምሕረት ሲዘምሩ ጳጳሱ ዝም ስላለ ልክ ነው አይባልም። ይህ በቸልተኝነት የመጣ ክፉ ልማድ ነው።

ወደፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት፣ ከሥርዓት የተጣላ ትውልድ እንዳይፈጠር እሰጋለሁ። ምክንያቱም አሁን አሁን በተለይ ከ1900 ዓ. ም ወዲህ ብዙ ነገሮች ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጡ ናቸው። ልምድ ሆነው ሰውም ዝም ብሏል። ክፉ ልማድ ሥር ሳይሰድ ካልነቀልነው የወደፊት ምእመናን ሃይማኖታቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጠ እየመሰላቸው ይቸገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት የተጣሉ የልማድ ሰዎች ይሆኑብናል። በእርግጥ አንዳንድ ታላላቅ አድባራት ላይ አሁንም ቢሆን ሴቶች በዓውደ ምሕረት አይዘምሩም። ይህ በሁሉም ሊሆን ይገባል።

፪) የጾም ሰዓት ከዐቢይ ጾም ውጭ ያሉት እስከ ፱ ሰዓት ይጾማሉ። ሰው ግን ጾሞ ግን 7 ሰዓት ላይ ይበላል። ከየት የመጣ ሥርዓት ነው ይሄ??? ጾሙን ሳይጨርሰው ገደፈኮ?። ይህ ሊስተካከል ይገባል።

አንድ ቀን ቆማ ፋሲለደስ አቡነ እንድርያስ ዐቢይ ጾም ሊገባ ሲል ዘወረደ እስከ ፲፪ ሰዓት ይጾማል፣ ሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ ፩ ሰዓት ይጾማል። ከቅድስት እስከ ኒቆዲሞስ ዓርብ እስከ ፲፩ ሰዓት ይጾማል ብለው አስተማሩና እንኳን እውነቱን ነገርኳችሁ እንጂ ከዚህ በኋላ የራሳችሁ ውሳኔ ነው አሉ።

እና ብዙ እውነታዎች አሉ። ያው መረር ቢላችሁም እውነታዋን መናገር ይሻላል። አንዳንዱ ይህ አንገብጋቢ ጉዳይ አይደለም ይልሀል። የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ካለመጠበቅ በላይ አንገብጋቢ ጉዳይ አለ ወይ? በሉ ደህና ዋሉ።
1.8K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 13:29:16 በቴሌግራም ቻናሌ ከሰኞ እስከ ዓርብ ማታ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ 2 ሰዓት ተኩል ትምህርት አለ። ከምጽፈው መጠየቅ ይቻላል። ኑ እንጠያየቅ። የቴሌግራም ቻናሌ https://t.me/betremariyamabebaw ነው። ፍትሐ ነገሥቱን እስከ ትንሣኤ በዚህ መልኩ እንጨርሰዋለን።

ዛሬም አለ
1.8K views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 08:44:04
አንዳንድ ጳጳሶች ግን ቆቡን ከመድፋታችሁ በፊት ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን ብትማሩ ደስ ይለኛል። ከሌላ እምነት ሰዎች ጋር በቦታ በጋራ የጸለየ ጳጳስ፣ ኤጲስ ቆጶስ፣ ቄስ ከሹመቱ ይሻር ብለው ሠለስቱ ምእት በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፬፣ አንቀጽ ፭፣ አንቀጽ ፮፣ አንቀጽ ፱ ተናግረዋልና።
2.3K viewsedited  05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 07:31:29
______ወልዲያ፣ ደሴ፣ ቆቦ____
መሠረታዊ የግእዝ ቋንቋ መማሪያ
