Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.24K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-04-18 12:14:52 _
፳፭) እብድ ማግባት አይገባውም።
_
፳፮) አካላትን የሚቆራርጥ ደዌ ሥጋ ያለባቸው ሰዎች ማግባት አይገባቸውም።
_
፳፯) ስትሰስን ተገኝታ የተፈታችውን ሴት ንስሓ መግባቷ እስኪታወቅ ድረስ፣ ጎረቤቶቿ መመለሷን እስኪመሰክሩላት ድረስ። ከተመሰከረለት በኋላ ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞላት ታግባ።
_
፳፰) ሚስት ባሏ ከሞተ ከ፲ ወር በፊት ሌላ ማግባት አይገባትም። በዚህ በ፲ ወር ውስጥ መተጫጨት ግን ይቻላል።
_
፳፱) ከሐፃኒ ከመጋቢ በታች ያለ ሕፃን ሐፃኒ መጋቢ ሳይፈቅድለት ማጨት አይገባውም። በባልና በሚስት ፈቃድ ነው እንጂ ያለሁለቱ ፈቃድ ጋብቻ አይጸናም አይፈጸምም።
_
፴) አካለ መጠን ያልደረሰችን ሴት ማግባት አይገባም። ከመተጫጨት ግን አይከለክልም።
_
፴፩) ያጨ ሙሽራ ማጫ ከሰጠ በኋላ ሊመነኩስ ቢወድ ለሙሽራይቱ የሰጠውን ማጫ መቀበል ይገባዋል።
_
፴፪) ለማግባት አስቀድሞ መተጫጨትና ቃል መጋባት በፍጹም ምክር በፍጹም ፈቃድ ይፈጸም ዘንድ ነው። መልኩን ግብሩን ጸባዩን አጥንቱን ለመመርመር ነው። ለሠርግ የሚያስፈልገውን ለማዘጋጀት ነው።
_
፴፫) ባልና ሚስት እርሱም ሌላይቱን እርሷም ሌላውን ሳያውቁ የተጋቡ እንደሆነ ፍቅር ይጸናል።
_
፴፬) መነኵሴን ማግባት አይገባም። ከስልሳ ዓመት በላይ የሆናትን ሴት ማግባትም አይገባም።
_
፴፭) ማጨት ቃል ኪዳን መጋባት ነው። ከጋብቻ አስቀድሞ የሚሆን አለኝታ ነው። በደብዳቤም ያለ ደብዳቤም ይሆናል። በእጮኝነት ጊዜ ካህናት እጅ ለእጅ አያይዘው፣ አንድ የሚያደርጋቸውን መስቀል አስጨብጠው፣ አንድ ቀለበት አድርገው በደብዳቤ ይወስኑላቸው።
_
፴፮) ያለ ትልወት፣ ያለ ማጫ ማግባትም ይገባል [ይቻላል]።
_
፴፯) ሰባት ዓመት ላልሞላው ሕፃን ማጨት አይገባም።
_
፴፰) አጭቶ ለማግባት ቀን ያልወሰነ ሰው በሀገር ያለ ቢሆን ሁለት ዓመት ይጠብቁት። ሩቅ ሀገር የሄደ ቢሆን ሦስት ዓመት መጠበቅ ይገባል። በታወቀ ምክንያት የቀረ ቢሆን አራት ዓመት መጠበቅ ይገባል። ከዚህ ያለፈ ቢሆን ግን ለሌላ ማጋባት ይገባል።
_
፴፱) በፈቃዷ የምትኖር ሴት የፈለገችውን መርጣ ማግባት ትችላለች። በእናት በአባቷ ቤት ያለች ከሆነች ግን በቤተሰቦቿ ፈቃድ ይሁን።
_
፵) የሚጋቡ ሰዎች አካለ መጠን ያላደረሱ እናት አባት አሳዳጊ የሌላቸው ድኆች ቢሆኑ ፲፭ ዓመት እስኪሆናቸው ይጠብቁ። ከዚያ የፈቀዱትን ያድርጉ።
_
፵፩) አንዲትን ሴት ከታጨች በኋላ ሌላ ወንበዴ አስገድዶ ቢደፍራት እና ያጫት አልቀጥልም ካለ አስገድዶ የደፈራት ሚስት የሌለው ከሆነ ከወደደችው ሊያገባት ይገባል።
_
፵፪) ወንዶች ፈጽመው አካለ መጠን የሚያደርሱበት 20 ዓመት ነው። ይህም ባይሆን 25 ዓመት ነው። ሴቶች ደግሞ 12 ዓመት ነው። ይህም ባይሆን 15 ዓመት ነው።
_
፵፫) ከተጫጩ በኋላ የአንደኛው ግብሩ ጠባዩ የከፋ መሆኑን ተረድቶ እምቢ ቢል ይችላል። እምቢ ያለች ሴቲቱ ከሆነች ዓረቦኑን እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች። ከሰጠ በኋላ አላገባም ያለ ወንዱ ከሆነ ዓረቦኑ ይቀርበታል።
_
፵፬) ልጁ በንጽሕና እኖራለሁ ካለ አባት ግድ አግባ ማለት አይገባውም።
_
፵፭) 25 ዓመት በላይ የሆናት ሴት ብትኖር አባት እናቷ ከማጋባት ቸል ቢሏት እርሷ ወደ ዳኞች አቤት ማለት ይገባታል። ራሷን የቻለች ከሆነች ግን ራሷ ማግባት ይገባታል።
_
፵፮) ጋብቻ ያለቁርባን አይጸናም።
_
፵፯) ለተጋቢዎች አንድ ልብስ ያለብሷቸዋል፣ ከጣታቸው አንድ ቀለበት ያገቡላቸዋል ጠባብ ከሆነ ፊት እርሱ አግብቶ ለእርሷ ይሰጣታል፣ አንድ መስቀል ያስጨብጧቸዋል። አንድ ዘውድ ይደፉላቸዋል እርሱ ደፍቶ ለእርሷ ይሰጣታል። ከዚያ እርሱ ቆርቦ ልብሱን ለእርሷ ይልክላትና ትቆርባለች። እሷም ከእናት ከአባቷ ቤት እርሱም ከእናት ከአባቱ ቤት ይቆያል። እንዲህ እያሉ ፵ ቀን ከኖሩ በኋላ ሠርግ ያደርጉላቸዋል። ልብስ የልጅነት፣ ቀለበት የሃይማኖት፣ ዘውድ የክብራቸው፣ መስቀል የመከራቸው ምሳሌ ነው።
_
፵፰) ሁለተኛ የሚያገቡ ካህናት ቢሆኑ ከሹመታቸው ይሻሩ። ከዚያ በኋላ ሦስተኛ ካገቡ ግን ርኩሳን ይሆናሉ።
_
፵፱) ሴት ስልሳ ዘመን ከሆናት በኋላ ተመልሳ አገባለሁ ብትል ከምእመናን ትለይ።
_
፶) ንጽሕ ጠብቀን ከሴት ርቀን እንኖራለን ብለው ከተሳሉ በኋላ ዳግመኛ የሚያገቡ ሰዎች ሕግ አፍራሾች ናቸው።
_
፶፩) አግብቶ ለፈታ ሰው መጽሐፈ ተክሊል ማድረስ አይገባም። ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞለት በቁርባን ያገባል እንጂ።
_
፶፪) [ቁጥር ፱፻፮] ከሚጋቡት ሰዎች አንዱ ድንግል ቢሆን ለብቻው ተክሊል ያድርሱለት።
_
፶፫) ከሦስተኛ ጊዜ በላይ ማግባት የታወቀ ዝሙት ነው። ከአራተኛ ግቢ የተወለዱ ልጆች ለክህነት ለርስት አይገቡም።
_
፶፬) ብዙ ሴት ማግባት ዝሙት መውደድ ነው። በአንድ ጊዜ ሁለት ሴት ማኖር ለማንም አይገባውም። ይህን ያደረገ ካለ ግን ሁለተኛይቱን እስኪፈታት ድረስ ሥጋውን ደሙን ከመቀበል ቤተክርስቲያን ከመግባት ይከልከል።
_
፶፭) በሚስቱ ላይ ዕቁባት ያኖረ ካህን ቢሆን ከሹመቱ ይሻር፣ ጨዋ ቢሆን ከምእመናን አንድነት ይለዩት።
_
፶፮) ያመነች ሴት ያላመነውን ወንድ ብታገባ ከምእመናን ትለይ። ከእርሱ ተለይታ ንስሓ ብትገባ ግን ይቀበሏት። ልጁን ለኢአማኒ የዳረ ቢኖር ከምእመናን ይለይ።
_
፶፯) ወንድ ሚስቱ ከሞተች ጀምሮ አንድ ዓመት ሳይሆነው ማግባት አይገባውም። ዓመት ሳይሆነው ቢያገባ ግን ሚስቱ ከተወችው ሊወርሰው ከሚገባ ገንዘብ ሁሉ ይከልከል።
_
፶፰) ሴትም ባሏ ከሞተ ጀምሮ አሥር ወር ሳይሆናት ባል ብታገባ ከገንዘቡ ምንም ምን አትውረስ።
