Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-06 08:33:32 __ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፩___
አንቀጽ ፲፪ ስለ ቅዳሴ ይናገራል።
፩) በቅዳሴ ጊዜ በቤተክርስቲያን ውስጥ በንጽሕና በጸጥታ ሁነው ሊቆሙ ይገባል።
_
፪) በቅዳሴ ጊዜ ኤጲስ ቆጶሳት በታቦቱ ፊት፣ ሊቀ ዲያቆናቱ በኤጲስ ቆጶሱ ቀኝ፣ ቀሳውስት ከኤጲስ ቆጶሳት በኋላ፣ ዲያቆናት ከቀሳውስት በኋላ፣ ሕዝቡ ከዲያቆናት በኋላ ይቁሙ። ወንዶች ለብቻቸው፣ ሴቶች ለብቻቸው ይቁሙ። ዲያቆናት ይህንን ይቆጣጠሩ።
_
፫) በቅዳሴ ጊዜ የሚተኛ እንዳይኖር፣ የሚስቅ እንዳይኖር ዲያቆናት ሕዝቡን ይጎብኙ።
_
፬) ካህን በቅዳሴ ጊዜ ቢስቅ አንድ ሱባዔ ይጹም። ሕዝባዊ ቢሆን ያን ጊዜ ወጥቶ ይሂድ። አንዱስንኳ በቤተመቅደስ ምራቁን እንትፍ አይበል። ታሞ ምራቅ ቢመጣበት ግን በመሐረብ ተቀብሎ ያሻሸው።
_
፭) በቤተክርስቲያን ዋዛ ፈዛዛ የሚናገር ሰው ወጥቶ ይሂድ። ያን ጊዜ ሥጋውን ደሙን አይቀበል።
_
፮) በቅዳሴ ጊዜ ካልታመመ በስተቀር እትው በሰላም ሳይባል ማንም ቢሆን ከቤተክርስቲያን አይውጣ።
_
፯) ካህናት የሚቀድሱባቸው የቅዳሴ ልብሶች ነጭ ይሁኑ። ለካህናት እስከተረከዛቸው የምትደርስ ትሁን። ዳግመኛም አምስት ከልጅ ያለው ካባ ይልበሱ። ሁለቱ በቀኝና በግራ፣ ሀለቱ በፊት፣ አንዱ በኋላ ነው።
_
፰) የሚቀደስባቸው አልባሳት ከገበዙ ቤት ወይም ከቤተመዛግብት ከዕቃ ቤት ሊኖሩ ይገባል።
_
፱) አንድ ሰውስ እንኳ ጫማ አድርጎ ከቤተ መቅደስ አይግባ።
_
፲) ዲያቆኑ ኅብስቱን በመሶበ ወርቅ አድርጎ ከቤተልሔም ወደ ቤተመቅደስ ይዞ ይግባ።
_
፲፩) ቅዳሴው ሲጀመር ያልነበረ ሰው አይቁረብ።


አንቀጽ ፲፫ ስለ ቁርባን ይናገራል
፩) ቁርባንን በሚገባ ሆነው ቢቀበሉት የእግዚአብሔር ባለሟል ያደርጋል። በሳምንት በሳምንት ዓርብ፣ ረቡዕ፣ ቅዳሜ፣ እሑድ እንዲሁም በበዓላት ይሠው።
_
፪) ካህን ወደ ቤተመቅደስ ማርና ወተት፣ ርግብ፣ ዋኖስ፣ ላም፣ ፍየል መሥዋዕት አድርጎ አያግባ። ለማብራት ከዘይት እና ከዕጣን በቀር ጌታ ካዘዘው ሌላ ማናቸውንም አግብቶ የሠዋ ካህን ቢኖር ይሻር። በቤተ መቅደስ ንጹሕ ከሚሆን ስንዴና ወይን በስተቀር አይሠዉ።
_
፫) በወራቱ የደረሰውን ዋግ ያልመታውን ክርዳድ የሌለበትን ስንዴ ይሠው። ወፍ ያልመጠጠው አይጥ ያልቆረጠው መጀመሪያ የደረሰውን ወይን ይሠው። መሥዋዕት ከቤተክርስቲያን ርስት ጉልት የተገኘ ይሁን። ርስት ጉልት ባይኖራት ግን ምእመናን ካመጡት መባዕ ይሠው።
_
፬) ሰውን የሚሳደቡትን መባዕ፣ የነፍሰ ገዳዮችን፣ የሴሰኞችን፣ ጣዖት የሚያመልኩትን፣ የሌቦችን፣ ጣዖት የሚሠሩትን፣ የሰካራሞችን፣ በማይገባ የሚያስገብሩትን፣ የቀማኞችን፣ የአመፀኞችን፣ በሰው ላይ መከራ የሚያደርሱትን፣ ባሮቻቸውን ክፉ አገዛዝ ከሚገዙ ሰዎች፣ ሕግን ከሚያፈርሱ ሰዎች ሁሉ መባዕ አይቀበሉ።