#ወልዲያ #ደሴ #ቆቦ ገብታለች። ስለዚህ ጥቂት ኮፒዎች ብቻ ስላሉ ደውላችሁ መውሰድ ትችላላችሁ። መጽሐፏን ከአቤል ተፈራ በላይ ስልክ ቁጥር 0912954888 ማግኘት ትችላላችሁ።
2.3K views04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 20:07:31 @በግልጽ ክህነቱ የተሻረ ቄስ፣ ጳጳስ፣ ዲያቆን ከሆነ ግን ከእርሱ መቁረብም፣ መጠመቅም፣ መባረክም አይገባም። ጸጋን አያሰጥምና። የካደ ውስጥ ውስጡን ከሆነና በገሐድ ካልሆነ ሰው ካላወቀው ግን ራሱ ይጎዳል እንጂ ምእመኑ ጸጋ አይቀርበትም።
1.5K viewsedited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 17:29:42 __በክፉ ጳጳሳት ብንባረክ ረድኤት እናገኛለንን???__
ጳጳሳት (ካህናት) ሌቦች፣ አጭበርባሪዎች፣ ኬልቄዶናውያን [መለካውያን]፣ ሙሰኞች፣ ዘማውያን፣ ከሓድያን ሊሆኑ ይችላሉ። እንዲህ ቢሆኑ የሚጎዱት በዋናነት ራሳቸው ናቸው። የእነርሱ በደል በሕዝብ ላይም ሥጋዊ መከራን ሊያመጣ ይችላል። የአባ አጋግዮስ ስግብግብነትና ሆዳምነት ዘመነ ሰማዕታትን እንዳመጣው ማለት ነው። ጳጳሳት የምግባር ጥሰት ቢኖርባቸው ራሳቸውን ይጎዳሉ እንጂ ለምእመኑ ግን ሀብተ ወልድና (ልጅነት)፣ ክህነት፣ ሥርየት ያሰጣሉ። ምዕመኑ ሥራቸውን (ምግባራቸውን) አለመቀበል ይችላል። ወዘከመ ምግባሮሙሰ ኢትግበሩ ብሎ ጌታ እንደተናገረው። መልካም ትምህርታቸውን እየተቀበልን ክፉ ትምህርታቸውን እና ድርጊታቸውን አለመቀበል ከምእመናን ይጠበቃል። አባት ስለሆኑ ስሕተታቸውን ሁሉ እንቀበል አይባልም። በክፉ ሥራቸው እንደ አባት አለመቀበል እንችላለን። በሚያሰጡን ጸጋ ግን ምንም ቢሆን እግዚአብሔር የሾማቸው ስለሆኑ ፈጽሞ መራቅ አይገባም። እነርሱ በቤተክርስቲያን የእግዚአብሔርን ሀብት እንዲያስተላልፉ የተመደቡ ናቸው እንጂ በዋናነት ሀብቱን በእነርሱ አድሮ የሚሰጠን እግዚአብሔር ነው። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፱፣ ቁጥር ፫፻፵፬ [ሐተታ ትርጓሜ] "ክህነት የአምላክ ገንዘብ ናት። በኃጥኡ ቄስና በጻድቁ ቄስ በተናዘዙ ሰዎች መካከል ሀብት ሥርየት ልጅነት በሚያገኙበት ሥልጣነ ክህነት መለያየት የለባቸውም። ኃጥእ ቄስ ራሱን ይጎዳል እንጂ ለሌላው ሀብት ልጅነት ሥርየት ይሰጣልና" ተብሎ እንደተገለጸው። ለምሳሌ አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ጳጳሳት ከላይ የጠቀስናቸውን በደሎች ሁሉ የሠሩ ክፉዎች ቢሆኑ ከእነርሱ አንባረክም፣ አንጠመቅም፣ ክህነት አንቀበልም ማለት አይገባም። ክፋታቸው ራሳቸውን ብቻ ይጎዳል እንጂ ምእመኑን አይገዳምና። ክፉ ጳጳስም ደግ ጳጳሳም ቢያጠምቁ፣ ክህነት ቢሰጡ የሁለቱም ጸጋ አንድ ነው። ራሳቸው ግን ከኩነኔ አያመልጡም። ደግ ቢሆን በደግነቱ ይጠቀማል። ክፉ ቢሆን በክፋቱ ይጎዳል። ለሌሎች ሰዎች በሚያስተላልፉት ጸጋ ግን ልዩነት የለም።