_
፶፱) ሳትሰስንበት ሰነፈች ደረቀች ብሎ ሚስቱን የፈታ ሰው ኃጥዕ ተብሎ ይፈረድበታል። በነውር የተፈታችውንም ንስሓ ሳትገባ ያገባት ሰው ቢኖር ኃጥዕ ተብሎ ይፈረድበታል።
_
፷) ባል ለሚስቱ የሚገባውን ፍቅር ያድርግላት፣ ሴትም ለባሏ የሚገባውን ፍቅር ታድርግለት።
407 views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 12:14:52 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፰__
አንቀጽ ፳፬ ስለ እጮኝነት፣ ስለ ጋብቻ ይናገራል።
፩) የጋብቻ ዓላማ ዘር ለመተካት ልጅ ለመውለድ፣ የፍትወት ጾርን ለማጥፋት እና ለመረዳዳት ነው።
_
፪) ወንድ ከሴት ሄዶ ማጨት ይገባዋል። አኮ መፍትው ትሑር ብእሲት ኀበ ብእሲሀ አላ መፍትው ይሑር ብእሲ ኀበ ብእሲቱ እንዲል።
_
፫) የፍትወት ጾር የጸናበት ሰው ካለ ማግባት ይገባዋል። በፈቲው ጾር ሲነዱ ከመኖር ማግባት ይሻላልና።
_
፬) የፍትወትን ፆር ድል መንሣት የተቻለው ሰው ማግባትን መተው ይገባዋል። ሚስት የሌለው ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝበትን ሥራ ያስባል።
_
፭) ማግባት በኦሪትም በወንጌልም የታዘዘ ነው። አንተ ሰው ሚስት ብታገባ ልፍታት አትበል።
_
፮) በድንግልና እኖራለሁ ብሎ ከተሳለ በኋላ ማግባት እጅግ ያሳፍራል። ኃፍረት ነው። ቢያገባ ግን ሁለተኛ ሚስት እንዳገባ ሰው ፍርድ ይሆናል።
_
፯) በሁለተኛ ግቢ ፍትሐት ዘወልድን ደግመው ያጋቧቸዋል እንጂ ሥርዓተ ተክሊል አይደረግም።
_
፰) ካህናት ሁለተኛ ካገቡ ክህነታቸው ይሻራል። ከሦስተኛ ግቢ በኋላ መጽሐፍ አላዘዘም።
_
፱) በሰው በእንስሳዊ ባሕርዩ የፈቲው ጾር ቢጸናበት ማግባት ይገባዋል። [ቁጥር ፰፻፳፯]። የፈቲው ጾር በሰው ባሕርይ እንደ ጭቃ ተለውሳ እንደ ነሐስ ተንሳ ትኖራለች [ሐተታ ቁጥር ፰፻፴፮]
_
፲) ከቅዱሳን አባቶቻችን ማግባትን ለዝሙት የሚሻ አላገኘንም። ዘእንበለ ለከዊነ ዘርዕ ባሕቲቱ። ልጅ ለመውለድ ብቻ ነው እንጂ።
_
፲፩) ፅንስ ከገፋ ሆድ ከሰፋ በኋላ ወንድ ከሚስቱ የደረሰ ቢሆን ይህ ሥራ የማይገባ ነው።
_
፲፪) የሚያጭ ሰው ራሱ ፈቅዶ ሂዶ ማጨት ይገባዋል። እርሱ ካልሄደ ሽማግሌ ልኮ፣ ወይም ደብዳቤ ሰዶ ማጨት ይገባዋል። ማጫ መስጠት ግን ለአሳዳጊው ወይም ለመጋቢው ይገባል።
_
፲፫) የሥጋ ዘመድን ማግባት አይገባም። መጽሐፍ ካላዘዘው ጋብቻ የተወለዱ አይጋቡ። ማግባት የማይፈቀድባቸው የሥጋ ዝምድናዎች:-
√ የልጅ ልጅ ልጅ
√ የልጅ ልጅ
√ ልጅ
√ እናት፣ አባት
√ አያት
√ ቅድመ አያት
√ አጎት፣ አክስት
√ ወንድም፣ እህት
√ የወንድም ልጆች፣ የእህት ልጆች
፲፬) ሐዋርያትም፣ ሠለስቱ ምእትም ከአራተኛው ትውልድ እና ከዚያ በላይ መጋባትን አልከለከሉም። [እስከ ሰባት ያለው ትውፊት ነው]። ይህንን መክፈል መጨመር ለኤጲስ ቆጶሳት ተገባቸው። ስለሆነም ዓላውያን በዝተው ከሰባት ትውልድ በላይ ባያገኙ ግብፃውያን በአራተኛው ማግባትን ፈቅደዋል።
_
፲፭) በትውልድ አቆጣጠር የአጎት ልጅ አራተኛ ነው። አቆጣጠሩም ፩ኛ አባቴ እኔን ወለደኝ፣ ፪ኛ አያቴ አባቴን ወለደ፣ ፫ኛ አያቴ አጎቴን ወለደው፣ ፬ኛ አጎቴ ልጁን ወለደ ይላል። [ሐተታ] በሀገራችን ግን በአንድ ወገን ሰባት፣ በአንድ ወገን ሰባት ተከልክሎ በስምንተኛው መጋባት ነው።
_
፲፮) በክርስትና ከተዛመዱ በኋላ መጋባት አይገባም። ይህ ዝምድና መንፈሳዊ ዝምድና ይባላል። የሚከተሉትን የሚከለከሉ ጋብቻዎች ናቸው።
√ አንሺ፣ ከተነሺ (ሴት ወንድን ብታነሣ)
√ ባል የሚስቱን ክርስትና ልጅ፣
√ ሚስት የባሏን ክርስትና ልጅ፣
√ የአንሺ እናት አባት ከተነሽ እናት አባት፣
√ የአንሺ ወንድም ከተነሽ ወንድም፣
√ የአንሺ ልጅ ከተነሽ ልጅ፣
√ የአንሺ የሚስት ልጅ ከተነሽ የሚስት ልጅ፣
፲፯) ሴት ከሌላ የወለደቻት ልጇን ባሏ ክርስትና ላነሣው ልጁ ማጋባት አይገባትም። ወንዱም ቢሆን ከሌላ የወለዳት ልጁን ሚስቱ ክርስትና ላነሣቸው ልጅ ማጋባት አይገባውም።
_
፲፰) መንፈሳዊ ዝምድናን ያፈረሰ ቀኖናው ሚስቱን ፈትቶ ምንኵስና ነው።
_
፲፱) በማሳደግና በማደጎ ከተዛመዱ በኋላ መጋባት አይገባም። የሚከተሉት የሚከለከሉ ጋብቻዎች ናቸው።
√ አሳዳጊ ከአዳጊ ጋር፣
√ የአሳዳጊ ልጅ ከአዳጊ ጋር፣
√ የአሳዳጊው ልጅ ከአዳጊ ልጅ ጋር፣
√ የአሳዳጊ እናት አባት ከአዳጊ እናት አባት፣
√ የአዳጊ አያት ከአሳዳጊ አያት፣
√ የአዳጊ አክስት አጎት ከአሳዳጊ አክስት አጎት
፳) በጋብቻ ከተዛመዱ በኋላ መጋባት አይገባም። የሚከተሉት የሚከለከሉ ጋብቻዎች ናቸው።
ልጅ የአባቱን ሚስት፣ ልጅ የእናቷን ባል፣
የልጅ ልጅ የአያቱን ሚስት/ባል፣
ልጅ የአባቱን ሚስት እኅት፣
የልጅ ልጅ የአያቱን ሚስት እኅት፣
ልጅ የአባቱን ሚስት እናት፣
የልጅ ልጅ የአያቱን ሚስት እናት፣
ልጅ የአባቱም ሚስት አያት፣
የልጅ ልጅ የአያቱን ሚስት አያት፣
አባት የልጁን ሚስት፣
አያት የልጅ ልጁን ሚስት፣
አጎት የወንድሙን ልጅ፣
ወንድም የወንድሙን ልጅ፣
አባት የልጁን ሚስት እኅት፣
አያት የልጅ ልጁን ሚስት እኅት፣
አባት የልጁን ሚስት እናት፣
አያት የልጅ ልጁን ሚስት እናት፣
አባት የልጁን ሚስት አያት፣
አያት የልጅ ልጁን ሚስት አያት፣
ወንድም የወንድሙን ሚስት፣
አጎት የወንድሙን ልጅ ሚስት፣
ወንድም የወንድሙን ሚስት እኅት፣
አጎት የወንድሙን ልጅ ሚስት እኅት፣
ወንድም የወንድሙን ሚስት እናት፣
አጎት የወንድሙን ልጅ ሚስት እናት፣
ወንድም የወንድሙን ሚስት አያት፣
አጎት የወንድሙን ልጅ ሚስት አያት
ባል የሚስቱን ዘመዶች
፳፩) የጌታ ሚስት ባሏ ነጻ ያወጣውን ባሪያ ማግባት አይገባትም። [ሐተታ] ልጇን ማግባት ነውና።
_
፳፪) በሃይማኖት የማይመስለንን/የማትመስለንን ማግባት አይገባም።
_