_
፭) ቤተክርስቲያን አውግዛ የለየቻቸውን ሰዎች መባዕ አትቀበል። ተወግዞ የተለየ አይቁረብ።
_
፮) ጋኔን ያደረበት ሰው የማይሳደብ፣ ከጣለው በኋላ የማያስለግገው ከሆነ በበዓል በበዓል ሥጋውን ደሙን ያቀብሉት።
_
፯) ዲያቆናት መባዕ ያመጡትን ሰዎች ስም ሁልጊዜ ይጻፉ። ሕያዋንንም ሙውታንንም ቢሆን ጸሎት በሚጸልዩበት ጊዜ ስማቸውን ይጠሩ ዘንድ።
_
፰) መሥዋዕቱ ዕለቱን ይላኩት እንጂ ለነገ ብለው አያሳድሩት። ኅብስቱ ነቅ ያለበት አይሁን። ነቅ የሌለበት ያላረረ ያልጠቆረ ይሁን።
_
፱) ዓመት ያለፈውን ወይን አይላክ። በወይኑ ከሲሶ የበለጠ ውሃ አይጨምርበት። ሁለት እጅ ወይን ሲሶ ውሃ ይሁን። ብዙ ወይን ከተገኘ ደግሞ ዘጠኝ እጅ ወይን አሥረኛ ውሃ ይጨመር። ደሙ እንዳይነጥብ ጽዋውን ከልክ አሳልፎ አይምላው።
_
፲) ጠንቅቆ ሳይጾም ማንም ማን ሥጋውን ደሙን አይቀበል። ተደፋፍሮ ሳይጾም የተቀበለ ይወገዝ።
_
፲፩) ምእመናን በቅዳሴ ጊዜ እስኪወጡ ድረስ ቀጥ ብለው በእግራቸው ይቁሙ። (እግራቸውን ሳያፋትሉ፣ ጥግ መቋሚያ ሳይሹ ይቁሙ)። በቤተክርስቲያን ሌላ ነገር ከመናገር ይጠበቁ።
_
፲፪) መባዕ የሚያስገባ ሰው ከማስገባቱ በፊት ከተጣላው ጋር ይታረቅ።
_
፲፫) ሳይገባው ሥጋውን ደሙን የሚቀበል ሰው በራሱ ላይ ፍዳን ያመጣል። ከኃጢአት ሳይነጻ ቢቀበል ፍዳን ያመጣበታል።
_
፲፬) ቁርባንን መጀመሪያ ኤጲስ ቆጶስ፣ ከዚያ ቀሳውስት፣ ከዚያ ዲያቆናት፣ ከዚያ ወንዶች ምእመናን፣ ከዚያ ሴቶች ምእመናን ይቀበሉ።
_
፲፭) ከቁርባን ምንም ምን እንዳይተርፍ ቀሳውስት ዲያቆናት ይጠንቀቁ። ቢተርፍ ጽኑ ፍዳ ይሆንባቸዋልና። ከደሙ የተረፈውን በቤተመቅደስ ያሉ ዲያቆናት ሁሉ ይላኩት።
_
፲፮) ማየ መቁርር ሥጋሁ ወደሙ ከአፍ እንዳይነጥብ ለቃልቆ ለማውረድ ነው። እትው በሰላም ሳይባል አንዱስንኳ ቁርባኑን በተርታ ኅብስት አያብርደው።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፪ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.1K views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 21:53:43 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲__
አንቀጽ 11 ስለ ሕዝባውያን ይናገራል።
፩) ወደ ኃጢአት ሥራ የሚሄድ አንድ ሰው ስንኳ ቢኖር የእግዚአብሔርን ትእዛዝ አፍርሷልና ከዓላዊ ጋር ይቆጠራል።
_
፪) እግዚአብሔር በሰጠህ መልክ ላይ ሌላ መልክ አትጨምር። አትከተብ፣ አትጠቆር።
_
፫) ያድግ ዘንድ ጸጉርህን አትንከባከበው። ጺምህ አትላጭ። (ለወንዶች)። ሰው ከባሕርይው ያገኘውን መልክ አይለውጥ።
_
፬) ረቂቅ (ስስ) ልብስ አትልበስ። ለጣትህም የወርቅ ቀለበት አታድርግ። ይህ ሁሉ የዝሙት ምልክት ነውና።
_