ብዙ ጊዜ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የሚባለው አጭበርባሪ ድርጅት ምእመናንን የሚያታልለው በዚህ ነው። ክፉ ጳጳሳትንና ክፉ ካህናትን መሠረት አድርጎ ጸጋ ስለማያሰጡ ከእነርሱ አትቁረቡ፣ አትጠመቁ፣ ክህነት አትቀበሉ እያሉ ክህነት፣ ቁርባን፣ ጥምቀት እንደሌለ አድርገው ያቀርባሉ። ይህንን ያስተካክልልናል ብለው ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥ ይነግሣል ብለው እስከዚያ ምሥጢራትን ሳይካፈሉ ሰዎች እንዲኖሩ ይሰብካሉ። ይህንን የወንበዴ ድርጅት ማንኛውም ክርስቲያን ሊያወግዘው ይገባል። ከላይ በጠቀስኩት ፍትሐ ነገሥት እንደተገለጠው ጳጳስ ክፉ ቢሆን፣ ቄስ ክፉ ቢሆን ራሱ ይጎዳል እንጂ ክህነት፣ ልጅነት አያሰጥም አይባልም። ከእርሱ አትቁረቡ አይባልም። በጳጳሱም በቄሱም አድሮ እኒህን ጸጋዎች የሚሰጥ እግዚአብሔር ነውና። በልጅነት የሚወልደን ክርስቶስ ነውና። ቤተክርስቲያን ሁላችንንም በጥምቀተ ክርስትና ወልዳናለች። እስመ ቤተክርስቲያን ወለደቶሙ ለኵሎሙ በጥምቀተ ክርስትና እንዲል። ፍት. ነገ. ፱፣፪፻፹። በክርስቶስ አምነው የተጠመቁ ሰዎች በልጅነት አንድ እንደሆኑ ተነግሯል።

በዚህ ሰሞን በሆነው ውንብድና ጳጳሳት የሊቃውንት ጉባዔ ያቀረበውን ኦርቶዶክሳዊ ቀኖና ትተው ምንም እንኳ በቀኖናው መሠረት ውግዘቱ የጸና ቢሆንም በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩና በክቡር ሽመልስ አብዲሳ አማካኝነት በገባናቸው ስምምነቶች መሠረት ውግዘቱን አንሥተናል ብለው አሳዝነውናል። ኬልቄዶናውያን ማለታችንም ፈጻምያነ ፈቃደ ንጉሥ በመሆናቸው እንጂ ክልዔ ባሕርይ ብለው እንዳልሆነ ልብ ይሏል። ከዚህ በኋላ እንደ አባት አለመቀበል እንችላለን ማለትም ክህነት፣ ልጅነት፣ ጥምቀት አያሰጡም ለማለት አይደለም። አባትና ልጅ ሲጣሉ ልጅ እናቱን ያን ባልሽን ተው በይው ይላል። አባትም ሚስቱን ያን ልጅሽን አሳርፊው ይላል ይባላል። ሁለቱ የተኳረፉበት ነገር ስላለ እንጂ ወላጅ መውለዱን ክዶ አይደለም። ክፉ ሥራውን እንዲያቆም የተነገረ ንግግር ነው። ልዑል እግዚአብሔር ሙሴን አበሱኒ ሕዝብከ (ሕዝብህ በደሉኝ) እንዳለው ያለ ነው። ቢበድሉበት ሕዝብየ ይላቸው የነበረውን ሕዝብከ ብሎ ተናግሯል። ስለዚህ ይህንን ክፉ ሥራ ጳጳሳት ስለሠሩ ከእነርሱ አንጠመቅም፣ ክህነት አንቀበልም፣ አንቆርብም ማለት አይገባም። በራሳቸው በደል ራሳቸው ይጠየቁበታልና። ለእኛም በረከት አይቀርብንምና። ምእመናን ሁልጊዜም አንድነታቸው የጸና መሆን አለበት። ይህንን አይተው ወደሌላ እምነት መፍለስ አይገባም። ከውስጣችን ሆነው እኛን ገፍተው ወደሌላ እምነት እንድንሄድ የሚፈልጉ ክፉ እረኞች ሊኖሩ ይችላሉ። እኒህን በጠራ መረጃና ማስረጃ እየያዝን እነርሱን እያስወጣን እኛ በአንድነት በፍቅር መኖር አለብን። የክርስቲያኖች አንድነት በክርስቶስ የወይን ግንድነት የተመሠረተ ነው። ምእመናን ቅርንጫፎች ናቸው። አንድ ሰው ክፉ ሥራ ሲሠራ ከግንዱ መለየቱ እርግጥ ነው። ጳጳስም ክፉ ሥራ ቢሠራ ለራሱ ሕይወት አይኖረውም። ለሌሎች ግን ሕይወትን ይሰጣል። ይኽም ገንዳን ይመስላል። ገንዳ የተቆረጠ ግንድ ነው። ራሱ ልምላሜ የሌለው ቢሆንም ነገር ግን ውሃን አቁሮ ለሌሎች ዕፀዋት ልምላሜ ይሆናል። ጳጳስ ክፉ ቢሆን እንደ ገንዳው ነው የሚሆን። ክፋቱ ራሱን ይጎዳዋል እንጂ የሚያጠምቀው ጥምቀት፣ የሚያቆርበው ቁርባን፣ የሚሰጠው ክህነት ለምእመናን ጸጋን ያሰጣል።