፳፫) አባለ ዘሩ ሩካቤ ማድረግ የማይችል ወንድ ማግባት የለበትም። ፈናፍንታምም ማግባት የለበትም። ፈናፍንት ማለትም የወንድና የሴት አካል ያለው ነው። የሚጠመቅበት ቀን የሚሸናበት ጾታ ታይቶ ይሆናል። በወንድ አካሉ የሚሸና ከሆነ በ፵ ቀኑ፣ በሴት ከሆነ በ፹ ቀኗ ትጠመቃለች።
_
፳፬) ሴት ልጅ በማኅፀኗ ሩካቤን የሚከለክል አፅም ካለባት ማግባት አይገባትም።
423 views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 06:30:31 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፯__
አንቀጽ ፳፫ ለክርስቲያኖች ስለሚገቡ ምግቦች፣ ልብሶች፣ ስለ ቤት እና ስለ ተግባረ እድ ይናገራል።
፩) በወንጌል የተከለከሉ ምግቦች ደም፣ ጥሬ ሥጋ፣ ታንቆ የሞተውን፣ ለጣዖት የተሠዋውን፣ የአውሬውን ትራፊ፣ ሙቶ የተገኘውን፣ ሲያርዱ አንገቱን ቆርጠው የጣሉትን ናቸው። ለጣዖት የተሠዋውን አትብሉ የተባለበት ምክንያት ምእመናን ወደ ጣዖት አምልኮ እንዳይሳቡ ነው።
_
፪) ርኵስ ፍጥረት እንደሌለ እግዚአብሔር የፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ንጹሕ እንደሆነ ተጽፏል። መጽሐፍ ከከለከለው በቀር ከምግብ ሁሉ እንዳንከለከል መሆን ይገባናል።
_
፫) አእምሮ ወደማጥፋት የሚያደርስን ምግብ፣ አራቱን ባሕርያትን የሚያነዋውጽን ምግብ፣ አካል የሚያጎድልን ምግብ መብላት አይገባም። ይኽውም መርዝ እንዳላቸው እንስሳትና እፀዋት ያሉትን ነው።
_
፬) አትብሉት ከተባለው የምግብ ወገን ደህነኛውን የሚገድል ድውዩን የሚፈውስ ቢሆን ደህነኛው ከመብላት ይከልከል። ድውዩ ግን የሚያድነው ከመሆኑ የተነሣ መብላት ይገባዋል።
_
፭) ሁሉን ሊበሉት እንዲገባ የሚያምን ሰው ሁሉን ይብላ። የሚጠራጠር ሰው ግን እህል ይብላ። ሁሉን የሚበላ አረማዊም ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊን ሃይማኖተ ግብዝ ብሎ አይንቀፈው። ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊም ሁሉን የሚበላ አረማዊን ይህ ሁሉ በአፌ ብሎ አይንቀፈው።
_
፮) ለሰው ክፉ ነገር እየተጠራጠሩ መብላት ነው። በሃይማኖት የማይሠራው ሥራ ሁሉ ኃጢአት ነው። ለጣዖት የተሠዋውንኳ አምነው ቢበሉት ጉዳት አያመጣም።
_
፯) በመብል ምክንያት ወንድምህ የሚጎዳ ከሆነ የተፈቀደውን እንኳ ስለእርሱ ብለህ አትብላ።
_
፰) በገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ብሉ። ፍጥረቱ ሁሉ የእግዚአብሔር ገንዘብ ነውና። እያመሰገኑ ቢቀበሉት ሁሉም በስመ እግዚአብሔር ይከብራል።
_
፱) ካላመኑ ሰዎች ወገን የጠራችሁ ሰው ቢኖር እና ልትሄዱ ብትወዱ ሳትመራመሩ ያቀረቡላችሁን ሁሉ ብሉ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ግን አትብሉ።
_
፲) በቀለም ያስጌጧቸውን ልብሶች ከመልበስ መጽሐፍ ከለከለ። ቤተመቅደስ ገብተው እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ የሚለብሱት ልብስ ነጭ ሊሆን ይገባል።
_
፲፩) ሴቶች የወንድ ልብስ አይልበሱ አለ። እጀ ሰፊ ቀሚስ፣ ሱሪ አይታጠቁ። አርዓያ መለወጥ ሥርዓት ማፍረስ ነውና። ወንዶችም የሴቶችን ልብስ አይልበሱ። ይኽውም እጀ ሰብስብ ቀሚስ አይልበሱ።
_
፲፪) ወንዶች ከጣታቸው ቀለበት አያግቡ የምንዝር ጌጥ ነውና። ሴቶች በወርቅ የተጌጠ የሚያስመካ ልብስ አይልበሱ። ሹማምንት ግን ያጌጠ ልብስ ቢለብሱ ይገባቸዋል።
_
፲፫) መነኮሳት ከፀምር ወገን ደጓሳ ልብስ ይልበሱ።
_
፲፬) ማንኛውም ሕዝብ የወደደውን መልበስ ይገባዋል። ዘመን ያስገኘውን መልበስ ዘመን ባስገኘው ማጌጥ ይገባቸዋል። ከሕዝባውያን ወገን ብዙዎቹ ሰዎች ያገኙትን መልበስ ይገባቸዋል።
_
፲፭) ካህናት የወታደር ልብስ አይልበሱ። ካህናት የአናፂ ልብስን አይልበሱ።
_
፲፮) ወጠቢብኒ ቅዱስ ባስልዮስ ይቤ ይደሉ ለነ ከመ ንሥራዕ ልብሰነ በዘንከድን ዕርቃነነ። ዕርቃናችንን እንሠውር ዘንድ ልብስ መሻት ይገባናል። ወንድኃን እምቍር ወዋዕይ። ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር ለመዳን ልብስ ያስፈልጋል [ቁጥር ፰፻፲፬]።
_
፲፯) ለሚኖሩበት ሰዎች ይጠቅም ዘንድ፣ ይሠውራቸው ዘንድ፣ ምግባቸውን ንብረታቸውን ያስቀምጡበት ዘንድ፣ ይሰበሰቡበት ዘንድ፣ ቤት መሥራት ይገባል።
_
፲፰) ጌታ ለወልደ እጓለ እመሕያውሰ አልቦቱ ኀበ ያሰምክ ርእሶ ተብሎ እንደተነገረው ቤት እንዳልነበረው ሁሉ ለባሕታውያንም በዚህ አብነት ቤት የላቸውም።
_
፲፱) የእንግዳ መቀበያ ይሆን ዘንድ ቤት ያስፈልጋል።
_
፳) ከሥራይ፣ ከጥንቆላ፣ ጣዖትን ከመሥራት፣ ከመዝፈን፣ ከተውኔት በስተቀር ክርስቲያን ሥራን ሁሉ መሥራት ይገባል።
_
፳፩) አንጥረኛ ሁሉ ጣዖት ከመሥራት ይከልከል። ከአመነ ከተጠመቀ በኋላ ይህን የሚያደርግ ቢኖር ንስሓ ይግባና ይተወው።
_
፳፪) ለጣዖት በገና የሚደረድር፣ የሚዘፍን ቢኖር በቀኖና ይለይ። ያም ባይሆን በውግዘት ይለዩ።
_
፳፫) ለክርስቲያኖች የሚገቡ ሥራዎች ግብርና፣ ማስገር፣ ልብስ መስፋት፣ ልብስ መሥራት፣ ቤት መሥራት፣ ሕክምና፣ አንጥረኝነት፣ ጠራቢነት፣ ጸሓፊነት፣ እንጀራ ጋጋሪነት ወጥ ሠሪነት፣ መምህርነት፣ ነጋዴነት፣ መርከብ መሥራት እና የመሳሰሉት ናቸው። ንግድ ከአንዱ ሀገር ያለውን ወደ አንዱ ሀገር ለመውሰድ በግድ ያለውድ ያሻል [ቁጥት ፰፻፳፬]።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፰ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.5K views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 16:55:37
ውድ ክርስቲያኖች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ
1.6K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 13:48:09 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፮___
አንቀጽ ፳፩ ስለ ድውያን (በሽተኞች) ይናገራል።
፩) የታመመ ሰው ቢኖር ይጸልዩለት ዘንድ ቀሳውስትን ይጥራ። በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ይቀቡት ዘንድ። አምነው የሚጸልዩት ጸሎት የታመመውን ሰው ያድነዋልና። ኃጢአትም ቢኖርበት ይሠረይለታል።
_
፪) ቀሳውስት ለሕሙማን መጽሐፈ ቀንዲልን እየደገሙ ይቀቧቸው። የታመመን መጠየቅ በምጽአት ጊዜ በቀኝ የሚያስቆም ግብር ነው።
_
አንቀጽ ፳፪
አንቀጽ ፳፪ ስለሙታን ይናገራል።
፩) ሰው ሲሞት ያለ ሀኬት ወደ ቤተክርስቲያን ተሰብሰቡ። ክቡራት መጻሕፍትን አንብቡ። ስላረፉ ሰዎች ዳዊት ድገሙ።
_
፪) ግንዘት ዘሰማዕታት፣ ግንዘት ዘአበው፣ ግንዘት ዘወራዙት፣ ግንዘት ዘሕፃናት፣ ግንዘት ዘአንስት፣ ግንዘት ዘመነኮሳት፣ ግንዘት ዘመምህራን አለ። መዋቲ ሕያውን እኔ እንደእናንተ ነበርኩ እናንተም እንደ እኔ ትሆናላችሁ መሰናበት ይገባዋል። ሕያው መዋቲውንም ሊሰናበት ይገባዋል።
_
፫) ስላረፉ ሰዎች ዳዊት ድገሙ፣ በቤተክርስቲያን መሥዋዕት ሠውላቸው። ዕጣን አቅርቡላቸው። በክርስቶስ አምኖ ለሞተ ክቡር ሞቶሙ ለጻድቃኒሁ በቅድመ እግዚአብሔር፣ ግብኢ ነፍስየ ውስተ ዕረፍትኪ እስመ እግዚአብሔር አሠነየ ለኪ እያልን እንዘምርለታለን።
_
፬) በእግዚአብሔር አምነው የሞቱ ሰዎች ሞተ ነፍስ የለባቸውም። በእግዚአብሔር አምነው የሞቱ ሰዎች አጽማቸው የተናቀ ርኵስ አይደለም። የሞቱ ሰዎችን በድን አጥበን ገንዘን እንቅበር።
_
፭) ሴት በወሊድ በኅርሷ ወራት በሞተች ጊዜ በአራስነቷ ወራትም ብትሞት አጥበው ባልወለደችበት ልብስ ገንዘው ከቤተ እግዚአብሔር አግብተው ይጸልዩላት።
_
፮) ሳይገንዙ መዋቲውን ማጠብ ይገባል። ጴጥሮስ ያነሳት ጣቢታን ከሞተች በኋላ አጥበዋት ነበርና።
_
፯) መዋቲው ካህን ቢሆን ከቤተ መቅደስ አግብተው በታቦቱ ፊት ያሰግዱት። ሟቹ ሕዝባዊ ቢሆን ከቅድስት ከቅኔ ማኅሌት አግብተው ያሰግዱት
_
፰) መዋቲን በመዓርግ በዕድሜ እንደእርሱ ያሉ ሰዎች በተቀበሩበት በክቡር ቦታ ይቅበሩት።
_
፱) ስለሞቱ ሰዎች ተዝካር አድርጉላቸው።
√ በዕለቱ
√ በሦስተኛው ቀን
√ በሰባተኛው ቀን
√ በዘጠነኛው
√ በአሥራ ሁለተኛው
√ በአሥራ አራተኛው
√ በሠላሳው
√ በአርባው
√ በስልሳው
√ በሰማንያው (መጽ. ግንዘት)
√ በመንፈቅ
√ በዓመቱ
ዕለት የሁሉ ነው። በሣልስት ቢታጎል በሦስተኛው ሣልስት በዘጠነኛው ቀን ያስቆርቡለት። በሰባት ቢታጎል በሁለተኛው ሱባዔ በአሥራ አራተኛው ቀን ያስቆርቡለት። አሥራ ሁለት የሁሉ ነው። ሠላሳው ቢታጎል በሁለተኛው ሠላሳ በስሳ ቀን ያስቆርቡለት። በአርባ ቢታጎል በሁለተኛው አርባ በሰማንያ ያስቆርቡለት። በመንፈቅ ቢታጎል በዓመት ያስቆርቡለት ማለት ነው።
_
፲) መታሰቢያ ሊሆነው ከሟች ገንዘብ ለነዳያን ስጡ መጽውቱ። ከተቻላቸው 40ውን ቀን ሁሉ ያስቆርቡለት።
_
፲፩) ሲገንዟቸው ባሕታውያንን እጃቸውን ከዓይናቸው ላይ ጥለው ይገንዟቸዋል። ቀሳውስትን እጃቸውን አመሳቅለው ይገንዟቸዋል። ዲያቆናትን እጃቸውን ከአንገታቸው ላይ ጥለው ይገንዟቸዋል። ሕጋውያንን እጃቸውን ከአባላ ዘርዓቸው ላይ ጭነው ይገንዟቸዋል።
_
፲፪) መቃብር ስለሚቆፍሩ ሰዎች ዋጋቸውን ከመስጠት አንዱስ እንኳ ቸል አይበል። መቃብሩን ለሚቆፍሩት፣ መቃብሩን ለሚጠብቁት ሰዎች ዋጋቸውን ይስጧቸው። ኤጲስ ቆጶሱ ለቤተክርስቲያን ከሚሠጠው ገንዘብ ይመግባቸው።
_
፲፫) ስለሞቱ ሰዎች የቀቢጸ ተስፋ ኀዘን እንደሚያዝኑ አሕዛብ ልናዝን አይገባንም። ካህን ከዘመዶቹ አንዱ ቢሞትበት ልብሱን አይቅደድ፣ ዘወትር ዬ ዬ ብሎ አያልቅስ፣ ራሱን አይላጭ ፊቱን አይንጭ፣ እግዚአብሔርን ፈጽሞ ያመስግነው እንጂ።
_
ፍትሕ መንፈሳዊ ተፈጸመ
አነሳስቶ ላስጀመረን
አስጀምሮም ላስፈጸመን
ልዑል እግዚአብሔር
ምስጋና ይገባል አሜን
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
መ/ር በትረማርያም አበባው።

__ፍትሐ ነገሥት የፍቅር ሕግ ነው_
እነሆድ አምላኩ ጹሙ ሲባሉ የተጨቆኑ ይመስላቸዋል። ሰነፎች ጸልዩ ሲባሉ ጭቆና ይመስላቸዋል። አንዳንዶች ፍትሐ ነገሥትን እንደ ጨቋኝ አድርገው ሲያቀርቡ ሳይ አዝናለሁ። ፍትሐ ነገሥት አካሏ ፍቅር ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት ቅድስት ቤተክርስቲያንን ሥርዓት የሚናገር መጽሐፍ ነው። ፍትሐ ነገሥትን ጨምሮ ሌሎችም ቅዱሳት መጻሕፍት መሠረታቸው ክርስቶስ ነው። በጠቅላላው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ጠባብ በር ናት። በሥርዓት በመንፈስ የሚመሩባት ናት እንጂ በሥጋ ፍላጎት የምትመራ አይደለችም። የልቆች ሃይማኖት አይደለችም። ሑሩ እንተ ጸባብ አንቀጽ እንዳለ ክርስቶስ። ቅዱሳን ሊቃውንት በመንፈስቅዱስ መሪነት የሠሩልን ሥርዓት ነው።

ሥርዓት እንደየዘመኑ ሊቀየር ይችላል የምትለዋን ብቻ ይዞ በራስ ፈቃድ ለመቀየር የሚፈልጉ ትንንሽ ሰዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል። በዚህ ሥርዓት ቤተክርስቲያን ከ1600 ዓመታት በላይ ስትመራበት ቆይታለች። ለመሆኑ አሁን ይህንን ለመቀየር የሚያበቃ ምን ምክንያት ተገኝቶ ይሆን!? ሠለስቱ ምእት ለዘመናቸው ምእመናን ይህንን ከሠሩ በአሁኑ ዘመን ያሉ ምእመናን በዚያ ዘመን ካሉ ምእመናን በምን ያንሳሉ? የፍትሐ ነገሥቱን ሥርዓት እንዳንፈጽም የሚያደርገን ምን ምክንያት ተገኘ!? በእርግጥ ፍትሐ ነገሥቱ ደረቴ ይቅላ ሆዴ ይሙላ ለሚሉ ሰባክያን አይመችም። ታዲያ ፍትሐ ነገሥቱን ወደእነዚህ ሰዎች ስሜት ማውረድ ይገባል ወይስ ሰዎችን ወደፍትሐ ነገሥት ሥርዓት ከፍ ማድረግ!?