፭) ከደጋግ ሰዎች ጋር ሕይወት የሚገኝባትን የወንጌልን ነገር ተነጋገር። ሁልጊዜ መልካም ነገርን ሥሩ።
_
፮) የወንድሞቻችሁን በደል ፈጥናችሁ ይቅር ማለት ይገባችኋል። ብትቆጡ ይቅር ሳትሉ አትደሩ።
_
፯) በክርስቶስ ያመንን እኛ ሥራ ፈት ሁነን መኖር አይገባንም [ቁጥር ፬፻፴፬]። ምእመናን ሆይ ከሚያሳፍር ነገር ራቁ። የማይረባ የማይጠቅም ነገር አትናገሩ።
_
፰) በአንድ ሰውስ እንኳ ክፉ ነገር አትናገር። ሁለት አንደበት አትሁን። ክፉ ምክር አትምከር። ቀናተኛ አትሁን። ቁጡ ብስጩ፣ ጠብ ክርክር ወዳጅ አትሁን።
_
፱) ሰው የሰይጣን ማደሪያ የሚሆነው በነፍስ ጽነት ሲገኝባት ነው።
_
፲) ያገኘኽውን ሁሉ አመስግነህ ተቀበል።
_
፲፩) ሕዝባዊ ለበረከት የመጣውን ኅብስት ቆርሶ መስጠት አይገባውም።
_
፲፪) ክርስቲያን ወደ ሠርግ ቤት ሄዶ በእጁ ማጨብጨብ በእግሩ ማሸብሸብ (መደነስ) አይገባውም።
_
፲፫) (ክርስቲያን ውርርድ ሊወራረድ አይገባም) በውርርድ አወጣጥተው የሚጠጡ ሰዎች ከተሰበሰቡበት ቤት ገብቶ መጠጣት መብላት አይገባውም።
_
፲፬) ሰውንና እግዚአብሔርን የማታፍር አትሁን። ዘርዕ ከማይዘራበት ተክል ከማይተከልበት እርሻ ቁፋሮ ከሌለበት ቦታ ያለ ሕዝባዊ ሊነግድ ቢያስብ መነገድ ይገባዋል።
_
፲፭) ከሰው ሁሉ ጋር ወንድሜ ወንድሜ ተባባል። ሰው ሁሉ በአንተ ዘንድ ከራስህ ይልቅ የከበሩ ይሁኑ።
_
፲፮) ለመገሠጽ ሕጻናትን ብቻ ካልሆነ ማንንም አትማታ። ይኽውም በብዙ ጥንቃቄ ይሁን። ፊትህን አማትበህ ብትሩን አሳይተህ መሬቱን ጉልበትህን መትተህ ይሁን።
_
፲፯) ሁልጊዜ ንቁሓን መሆን ይገባናል። ማንም ቢሆን ከክፉ ሥራ ክርስቶስ ያዘዘውን በጎ ሥራ ወደ መሥራት ሳይመለስ ክርስቲያናዊ ነኝ ብሎ አያስብ። ክርስቲያን ነኝ እያለ የክርስቲያንን ሥራ የማይሠራ ሰው የዲያብሎስ መዘባበቻ ይሆናል።
_
፲፰) ምእመን ድኅነተ ነፍስ ለማይገኝበት ለአዝማሪ ለዘዋሪ ገንዘቡን አይስጥ።
_
፲፱) ክርስቲያን አንዲት ሴት አግብቶ በዚያች ጸንቶ ይኑር። እግዚአብሔርን ፈርቶ ልጆችን ቀጥቶ ያሳድግ። መከራ በመጣ ጊዜ ልጆቹን ጥሎ አይሽሽ።
_
፳) ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ መገኛ ነው። የዕለት ጉርስ የዓመት ልብስ ካገኘን ይበቃናል። ምእመናን ተግባረ እድን አትተው። እናንተም የምትመገቡትን ለነዳያንም የምትሰጡትን ባለዘመናችሁ ታገኙ ዘንድ።
_
፳፩) ወላጆች ለልጆቻቸው ሃይማኖትን ምግባርን መጻሕፍትን ያስተምሯቸው። ሥጋዊ ጥበብንም እያስተማሩ ያሳድጓቸው። ሥራ ፈት ሆነው እንዳይኖሩ።
_
፳፪) ወላጆች ልጆቻችሁ ወደ መጠጥ ቤት እንዳይሄዱ ተቆጣጠሯቸው። ወላጆች ቸል ብለዋቸው ሕጻናት ቢበድሉ ወላጆችም በሕጻናቱ በደል ከፈጣሪ ዘንድ ይጠየቁበታል።
_
፳፫) ወላጆች ለልጆቻቸው ሀብት ንብረት ሊያኖሩላቸው ይገባል። ሕጻናት ለወላጆቻቸው ሊታዘዙ ይገባል። እድሜያቸው ይበዛ ዘንድ። ወላጆች ልጆቻችሁን በጎ ምክር እየመከራችሁ ወንጌል እያስተማራችሁ አዳድጓቸው።