በጳጳሳት ሹመት ምእመናን ድርሻ አላቸው። የአንድ ሀገረ ስብከት ምእመናን ችግር ያዩበት ጳጳስ ካለ አለመቀበል መንፈሳዊ መብታቸው ነው። ወደፊት ሲሾም ደጋግ መነኮሳት፣ የተማሩና ግብረ ገብ የሆኑ መነኮሳት እንዲመረጡ ምእመኑ ጫና መፍጠር አለበት። ደጋግ ጳጳሳት ቢሾሙ ለሀገር በረከትን ሰላምን ፍቅርን ያመጡልናል። ለምእመናን ዕረፍተ ሥጋ ዕረፍተ ነፍስን ያመጡልናል። ስለዚህ ከዚህ በኋላ የሚሾሙት ላይ ጥንቃቄ እናድርግ። ክፉዎች ሲመጡ እምቢ እንበል። አብዝተን መጸለይ፣ ንስሓ እየገባን ሥጋውን ደሙን መቀበል ይገባናል።
2.2K views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 04:45:27 _
፴፩) ቄሱ ዲያቆኑን ቢጣላው፣ ዲያቆኑም ቄሱን ቢጣላው ቅጣታቸው በኤጲስ ቆጶሱ ሰባት ሱባዔ ይሁን። አንባቢ ቄሱን ቢጣላው ቄሱ ይቅጣው።
_
፴፪) ካህን ከካህን ጋር ቢጣላ ታርቀው እስኪመለሱ ድረስ ሁለቱም ከአገልግሎት ይለዩ።
_
፴፫) ደዌ ሥጋ የታመመ ሰው እና ለምጻም ሰው ቤተመቅደስ ገብቶ ማገልገል አይገባውም። ነውር ሆኖ አይደለም። ካህናትን እንዳያሰድብ ነው እንጂ።
_
፴፬) ካህን ኤጲስ ቆጶሱ የሰጠውን የክህነት ወረቀት ሩቅ ሀገር ሲሄድ ካልያዘው የዚያ ሀገር ሰዎች ወረቀቱን ሳያዩ አይቀበሉት።
_
፴፭) ከተወገዘ ሰው ጋር አብሮ የጸለየ ከምእመናን ይለይ።
_
፴፮) {ቁጥር ፫፻፴፱} ካህን በአነዋወሩ ደግ ቢሆን ተስማምተው ሊያከብሩትና ሊታዘዙት ይገባል። በአኗኗሩ ክፉ ቢሆን ግን፣ በደሉ ቢታወቅ፣ በበደሉ ጸንቶ ቢኖር ሊቃውንት መጽሐፍ እንዳዘዘው ሊፈርዱበት ይገባል። በደሉ ባይታወቅ ግን፣ በበደሉ ጸንቶ ባይኖር ሊሽሩት አይገባም።
_
፴፯) ክህነት የአምላክ ገንዘብ ናት። በኃጥኡ ቄስና በጻድቁ ቄስ በተናዘዙ ሰዎች መካከል ሀብት ሥርየት ልጅነት በሚያገኙበት ሥልጣነ ክህነት መለያየት የለባቸውም። ኃጥእ ቄስ ራሱን ይጎዳል እንጂ ለሌላው ሀብት ልጅነት ሥርየት ይሰጣልና። [ቁጥር ፫፻፵፬ ሐተታ]።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፱ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው።
2.4K views01:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 04:45:27 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፰___
አንቀጽ ፱ የካህናትን ሁሉ ነገር ይናገራል። ካህናት የሚላቸው የሚከተሉት ናቸው።
፩) ሊቀ ጳጳሳት (ፓትርያርክ)
፪) ጳጳስ (መጥሮጶሊስ)
፫) ኤጲስ ቆጶስ
፬) ቆሞስ (ኮሬ ኤጲስ ቆጶስ)
፭) ቀሳውስት
፮) ዲያቆናት
፯) ንፍቀ ዲያቆናት
፰) አናጉንስጢስ
፱) መዘምራን
፲) አፃዌ ኆኅት. ናቸው።
፩) ከተጠመቀ በኋላ የገዘሩትን (የገረዙትን)፣ በግድ ሰዎች የሰለቡትን፣ ባለመድኃኒት በደዌ ምክንያት አባለ ዘሩን መድኃኒት አድርገት የተቆረጠውን ለክህነት በቅተው ከተገኙ ይሾሙ። በፈቃዱ ራሱን የሰለበ ግን አይሾም።
_
፪) ባሮች ጌቶቻቸው ሳይፈቅዱላቸው ከክህነት ሥራ ወገን በማናቸውም አይሾሙ። ጌታው ነጻ ያወጣው ቢሆንና በራሱ ፈቃድ ያድር ዘንድ ነጻ ቢያወጣው ለክህነት የበቃ ቢሆን ይሾም።
_