እስኪ ከፍትሐ ነገሥት ከባድ ነው የምትሉት ሥርዓት አንድ ጥቀሱ!? እውነት ከባድ ሆኖ ነው ወይስ ለሥጋ ስላልተመቸ!? ለሥጋ የሚመች ሥርዓት ፈልጋችሁ ነው ይሆን!? ጾም የከበደው ሰው ስለ ሰማዕትነት ለማስተማር ምን ሞራል አለው?? ንጉሥ የወደደውን ዘመን ያነሣውን የሚል ሰባኪ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ለመስበክ ምን ሞራል ይኖረዋል!? እንደ ጳውሎስ መኑ የኀድገነ ፍቅሮ ለክርስቶስ ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል! ተሰዶኑ መጥባሕትኑ ረኀብኑ ለማለትኮ የበቃ አይደለም። ትክክለኛ ሰባኪ ክርስቶስ ለሰበከው እውነትና ፍቅር ይኖራል እንጂ በአድርባይነትና በአጨብጫቢነት እውነትን አይጨቁናትም። ለእውነት ይኖራል። እውነትን ይዞ ይሞታል እንጂ ስለሰው ብሎ እግዚአብሔርን አይክድም።

ፍትሕ ሥጋዊን ከበዓል በኋላ እንማማረዋለን። ውድ ክርስቲያኖች መልካም በዓል ይሁንላችሁ።
1.6K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:20:53 _
፱) በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ደማቸውን ስላፈሰሱ ሰዎች ሁሉ በአረፉባት ቀን መታሰቢያ ያድርጉላቸው። የሰማዕታት መቃብር በቤተክርስቲያን ዙሪያ ይሁን። አንድም በቅድስት ይሁን። ቤተክርስቲያን በሰማዕታት አፅም የምትከብር ሆና አይደለም። ሰማዕታት ከቤተክርስቲያን ክብርን ያገኛሉ እንጂ። ቤተክርስቲያን ክብር አላትና።
_
፲) የሰማዕታት ገድላቸው ታሪካቸው ሰማዕት በሆኑባት ዕለት ይነበብ።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፮ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
2.2K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:20:52 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፭__
አንቀጽ ፲፱ ስለ ዕለተ እሑድና ስለ ቅዳሜ እንዲሁም ስለበዓላተ እግዚእ ይናገራል።
፩) ክርስቲያኖች እንደ አይሁድ በዕለተ ቀዳሚት ሥራ ፈትተው መዋል አይገባቸውም። በዕለተ ቀዳሚት እንደ ክርስቲያን ሥራ ይሥሩ እንጂ። (ሐተታ) የታመመ መጠየቅ፣ የሞተ መቅበር ይገባልና።
_
፪) በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቅዳሜ፣ በክቡራን በዓላት ስግደት አይገባም። የተድላ የደስታ ዕለታት ናቸውና። ይህ አንቀጽ ውግዘት የሌለበት ነው። ባሕታዊ ፆር ተነስቶበት ቢሰግድ ዕዳ የለበትምና።
_
፫) በዕለተ እሑድ ፍርድ ቤት አይሂዱ። እሑድ ቀን አያሟግቱ አያፋርዱ። በእሑድ ቀን ማንም ማን ገንዘቤን አምጣ ብሎ አይያዝ። ሁሉም ወደ ቤተክርስቲያን ይሂዱ እንጂ። ምእመናንም ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን፣ ኤጲስ ቆጶስ አሥራት በኩራት፣ ነጋድራስ ቀረጥ አምጡ ይለናል ብለው ሳይፈሩ በንጽሕና በትህትና ሁነው ወደ ቤተክርስቲያን ይምጡ።
_
፬) በዕለተ እሑድ ከነጋድራሶች አንዱስንኳ ወደቤተክርስቲያን ከሚሄዱ ሰዎች ቀረጥ ይቀበል ዘንድ የድፍረት ሥራ የሠራ ቢሆን እጥፍ አድርጎ ይክፈል።
_
፭) ሁልጊዜ በቤተክርስቲያን ተሰብሰቡ። ይልቁንም በዕለተ እሑድና በዕለተ ሰንበት እንዲሁም በጌታ በዓላት ወደ ቤተክርስቲያን ተሰብሰቡ።
_
፮) ጥቅም የሌለው ነገር አትናገሩ። የማይገባ ሥራም አትሥሩ።
_
፯) ባሮች (የቤት ሠራተኛዎች) አምስቱን ቀን ሠርተው ቅዳሜና እሑድ ግን የእግዚአብሔርን አንድነቱን ሦስትነቱን ይማሩ ዘንድ ከቤተክርስቲያን ሆነው ይዋሉ።
_
፰) ቅዳሜ መከበሯ ጌታ ፍጥረትን ከመፍጠር አርፎባታልና ነው። እሑድ መከበሯ ደግሞ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶባታልና ነው።
_
፱) የጌታ ዐበይት በዓላት የሚባሉት የሚከተሉት ናቸው (ዐቢይነታቸው በአከባበራቸው ነው):-
√ በዓለ ጽንሰት (ትስብእት) መጋቢት ፳፱
√ በዓለ ልደት (ታኅሣሥ ፳፱)
√ በዓለ ጥምቀት (ጥር ፲፩)
√ በዓለ ሆሣዕና
√ በዓለ ትንሣኤ
√ በዓለ ዕርገት
√ በዓለ ጰራቅሊጦስ
√ በዓለ ደብረ ታቦር (ነሐሴ ፲፫)
√ በዓለ ስቅለት
፲) የጌታ ንዑሳት በዓላት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው
መስቀል (መስከረም ፲፯ & መጋቢት ፲)
ስብከት
ብርሃን
ኖላዊ
ጌና (ታኅሣሥ ፳፰)
ግዝረት (ጥር ፮)
ልደተ ስምዖን (የካቲት ፰)
ደብረ ዘይት
ቃና ዘገሊላ (ጥር ፲፪)
፲፩) የልደትና የጥምቀት ቁርባን በመንፈቀ ሌሊት ይሁን። ይኽውም ስለ ክብረ በዓሉ ነው።
_
፲፪) የትንሣኤን በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ አታክብሩ። እኛን ለማዳን አንድ ጊዜ ስለሞተ በዓመት አንድ ጊዜ አክብሩ እንጂ። የትንሣኤን በዓል በዕለተ እሑድ እንጂ በሌላ ቀን አታክብሩ። በዶሮ ጩኽት ብሉ። ያም ባይሆን በነግህ ብሉ።
_
፲፫) መዓርገ ቁርባን አምስት ናቸው። እነዚህም:-
√ የትንሣኤ፣የልደት፣የጥምቀት ሌሊት በ፲ ሰዓት
√ በዓለ ኃምሳ እና ቅዳሜ ጠዋት ፫ ሰዓት
√ እሑድ ጠዋት ፩ ሰዓት
√ በሰባቱ አጽዋማት በ፱ ሰዓት