_
፳፬) ወላጆች ለልጆቻቸው በሰባቱ ጊዜያት ጸሎት መጸለይን ያስተምሯቸው። እናትና አባትህን አክብር። የመገኛህ ምክንያት እነርሱ ናቸውና።
_
፳፭) ወንዶች ሚስቶቻቸውን መውደድ ሴቶችም ለባሎቻቸው መታዘዝ ይገባቸዋል። ሚስት ባሏን ትውደደው ትፍራው ታክብረው። ባልም ሚስቱን እንደራሱ አድርጎ ይውደዳት።
_
፳፮) ባል ሚስቱን ደስ ለማሰኘት የሚፋጠን ይሁን። ሚስትም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ ባልሽን ደስ አሰኚው።
_
፳፯) ሴት መንገድ በምትሄድበት ጊዜ በሰርሜዳዋ ትከናነብ። ክፉ ሰዎችን ከማየት፣ በክፉ ሰዎች ከመታየት ትድን ዘንድ። ፊቷን አትጠቆር። ሴት ዘወትር ራሷን ትከናነብ።
_
፳፰) ሚስት ከባሏ ጋር አትፈካከር። ሠራተኞች ለአሠሪዎቻቸው ይታዘዙ። አሠሪም ሠራተኞቹን እንደ ልጆቹ ይያቸው።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲፩ ይቀጥላል።
1.8K views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 21:35:27 Live stream finished (33 minutes)
18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 21:01:38 Live stream started
18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 18:18:19
የመድኃኔዓለም በዓል፣ የልደት በዓል (ታኅሣሥ 29) እና ታኅሣሥ 19 እጅግ በጣም ደስ የሚሉኝ ልዩ ቅዱሳት በዓላት ናቸው። እንኳን አደረሳችሁ።
መጋቢት 27 ሰውን ለማዳን ልዑል አባታችን መድኃኔዓለም በመስቀል ላይ ተሰቀለ። በሞቱ ሞትን አጠፋልን። የፍቅርን መጨረሻ አሳየን። ራስን ስለሌሎች ቤዛ አድርጎ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ፍቅር የለምና። መጋቢት 27 ዕለተ ዓርብን ቀንም፣ ማታም፣ ሌሊትም፣ በጋም፣ ክረምትም፣ በማንኛውም ሰዓት ማስታዎስ የምፈልገውና ባስታወስኩት ቁጥር ጥልቅ ደስታን የሚሰጠኝ ልዩ ዕለት ነው። ለእኔ ልዩ ቀን ነው።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ
2.3K viewsedited  15:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 07:30:02 _ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፱__
አንቀጽ ፲ ስለ መነኮሳት ይናገራል።
፩) ምንኩስና ወንጌል ያመጣቻት ሕግ ናት። መነኮሳት ምድራውያን መላእክት ናቸው።
_
፪) መነኮሳት ለእግዚአብሔር ትእዛዝ እየኖሩ፣ ጌታን ስለወደዱ ሰውነታቸውን ሁሉ ሳይቀር የናቁ ናቸው።
_