፫) ምእመን በክርስቶስ ስም አምኖ መከራ ቢቀበል ዲቁና ቅስና ተሹሞ ለማገልገል በአንብሮተ እድ አይሹሙት። አምኖ በሰማዕትነት በተቀበለው መከራ መንፈስቅዱስ አክብሮታልና። መንፈስቅዱስ ሹሞታልና። የክርስቶስን ስም አልክድም ብሎ አምኖ ወደ ዓላውያን ነገሥታት ገብቶ መከራ ባይቀበል፣ እጁን በሰንሰለት እግሩን በእግር ብረት ታሥሮ መከራ ያልተቀበለ ቢሆን ከሰው የተለየ መከራ ባያገኘው ግን በአንብሮተ እድ ይሹሙት። ኤጲስ ቆጶስነት የሚሾም ቢሆን ግን በአንብሮተ እድ ይሹሙት።
_
፬) ሰው በአካሉ ነውር ስለተገኘበት ከሹመት አይከልከል። አንካሳም ቢሆን፣ አንድ ዓይናም ቢሆን፣ ግራኝም ቢሆን በቅቶ ከተገኘ መቀደስ የሚችል ከሆነ ይሾም።
_
፭) ቤተክርስቲያን ሁላችንንም በጥምቀተ ክርስትና ወልዳናለች።
_
፮) ሁለተኛ ያገባ፣ ሚስት ካገባ በኋላ ገልጦ ወይም ሰውሮ ዕቁባት ያኖረ፣ አግብታ የተፈታችውን ያገባ፣ ዘማዊትን ያገባ፣ ወደዘፈን ቤት የምትሄደውን ያገባ ክህነት አይሾም።
_
፯) አዲስ አማኝ የሃይማኖቱ መረዳት ንጽሕናው እስኪመረመር ድረስ ክህነት አይሾም።
_
፰) አንዱስ እንኳ ለክህነት ይበቃል ብለው ሳይመሰክሩለት አይሾም። ካህናት ከመሾማቸው በፊት ሊቀ ዲያቆኑ አስቀድሞ በንባብ ይፈትናቸው።
_
፱) ለጸሎት ለአገልግሎት እንዳያንሱ በቤተክርስቲያን የሚኖሩ ካህናት ጥቂቶች አይሁኑ። ዳግመኛም ቤተክርስቲያን የምትሰጠው ምግብ እንዳታጣ ካህናት አይብዙ። ምግብ ልብስ መስጠት በሚቻላት መጠን ትሹም እንጂ።
_
፲) ኤጲስ ቆጶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሾመ ነፍስን ሥጋን ከጥፋት ይጠብቅ ዘንድ ነው። ክህነት በክብር ከመንግሥት ትበልጣለች።
_
፲፩) በብሉይ ኪዳን ደቂቀ ሜርያርይ ንዋየ ቅድሳትን ይሸከሙ ነበር፣ ደቂቀ ጌድሶር አዕማደ ደብተራ ኦሪትን ይሸከሙ ነበር፣ ደቂቀ ቀዓት ታቦተ ጽዮንን ይሸከሙ ነበር፣ አልዓዛር ኢታምር መሥዋዕተ ሠክር መሥዋዕተ ነግህ ይሠው ነበር፣ ናዳብ አብዩድ አርደው አወራርደው ያቀርቡ ነበር፣ አሮን ከዓመት አንድ ጊዜ ቅድስተ ቅዱሳን ገብቶ ይሠዋ ነበር፣ ሙሴ አሮንን ከሾመ በኋላ የክህነት ሥራን አልሠራም።
_
፲፪) ወደ ቤት ስትገቡ "ሰላም ይኵን ለሰብአ ዝንቱ ቤት" በሉ። በረከት የሚገባው ሰው ከዚያ ቢኖር በረከታችሁ ይደርበት። በረከት የሚገባው ሰው ባይገኝ ግን በረከታችሁ ወደእናንተ ይመለስ።
_
፲፫) በከንቱ የሚራገም ሰው ራሱን ብቻ ረገመ። በማይገባ የሚሆን መርገም በማንም በማን አይደርስም። [ቁጥር ፪፻፺፫]።
_
፲፬) (ሐተታ) እየጸለይን ሳለ አንዱ ሊያነጋግረን ቢመጣ አረማዊ ከሆነ ውዳሴ ማርያም እየደገምን ከሆነ የዕለቱን ጨርሰን፣ ዳዊት እየደገም ከሆነ አሥሩን መዝሙር ጨርሰን በአቡነ ዘበሰማያት አሥረን እናነጋግረው። ክርስቲያን ከሆነ የያዝነውን አንቀጽ ጨርሰን በአቡነ ዘበሰማያት አስረን እናነጋግረው። ከዚያ ካረፍንበት መቀጠል ነው። አቋርጠን ከተነጋገርን ግን እንደገና ጀምረን መጸለይ ይገባናል።
_
፲፭) መዓርጋቸውን እንዳያስነቅፉ ካህናት ምጽዋት መቀበል አይገባቸውም። ከቤታቸው ይስጧቸው እንጂ ከአደባባይ ወድቀው አይለምኑ።
_
፲፮) ካህናት ከሠርግ አዳራሽ ሄደው ዘፈን መስማት አይገባቸውም። የሚፈክሩት የሚዘፍኑት ሳይመጡ በልተው ጠጥተው መርቀው ይመለሱ እንጂ።