√ የጸሎተ ኃሙስ በሠርክ (፲፪ ሰዓት)
፲፬) በበዓላት ጊዜ በቤተክርስቲያን ተሰብስባችሁ መጻሕፍተ ነቢያትን ኦሪትን እያነበባችሁ፣ ዳዊት እየደገማችሁ አቡነ ዘበሰማያት እያላችሁ ጸልዩ። ለምእመናኑ ሊድኑበት የሚገባውን ንገሯቸው።
_
፲፭) ከትንሣኤ በኋላ በስምንተኛው ቀንም በዓል አክብሩ (ዳግማይ ትንሣኤን ነው)።
_
፲፮) ከሰሙነ ሕማማት እስከ ሰሙነ ትንሣኤ (እስከ ዳግማይ ትንሣኤ) አንድ በዓል ነውና ሥራ አትሥሩ።
_
፲፯) ሐዋርያት ባረፉበት ቀን ሥራ አትሥሩ። ሐዋርያት ክርስቶስን ለማወቅ ያስተማሯችሁ መምህሮቻችሁ ናቸውና። ሀብተ መንፈስቅዱስንም ለመቀበል አብቅተዋችኋልና።
_
፲፰) የተቻለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶድ በሰውነቱ መከራ የተቀበለባቸውን መካናት እጅ ይንሣ። የተነሣበትንም ቦታ ይይ። አምላክ በሠራቸው ግብራት ይከብር ዘንድ። (ሐተታ) መካነ ልደቱን አይቶ በረከተ ልደቱን፣ መካነ ጥምቀቱን አይቶ በረከተ ጥምቀቱን፣ መካነ ትንሣኤውን አይቶ በረከተ ትንሣኤውን ያገኛልና። ለመሄድ የማይቻለው ግን መብዓ ይስደድ። በዚያው የሚኖሩ ሰዎች ይረዱበት ዘንድ።
_
አንቀጽ ፳
አንቀጽ ፳ ስለ ሰማዕታት ይናገራል።
፩) ሰማዕታት በእናንተ ዘንድ የከበሩ ይሁኑ። በጌታ ስም ስላመነ በሃይማኖት ስለፀና ወደ መከራ ሥጋ የሚያገቡት ክርስቲያናዊን ከመርዳት ቸል አትበሉ። ምንም የሌላችሁ ብትሆኑ እንኳ ስለእነርሱ እናንተ ግማሽ እየበላችሁ የምግባችሁን ግማሽ ስጧቸው።
_
፪) ሰማዕታት የክርስቶስ የመከራው ተሳታፊዎች፣ የመንፈስቅዱስ ማደሪያዎች ናቸው። የሰማዕታት ምስክራቸው ክርስቶስ ነው። ሰማዕታትን ከሚረዳቸው ሰዎች አንዱን መከራ ቢያገኘው ንዑድ ክቡር ይባላል። የሰማዕታት የመከራቸው ተባባሪ ሆኗልና። ክርስቶስን መስሎታልና።
_
፫) ሃይማኖት አንለውጥም ስላሉ ከሀገር አስወጥተው የሚሰዷቸውን (የሚያሳድዷቸውን) ተቀብላችሁ ከረኀብ ከጥም አሳርፏቸው። በተቀበላችኋቸው ጊዜ ደስ ይበላችሁ።
_
፬) ጌታ በዚህ ዓለም መከራ ኀዘን ያገኛችኋል ብሎናል። እስከመጨረሻው የጸና እርሱ ይድናል። ከእግዚአብሔር ይልቅ ራሱን የወደደ ሰው ይቅርታውን አያገኝም። የሰው ወዳጅ የእግዚአብሔር ጠላት ሊሆን ወዷልና።
_
፭) ሥጋችሁን የሚገድሉትን ሰዎች አትፍሯቸው። ነፍሳችሁን ግን መግደል አይቻላቸውም። ይህንን ዓለም አትውደደው። በሰው መመካትን ተው። ከአለቆች ውዳሴ ከንቱን አንቀበል።
_
፮) ለሌሎች ሰዎች የክህደት አብነት እንዳንሆን ወንድሞቻችንን በሃይማኖት በምግባር እናጽናቸው። በመከራ ብንጨነቅ በኃላፊው ዘመን የሚሆነውን መከራ ፈርተን ሃይማኖታችንን አንለውጥ።
_
፯) ሰው አምኖ ሳይጠመቅ መከራ ቢደርስበት አይዘን። በክርስቶስ ስም አምኖ የተቀበለው መከራ የተወደደ ጥምቀት ይሆንለታልና። እስመ ተጠምቀ በደሙ (ለክርስቶስ) እንዲል።
_
፰) ዓላውያንን ፈርቶ በግድ የካደ ሰው ቢኖር በኋላ ንስሓ ቢገባ ንስሓውን ይቀበሉት። ካህን ከሆነም ቅዳሴ ከመግባት አይከልከል። ይህን ወዶ አላደረገውምና። መከራ ሳያጸኑበት ገንዘቡን ሳይወስዱበት ፈርቶ አስቀድሞ የካደ ቢኖር ብዙ ዘመን በንስሓ ይኑር። ከዚያ በፍጹም ልቡናው ቢመለስ ሥጋውን ደሙን ሊቀበል ቢወድ ያቀብሉት።
2.2K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 09:01:09 _
፰) ጉልት ፍጽምት የሆነች ምጽዋት ናት። በዚህ ዓለምም በሚመጣው ዓለምም ዋጋን ታስገኛለች።ለቤተክርስቲያን ጉልት መጎለት መልካም ነው።
_
፱) የሚጎለተው ጉልት ለሚጎለትላቸው ሰዎች እየኖረ ጥቅም የሚገኝበት ሊሆን ይገባል። ጉልት ዘወትር የሚኖር መሆን አለበት። ይኽውም ምሳሌ የእርሻ ቦታ፣ ቤት፣ አዝርዕት አትክልት ያሉበት ቦታ ወዘተ ይሁን። ባሮችን፣ ከብቶችን፣ ንብ ወዘተ መጎለት አይገባም። እነዚህ ሁሉ ዘወትር አይኖሩምና።
_
፲) የሚጎልተው ሰው ከገንዘቡ የሚያዝበትን እንጂ የማያዝበትን መጎለት አይገባውም። የሚጎልት ሰው አካለ መጠን ያደረሰ፣ አዋቂ፣ ራሱን የቻለ፣ በልቡ በጎ ነገርን የሚያስብ ሊሆን ይገባል። የሚጎልቱለት ሰውም ሃይማኖት ከምግባር ያለው ሊሆን ይገባል።
_
፲፩) የተጎለተለት ሰው ከጉልቱ ምንም ምን አይሽጥ። ሩቅ ሀገር ለሄደ ሰው ጉልት ቢጎለትለት መታጣቱ (መሞቱ) ቢታወቅ ለእርሱ የታዘዘው ጉልት ለቤተክርስቲያን ይግባ። የተቸገሩ ሰዎች ይረዱበት ዘንድ።
_
፲፪) ጥቅም የሚገኝበት ሥርዓት ቢፈርስ መልሶ ሊያጸኑት ይገባል።
_
፲፫) ጎላቹ ቢቸገር ከጉልቱ ከርቦው ከአምሾው ሊሰጡት ይገባል።
_
፲፬) የሚጎለተው ጉልት የንጉሥ ግብር ያለበት መሆን የለበትም።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፭ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
2.2K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 09:01:09 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፬__
አንቀጽ 16 ስለ ምጽዋት ይናገራል።
፩) ምጽዋት ከርኅራኄ ወገን የሚሆን ርኅራኄ ነው። ይኽውም ሰው አበድሬ እቀበላለሁ ሳይል በገንዘቡ የሚያደርገው ርኅራኄ ነው።
_
፪) ምጽዋት የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ ድልብ ነው። የተቻለውን ያህል በመስጠት ሰው ፈጣሪውን ይመስላል። የጌታ የባሕርይ የሰው የጸጋ ነውና።
_
፫) ምጽዋት ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያኖራት የብልህ አደራ ናት።
_
፬) ለለመነህ ስጠው። ለሰው የሚያዝኑ የሚራሩ ሰዎች ንዑዳን ክቡራን ናቸው። ለእነርሱም ሥላሴ ይራሩላቸዋልና። ጌታ በምጽዋት ለሰው ለሚራሩ ሰዎች ንዑ ኀቤየ ብሎ ወደ መንግሥተ ሰማያት ያስገባቸዋል።
_
፭) ለተቸገሩ፣ ለተራቡ፣ ለተጠሙ፣ ለታረዙ፣ ለእንግዶች፣ ለታመሙ፣ በሃይማኖታቸው ምክንያት ለታሠሩ፣ በሃይማኖታቸው ምክንያት ለተሰደዱ ሊመጸውቱ ይገባል። እንግዳ መቀበል ከምጽዋት ወገን ነው።
_
፮) አሥራቱን፣ በኩራቱን፣ ስለቱን እግዚአብሔርን ለሚያገለግሉ ካህናት ከፋፍለው ይስጧቸው።
_
፯) በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን ታገኙ ዘንድ፣ አሥራቱን፣ ስለቱን፣ እጅ መንሻውን፣ መጀመሪያ የደረሰውን እህል (ቀዳምያቱን) ስጡ። በረከት በሚመጸውት ሰው አትጠፋምና።
_
፰) ምጽዋት መጀመሪያ ሃይማኖታችንን አንክድም ብለው ለታሠሩ ሰማዕት ትገባለች። ከዚህ ቀጥሎ ለካህናት፣ ከዚያ ቀጥሎ ለዘመድ፣ ከዚያ ቀጥሎ ለምእመናን፣ ከዚያ ቀጥሎ ላላመኑ ሰዎች ትገባለች።
_
፱) ምጽዋትን ለተቸገረ ሁሉ ሊሰጧት ትገባለች። እግዚአብሔር ለኃጥአንም ለጻድቃንም ዝናምን እንደሚያዘንብ።
_
፲) ተመጽዋቾች ምጽዋቱን ስለ ሰጧቸው ሰዎች መጸለይ ይገባቸዋል። አብዝቶ ይጸልይላቸው።
_
፲፩) ያልተቸገሩ ሰዎች ምጽዋት መቀበል አይገባቸውም። እየተቻለው ምጽዋት የማይሰጥ ሰው እንደ ከሓዲ፣ እንደ ወንበዴ፣ እንደ ሌባ ነው።
_
፲፪) ምጽዋት ከኃጢአት ታነጻለች። ከመቅሠፍትም ታድናለች። ምጽዋት መስጠት እጥፍ ድርብ ዋጋን ያስገኛል።
_
፲፫) ምጽዋትን ከሰጡ በኋላ መጸጸት አይገባም። (ጸጸትን እንዳያመጣ አስቦ መስጠት ይገባል)።
_
፲፬) ምጽዋት የሚሰጥ ሰው በሚሰጠው ሰው ላይ መታበይ የለበትም።
_
፲፭) የሚመጸወተው ገንዘብ ነውር ነቀፋ የሌለበት ይሁን። ይኽም ላለፈው የተሰረቀ የተቀማ፣ ለሚመጣው ውዳሴ ከንቱ ያለበት አይሁን።
_
፲፮) ደስ ብሎት ደስ አሰኝቶ የሚሰጠውን ሰው እግዚአብሔር ይወደዋል።
_
፲፯) ከክፉዎች ምጽዋት ትቀበሉ ዘንድ አትውደዱ። ከእነርሱ ምጽዋትን ከምትቀበሉ በረኀብ ብትሞቱ ይሻላችኋል።

__አንቀጽ ፲፯___
ይህ አንቀጽ በምጽዋትና በቤተክርስቲያን ገንዘብ እንዲሁም በመብዓው ስለሚሾሙ ሰዎች ይናገራል
፩) ኤጲስ ቆጶስ በቤተክርስቲያን ገንዘብ ሁሉ ማዘዝ ይገባዋል። ለራሱ የሚሻውን፣ ከካህናት ወገን ለተቸገሩ ሰዎች ማወጣጣት ይገባዋል።
_
፪) ኤጲስ ቆጶስ የቤተክርስቲያንን ገንዘብ ምንም ድሆች ቢሆኑ ለዘመዶቹ መስጠት አይገባውም።
_
፫) የቤተክርስቲያን ገንዘብ፣ ልብስ፣ እርሻ፣ የተክል ቦታ፣ ላም፣ በሬ፣ ፈረስ እግዚአብሔርን በሚፈሩ በታመኑ ሰዎች እጅ ይጠበቅ።
_
፬) የቤተክርስቲያንን ገንዘብ የሸጠ፣ ገዝቶም የያዘ ሰው ይመልሱ። ባይመልሱ በኤጲስ ቆጶሱ እጥፍ አድርገው ይክፈሉ።
_
፭) ከምእመናን አንዱ ገንዘቤን ለቤተክርስቲያን ስጡ ብሎ አዝዞ ቢሞት የቤተክርስቲያኑ ገበዝ ይቀበል። የሚቀበለው ገንዘብ የንጉሥ ግብር ያለበት ከሆነ አይቀበሉት። ቤተክርስቲያን ከነገሥታት ሥልጣን በታች ልትሆን አይገባምና።
_
፮) በቤተክርስቲያን በገቢው ገንዘብ የተሾመው በወጭ ገንዘብ ከተሾመው ይለይ።
_
፯) በየሀገሩ ሁሉ ለታመሙ ለድኆች ለእንግዶች የሚያድሩበት ቤት ይለዩላቸው። እነርሱን ያስተዳድርለት ዘንድ ኤጲስ ቆጶሱ መነኩሴ ይሹም። ለሹሙ ቤት ምግብ ይመቻችለት። የቤተክርስቲያኑ ገንዘብ ቢያንስ ከምእመናን ሁሉ እንደአቅማቸው በየጊዜው ምግብ ይሰብስብላቸው። ስለዚህ ነገር ብዙ ኃጢአት ይሠረያል።
_
፰) አሥራት ሁሉ ለካህናት ሊሆን ይገባል።
_
፱) በሾላ፣ በሽንኩርት፣ በዱባ፣ በቅል እና እነዚህ በሚመስሉ አትክልት ከቤተክርስቲያን አግብተው አይጸልዩባቸው። በጽጌረዳ፣ በወይን፣ በበለስ፣ በሮማን፣ በዘይት፣ በሙዝ፣ በእንኮይ ግን ይጸልዩባቸው።
_
፲) ከመሥዋዕት የተረፈውን ለኤጲስ ቆጶሱ 4 ክፍል፣ ለቀሳውስት 3 ክፍል፣ ለዲያቆናት 2 ክፍል፣ ከዚያ በታች ላሉት እስከ ዲያቆናዊት ድረስ 1፣ 1 ክፍል ይስጧቸው።

__አንቀጽ 18____
ይህ አንቀጽ ስለ አሥራት፣ ስለ በኩራት፣ ስለ ስለት፣ ስለ ጉልት ይናገራል።
፩) አሥራት፣ በኵራት፣ ስለት፣ ጉልት የምጽዋት ወገኖች ናቸው።
_
፪) በኩራት (ቀዳምያት) መጀመሪያ የተቀዳውን ዘይት፣ መጀመሪያ የተቆረጠውን ማር፣ መጀመሪያ የታለበውን ወተት፣ መጀመሪያ የተሸለተውን ጸጉር፣ ጽፈው ደጉሰው መጀመሪያ ያገኙትን ገንዘብ ለቤተክርስቲያን መስጠት ነው። ካህኑ ላመጡት ሰዎች ከመጋረጃ ውጭ ሆኖ እግዚአብሔርን ያመስግነው።
_
፫) ስለት ከልዑል እግዚአብሔር ዘንድ በጎ ነገርን ለማግኘት ሰው በራሱ፣ በልጆቹ፣ በገንዘቡ የተሳለውን ለመፈጸም ከፈጣሪው ጋር የተማማለው መሓላ ነው። የሚሻውን ነገር ባገኘ ጊዜ ስለቱን እንዲፈጽም ሰው ከመሳሉ በፊት በደንብ ያስብ።
_
፬) ይህ ዓለም ኃላፊ ያ ዓለም ኗሪ እንደሆነ አውቆ መሳል በጎ ነገርን ለማግኘት ነው።
_