_
፲፯) ካህን ከሰው ወገን ለአንዱስንኳ አይገዛ። ካህናት የሰው ተገዦች ሊሆኑ አይገባም። ክፉ ሥራ በመሥራት ለሰው አብነት አይሁኑ። ካህን ከሥጋዊ ሹማምንት ለአንዱስንኳ ሹም አይሁን። [ቁጥር ፫፻፯]
_
፲፰) ካህናት ፈጽመው አይነግዱ። እደ ጥበብ ይማሩ እንጂ። ጽፈው ደጉሰው ራሳቸውን ያኖሩ ዘንድ።
_
፲፱) በካህናት የሚፈረደውን ፍርድ ወደ መኳንንት አይውሰዱት። የዚህ ዓለም ነገሥታት መኳንንት በካህናት ላይ አይፈርዱምና። እያንዳንዱ ካህናት በመኳንንት ይፈርዳሉ እንጂ።
_
፳) በኤጲስ ቆጶስ ክፉ ቃል የሚናገር ሰው እነሆ እግዚአብሔርን በደለ።
_
፳፩) ልጄ ሆይ ቃለ እግዚአብሔር ወንጌልን ያስተማረህን ልጅነትን ለማግኘት ምክንያት የሆነኽን እንደ እግዚአብሔር አክብረው።
_
፳፪) ካህናት በጨዋ ዳኛ መዋስ አይገባቸውም። ራሱን የሰለበ ካህን ከሹመቱ ይሻር።
_
፳፫) ገበጣ የሚጫወት ካህንን ተው ይበሉት። ባይተው ከክህነቱ ይሻር። ሕዝባውያንም ካሉ ከምእመናን ይለዩ።
_
፳፬) በአንድ ዓይና፣ በአንካሳ፣ በዕውር የዘበተ ካህን ቢኖር ከምእመናን ይለይ።
_
፳፭) በሐሰት የማለ ካህን ከሹመቱ ይሻር። ሥጋዊ በሽታ ሳይከለክለው ዐቢይ ጾምንና ረቡዕ እና ዓርብን የማይጾም ካህን ከሹመቱ ይሻር።
_
፳፮) የቅስና መዓርግ ከተቀበለ በኋላ ሚስት ያገባ ለሹመቱ ይሻር።
_
፳፯) ቄስ ጠጥቶ ቢሰክር፣ ቢራቆት ከሰው ተለይቶ ሰባት ሱባዔ ይጹም። ከቅስና በታች ባለ መዓርግ በዲቁና እያገለገለ አንድ ዓመት ይኑር። ዲያቆን ቢሆን አምስት ሱባዔ ይጹም። በንፍቀ ዲያቆናት አራት ወር ያኑር።
_
፳፰) ጨዋው ጨዋውን ቢሰድብ እንደ ሕፃን ተቆጥተው ይተውት። ካህን ካህኑን ቢሰድብ ይለይ። ቀኖናውን እስኪፈጸም ድረስ ከምእመናን ይለይ።
_
፳፱) ነገር እያሠራ ዘወትር የሚያጣላ ሰው ቢኖር አንድ ጊዜ ሁልጊዜ ይተው። ዘወትር ነገር መሥራቱን ባይተው ከሹመቱ ይሻር።
_
፴) የወታደር ልብስ የለበሰ ቄስ ቢኖር አራት ወር ከቤተመቅደስ በአፍአ ይቁም። ዲያቆን ቢሆን በአፍኣ ሁለት ወር ይቁም።
2.1K views01:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 16:50:58 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፯__
አንቀጽ ፯ ስለ ዲያቆናት ይናገራል።
፩) ዲያቆናት ጸጥ ያሉ፣ የሚታዘዙ ይሁኑ። ዲያቆናት ሁለት ሦስት ሰዎች መስክረውላቸው ይሾሙ። በአገልግሎት ሁሉ ይፈተኑ። ለሰው የሚያዝኑ የሚራሩ ይሁኑ። በቀለኞች ሳይሆን በቀልን የሚተው ይሁኑ። ቁጡ ብስጩ አይሁኑ።
_
፪) ዲያቆናት ባለጸጎችን ደስ የሚያሰኙ ነዳያንን የሚያሳዝኑ አይሁኑ። አንድነትን ሦስትነትን (ምስጢረ ሥላሴን) ለመማር ለማስተማር ይትጉ። ምዕመናንን በፍጹም ክብር ያክብሩ። ሰውን በማፈር እግዚአብሔርን በመፍራት ይኑሩ። ዲያቆን በአንብሮተ እድ ይሾማል። ቀሳውስት ዲያቆናትም ቆመው ይጸልዩለት።
_
፫) ሰው ተምሮ ከተገኘ ዲቁና በ7 ዓመት፣ በ12 ዓመት መሾም ይችላል። ሀገሪቱ ሰፊ ካልሆነች ሰባት ዲያቆናት ሊሾሙ ይገባል። ሀገሪቱ ሰፊ ከሆነች ኤጲስ ቆጶሱ እንደወደደ ይሹሙ። ዲያቆናት ከቤተክርስቲያን ገንዘብ ይመገቡ። ዲያቆናትን ያክብሯቸው። ዲያቆን ቀሳውስትን ያገልግላቸው። ከሕዝቡ ወገን ጠያቂ የሌላቸውን ድውያንንም በመጠየቅ ያገልግላቸው። ለኤጲስ ቆጶሱም ችግራቸውን ይንገረው።