፭) መከራ ባገኘው ጊዜ ተሳለ እንጂ የተሳለውን ስለት መፈጸም የማይቻለው ድኃ ቢሆን ወደ ኤጲስ ቆጶሱ ወይም ወደ ቄሱ ይሂድ። ቄሱ ወይም ኤጲስ ቆጶሱም የሚችለውን መጠን አይተው ይወስኑለት።
_
፮) ስለትን አለመፈጸም ከእግዚአብሔር ዘንድ ፍዳን ያመጣብናል።
_
፯) ሴት ልጅ በአባቷ ቤት ሳለ በራሷ ላይ ብትሳል ማለትም ንጽሕ ጠብቄ ሰውነቴን ለእግዚአብሔር ልዩ ገንዘብ አደርገዋለሁ ብላ የተሳለችውን ስለት መፈጸም ይገባታል። አባቷም ስለቷን አያፍርስባት። ስትሳል ሰምቶ ስለቷን ቢያፈርስባት ግን ስለቷ አይጸናላትም። እግዚአብሔርም በዚህ አይመራመራትም። ባል ብታገባ ግን በተሳለችው ስለት ባሏ ሊያዝበት ይገባል። ባሏ ስትሳል ቸል ብሎ ከዚህ በኋላ ቢከለክላት ኃጢአቱ በእርሱ ይሆናል።
2.1K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:18:45 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፫__
አንቀጽ 15 ስለ ጾም ይናገራል።
፩) ጾም በመጸሐፍ በታወቀው ዕለትና ሰዓት ከምግብ መከልከል ነው።
_
፪) የጾም ጥቅሞች ከብዙ በጥቂቱ:-
√ ኃጢአትን ያስተሰርያል (ይቅር ያስብላል)
√ ረድኤት በረከትን ያሰጣል
√ የፍትወት ፈተናን ያደክማል (ይቀንሳል)
√ ሥጋ ለነፍስ እንድትገዛ ያደርጋል
፫) በጾም ሥጋ፣ ወተት (የፍስክ ምግቦች) የተከለከሉ ናቸው።
_
፬) ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሊጾማቸው የሚገቡ አጽዋማት የሚከተሉት ናቸው።
ዐቢይ ጾም
ዓርብና ረቡዕ
የነነዌ ጾም
የልደትና የጥምቀት ዋዜማ (ገሐድ)
የነቢያት ጾም
የሐዋርያት ጾም
የፍልሰታ ጾም
፭) ዓርብ እና ረቡዕ በበዓለ ኃምሳ እና ልደትና ጥምቀት ከዋሉባቸው አይጾሙም።
_
፮) ዓርብና ረቡዕን፣ ጾመ ሐዋርያትን፣ የነቢያት ጾምን፣ የነነዌ ጾምን፣ የፍልሰታ ጾምን እስከ ዘጠኝ ሰዓት ይጹሟቸው።
_
፯) የነቢያት ጾም በአራቱም ዘመናት (በዘመነ ዮሐንስ፣ በዘመነ ማቴዎስ፣ በዘመኑ ማርቆስ፣ በዘመነ ሉቃስ) ኅዳር 15 ይጀምራል። ፍጻሜው የልደት በዓል ነው።
_
፰) የሐዋርያት ጾም ከበዓለ ኃምሳ ቀጥሎ ይሆናል። ፋሲካው ሐምሌ ፭ ቀን ነው። የፍልሰታ ጾም ነሐሴ ፩ ይጀመራል። ፋሲካው ነሐሴ ፲፮ ነው።
_
፱) ከጥሉላት በቀር እሑድና ቅዳሜ አይጹሙ።
_
፲) ሰው በጾም መላእክትን ይመስላል። የሚጾም ሰው የረኀብን የጥምን ጾር ያውቃል። በዚህም ምክንያት ለሚራቡት ለሚጠሙት ይራራላቸዋል።
_
፲፩) ከቅዳሜ ስዑር ውጭ ቅዳሜን መጾም አይገባም።
_
፲፪) በሰሙነ ሕማማት ውሃ ብቻ ከመጠጣት የጨው ቂጣ ከመብላት በቀር ሌላ አይብሉባቸው። በእነዚህ ዕለታት ወይን መጠጣት አይገባንም። የኀዘን የልቅሶ ዕለታት ናቸውና።
_
፲፫) (አክፍሎት) ዓርብና ቅዳሜን ሁለቱን አንድ አድርጋችሁ ጹሟቸው። ሁለቱን መጾም ያልቻለ ቀዳሚትን ብቻ ይጹም።
_
፲፬) በዓለ ኃምሳን በመብል በመጠጥ ከፈጸማችሁ በኋላ ሰባት ቀን በዓለ ጰራቅሊጦስን አክብሩ።
_
፲፭) እንጹም እንብላ በማለት ጠብ ክርክር ቢነሳ መጾም ይገባል። ለነፍስ ከመብል ጾም ይሻላታልና።
_
፲፮) እሑድ እና ቅዳሜ (ከቅዳሜ ስዑር ውጭ) ሲጾም የተገኘ ካህን ከክህነቱ ይሻር።
_
፲፯) በዐቢይ ጾም የሰማዕታትን በዓል በመብል በመጠጥ ልናከብር አይገባንም። እሑድና ቅዳሜ ይከበር። ሰኞ፣ ማክሰኞ፣ ረቡዕ ቢውል ባለፈው እሑድ ይከበር። ኃሙስ፣ ዓርብ፣ ቅዳሜ ቢውል በሚመጣው እሑድ ይከበር። ረቡዕ ቢሆን ባለፈውም በሚመጣውም ይሆናል።
_
፲፰) በዐቢይ ጾም፣ በዓርብ ረቡዕ ወይን መጠጣት አይገባም። ከውሽባ ቤትም አይግባ።
_
፲፱) በዐቢይ ጾም ሰው ከሚስቱ ጋራ በአንድ ምንጣፍ አይተኛ።
_
፳) የልደትና የጥምቀት ቁርባን ሌሊት ይሁን።
_
፳፩) በዘወረደ እስከ 12 ሰዓት ይጹሙ፣ ከቅድስት እስከ ኒቆዲሞስ እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፣ በሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ይጹሙ።
_
፳፪) በሰሙነ ሕማማት ሴቶች ጌጣቸውን ያኑሩ።
_
፳፫) እግዚአብሔር የሚቀበለው ጾም ልቡናን ከቂም ከበቀል ንጹሕ አድርጎ የሚጾሙት ጾም ነው።
_
፳፬) በዐቢይ ጾም አያግቡ አይጋቡ። በሰሙነ ሕማማት ማጥመቅ፣ ቅስና ዲቁና መሾም፣ ስለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም። [ቁጥር 600]። በሆሳዕና ግንዘተ ሙታን ይነበብ። በሰሙነ ሕማማት ስለሚሞቱ ሰዎች ፍትሐት ይፈታ።
_
፳፭) በጸሎተ ኃሙስ የሰላምታ ጸሎት አይገባም። የይሁዳ ሰላምታ ይሆናልና። የቡራኬ ጸሎት አይጸልዩ። በቀዳም ሥዑር ግን እግዚአ ሕያዋን ይባል። ፍትሐት ይፈታ። ጸሎተ ዕጣን ይጸልዩ። ስዒም ግን አልተፈቀደም።
_
፳፮) በዕለተ እሑድ መገነዝ አይገባም። በፋሲካ የንስሓ ልቅሶ ማልቀስ አይገባም። በሰሙነ ፋሲካ ማልቀስ አይገባም።
_
፳፯) በዐቢይ ጾም ማግባት መጋባት፣ ቅስና ዲቁና መሾም፣ ጥምቀተ ክርስትና አይገባም። የሞተ ሰው መፍታት፣ ይሞታል ብለው የሚፈሩትን ማጥመቅ ግን ይገባል።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፬ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.3K views15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