_
፬) ዲያቆኑ በቤተክርስቲያን ሕዝቡ እንዳይተኙ እንዳይስቁ እንዳይዘባበቱ ይጎብኛቸው። ዲያቆን ደሙን በቄሱ ትእዛዝ ለምእመናን ያቀብል። በመዓርግ ከእርሱ ለሚበልጥ ደሙን አያቀብል። ኤጲስ ቆጶስ ቄስ ባይኖር በምሳ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት ደግሞ ባርኮ ይስጥ። ዲያቆን ያስተምት ያጠምቅ፣ ሥጋውን ደሙን ያቀብል ዘንድ፣ ሕዝብን ይባርክ ዘንድ አይገባውም። ዲያቆን ዓውዱን አይያዝ።
_
፭) ሊቀ ዲያቆን በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ከኤጲስ ቆጶስ ቀጥሎ ይቁም። ከኤጲስ ቆጶሱ ብቻ በቀር ሌላ በበላዩ አይፍረድ አይቀመጥ። እስመ ውእቱ ሊቀ ካህናት። የካህናት አለቃ ነውና።
_
፮) ዲያቆናት ሆይ የተቸገሩትን ልትጎበኟቸውና የተቸገሩበትንም ነገር ለኤጲስ ቆጶሳችሁ መንገር ይገባችኋል።
_
__አንቀጽ ፰___
ስለ ንፍቀ ዲያቆን፣ አናጉንስጢስ፣ አፃዌ ኆኅት፣ መዘምር (ዳዊት ደጋሚ) እና ዲያቆናዊት ይናገራል። ሁሉም በቃል እንጂ በአንብሮተ እድ አይሾሙም።
፩) አናጉንስጢስ (አንባቢ) በንባብ ከፈተኑት በኋላ ይሾም። ነገር የማያበዛ ይሁን። ዋዛ ፈዛዛ አይናገር። አከናውኖ የሚያናብ ይሁን። የሚያነበውን ለመሥራት የሚተጋ ይሁን። ሚስት የሌለው ይሾም። አናጉንስጢስ ቢሰርቅ ለዓመት ከአገልግሎት ይከልከል። ከዓመት በኋላ ያንብብ። እስከ ዕለተ ሞቱም በአናጉንስጢስነት መዓርግ ይኑር።
_
፪) ዲያቆናዊትነትን የምትሾም ሴት 60 ዓመት የሆናት ትሁን። በአንድ ወንድ ጸንታ የኖረች ትሁን። በበጎ ሥራ ጸንታ እንደኖረች የመሰከሩላት ትሁን። ልጆቿን በሥርዓት ያሳደገች፣ እንግዳ የምትቀበል ትሁን። ዲያቆናዊት የምትሾም ሴቶችን እንድታገለግል ነው። ተጠማቂ ሴትን ከአንገቷ በላይ ቄሱ ሜሮን ይቀባታል። የቀረውን የአካል ክፍል ዲያቆናይቱ የቄሱን እጅ ይዛ ትቀባታለች። ዲያቆናዊት ሴቶችን ትገሥፃቸው።
_
፫) ንፍቀ ዲያቆናት ረዳቶች ናቸው። በዲያቆን ቦታ ሆነው ማገልገል አይገባቸውም። ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩ አልተፈቀደም። ልብሰ ተክህኖ መልበስ አልተፈቀደላቸውም።
_
፬) መዘምራን ዳዊት ደጋሚ እንደመሆናቸው ዳዊት. ይድገሙ። መዘምራን እና አናጉንስጢሳውያን ሚስታቸው ሞታ ሁለተኛ እናግባ ቢሉ ማግባት ይችላሉ።
_
፭) በር ጠባቂዎች (ዐጸውተ ኀዋኅው) ወንዶች በሚገቡበት በር ቁመው ይጠብቁ። በር ጠባቆች አንድ ሰዓት እንኳ ከበር መለየት የለባቸውም።
_
፮) ከሴቶች ወገን ቅስና ዲቁና መሾም አይገባም። በቤተክርስቲያንም ጸሎት መጀመር አይገባቸውም። ቃላቸውን ከፍ አድርገው አይጸልዩ።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
ክፍል ፰ ይቀጥላል።
መ/ር በትረማርያም አበባው።
1.3K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 07:50:04 ___ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፮___
አንቀጽ ፮ ስለ ቀሳውስት ይናገራል።
፩) ቅስና ነውር ነቀፋ የሌለበት አንዲት ሴት ያገባ ሰው ይሾም። ቂመኛ አይሁን። አብዝቶ የሚጠጣ አይሁን። እንግዳ መቀበልን የሚወድ ይሁን። ደግ ሰው፣ ቸር ይሁን።
_
፪) ነገረ ሃይማኖትን የሚያስተምር ይሁን። እውነተኛ ትምህርትን በማስተማር ሰውን ማረጋጋት የሚችል ይሁን። ምን የበቃ ቢሆን ቄስ ፴ ዓመት ሳይሞላው አይሾም። የመጻሕፍትን ነገር የማያውቅ ቅስና አይሾም። ይልቁንም አራቱን ወንጌል ያልተረጎመ አይሾም።
_
፫) አምስት ሰዎች ያልመሰከሩለት ቅስና አይሾም። ቄስ በኤጲስ ቆጶሱ በአንብሮተ እድ ይሾማል። ቀሳውስት ቁመው ይጸልዩለት። ቄስ መምህር እንደመሆኑ ያስተምር።
_
፬) የቄስ ሥልጣን ማስተማር፣ ማጥመቅ፣ ቀድሶ ማቁረብ እና ሕዝቡን መባረክ ነው። ቄስ ማንንም አይሹም። ቀሳውስት በመንበሩ ዙሪያ ከኤጲስ ቆጶስ ፊት ሊሄዱ አይገባም።
_
፭) ቄስ ሁለት እህትማማች ካገባ ሰው ሠርግ አይሂድ። ይህን ያደረገ ሰው ንስሓ የሚገባው ነውና። ቄስ ከሐዋርያት የወጣ ሥርዓት በሕዝቡ ምንም ምን አያጽናባቸው።
_
፮) የሚታከም ቢሆን ነው እንጂ ቄስ በማንም በማን ፊት አይራቆት። ቀሳውስት ከኤጶስ ቆጶሳቸው በዓመት ሦስት ጊዜ ይሰብሰቡ።
_
፯) በጉቦ፣ በማስፈራራት፣ በማድላት፣ በተንኮል የተሾመ ቄስ ይሻር። ሁለት ሴት ያገባ ቄስ ይሻር። ሕዝቡን ከማስተማር ቸል የሚል ቄስ ይሻር።
_
፰) ሐሰት በመመስከር ሰውንም በማጣላት የታወቀ፣ የሚታበይ፣ ሥርዓትን አውቆ የማይሠራት፣ ዘወትር የሚሰክር፣ አራጣ የሚቀበል፣ ከሴሰኛ ሴት የደረሰ፣ በጠንቋዮች ነገር የሚያምን፣ ኮከብ በመቁጠር የሚታመን፣ ሥር የሚምሱትን ቅጠል የሚበጥሱትን ነገር የሚያምን፣ ከከሓድያን የተጠመቀ ቁርባናቸውን የተቀበለ፣ አብሯቸው የሚጸልይ ከክህነቱ ይሻር።
_
፱) አባለዘሩን የሰለበ፣ ሲሰርቅና በሐሰት ሲምል የተገኘ፣ የጋብቻ ሥርዓትና ሥጋ መብላት እንዲሁም ወይን መጠጣት አይገባም የሚል፣ በገበያ መካከል የሚበላ፣ ከመሸታ ቤት ገብቶ የሚጠጣ፣ ሙቶ የተገኘውን የአውሬ ትራፊ የሆነውን የሚበላ፣ ከደዌ ለመዳን ከዓላውያን ቤተክርስቲያን የገባ፣ የአይሁድን ጾም የሚጾም በዓላቸውን የሚያከብር፣ ወደ ዓላውያን ቤተክርስቲያን እጅ መንሻ የሚወስድ፣ ተወግዞ ከተለየው ጋር የተነጋገረ አብሮት የሚጸልይ፣ የኤጲስ ቆጶሱን ደብዳቤ ሳይዝ ሩቅ ሀገር የሚሄድ ከክህነቱ ይሻር።
_
፲) አገለግላለሁ ብሎ ወይም እመነኩሳለሁ በማለት ሚስቱን የፈታ ቄስ ይሻር። በታወቀ ምክንያት የተሻረ ቄስ ወይም ዲያቆን ቢኖርና ከተሻረ በኋላ የክህነት ሥራ ቢሠራ ከምዕመናን ፈጽሞ ይለይ። መሻሩን እያወቀ ከእርሱ ጋር አንድ የሚሆንም ይለይ።
_
፲፩) ምእመናንን ከቁርባን የሚከለክል ቄስ ከሹመቱ ይሻር። ቄስ ከተሾመ በኋላ ሳይሾም የሠራት ኃጢአት ብትታወቅበት ከምእመናን ይለይ። ቀሳውስት ሐሜተኞች አይሁኑ።
_
፲፪) ለሴት በደሟ ወራት ሥጋውን ደሙን ያቀበለ ከሹመቱ ይሻር። ቀሳውስት ዲያቆናት ከሚያገለግሉባት ቤተክርስቲያን ወጥተው ወደ ሌላ ቢሄዱ ምእመናን ሊቀበሏቸው አይገባም።
_
፲፫) ቄስ ሚስቱ ብትወልድ ከአገልግሎት አይከልከል።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
ክፍል ፯ ይቀጥላል።
መ/ር በትረማርያም አበባው።
902 views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