፫) መነኮሳት ጌታ ፍጹም ልትሆን ከፈለግህ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ተከተለኝ ያለውን ቃል የተገበሩ ናቸው።
_
፬) መነኩሴ የማለውን መሓላ ለመፈጸም የማይነዋወጥ ኅሊና ያለው ሊሆን ይገባል። ከመነነ በኋላ ወደኋላ አይመለስ።
_
፭) ጋኔን ያደረበት ሰው አይመንኩስ። ልጁን፣ ቤተሰቡን፣ አባቱን፣ ሚስቱን ጥሎ የመጣ ሰውን ሳይመረምሩ አያመንኩሱት። ልጆች ወልዶ ያለምግብ የሚተዋቸው ከሆነ አያመንኩሱት። እናት አባቱ የሚረዱ ሆነው ሳለ ትቷቸው የመጣን ሰው አያመንኩሱት። በምን ምክንያት ሊመነኩስ እንደመጣ ይጠይቁት።
_
፮) ሚስቱ የፈቀደችለት፣ ባሏ የፈቀደላት መመንኮስ ይችላሉ። ከምእመናን ለአንዱ ባሪያ ሆኖ ጌታው ሳይፈቅድለት አያመንኩሱት። በአባቱ ፈቃድ የሚኖርን ሕጻን አባቱ ሳይፈቅድለት አያመንኩሱት። ራሱን የቻለ ቢሆን ያመንኩሱት።
_
፯) በድንገት በእጁ ሰው የሞተበት ሰው መመንኮስ ቢፈልግ ያመንኩሱት። ከመነኮሰ በኋላ ባለደሞቹ እንገድላለን ቢሉ እርሱን ለማዳን አበምኔቱም ማኅበሩም ይውጡ። ወዶ አልገደለምና። ይህ አንቀጽ ግዘት የለበትም። አውጥተን እንገድላለን ቢሉ ያልተወገዘበት አንቀጽ ነው።
_
፰) ሰው ከመመንኮሱ በፊት በገንዘቡ ማዘዝ ይችላል። ከመነኮሰ በኋላ ግን ገንዘቡ ሁሉ ለገዳሙ ይሆናል።
_
፱) ደናግላንም ያገቡትም መመንኮስ ይችላሉ። ድንግል ሆነው የመነኮሱት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረውን ቃል የጠበቁ ናቸው። ያላገባ የበለጠ እግዚአብሔርን አገለገለ እንዲል። አግብተው የመነኮሱት ደግሞ ስለእኔ ሚስቱን የተወ የዘለዓለም ሕይወት አለው ያለውን የጌታ ቃል የጠበቁ ናቸው።
_
፲) ምንኩስና የዚህን ዓለም ሹመት ሽልማት መተው ነው። ምንኩስና በገዳም ጸንቶ መኖር ነው። መነኩሴ ማቅ ለብሶ ወገቡን በዝናር (ቅናት) ይታጠቃል። ምንኩስና ሥጋን መብላትንና ወይንን መጠጣትን መተው ነው። ወይን ለመጠጣት የሚያስፈልግ ደዌ ካላገኘው። ምንኩስና ለቁመተ ሥጋ ያህል ምግብን ከፍሎ (ቀንሶ) መመገብ ነው።
_
፲፩) መነኮሳት በገዳም ተሰብስበው እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው ይኑሩ።
_
፲፪) አበ ምኔት በኤጲስ ቆጶሱ ፈቃድ ይሾማል። ቆሞስ የሆነ ይሾማል። አበ ምኔቱ በሕይወተ ሥጋ ሳለ ከእኔ ቀጥሎ እገሌ ይሾም ብሎ ቢያዝዝ ከዘመዱ ወገን ያይደለ ሃይማኖቱ የጸና ለገዳሙ የሚረባ ምግባር ያለው ከሆነ ይሾም። ይህ አንቀጽ ውግዘት የለበትም። ሌላ የበለጠ አግኝተው ቢሾሙ እዳ የለባቸውም።
_
፲፫) አበ ምኔት በገዳሙ ያደገ፣ ድንግልና ከምንኩስና ያለው፣ መጽሐፍ የተማረ ይሁን። አበምኔት ለመነኮሳቱ እንደ አባት ይሁናቸው።
_
፲፬) መንፈሳውያን አባቶቻችንን ፈጽመን መርዳት ማገልገል ይገባናል። መምህራንም ደቀመዛሙርቶቻቸውን እንደ ልጆቻቸው ሊንከባከቧቸው ይገባል። ከፍጹምነት አድርሳቸው በሃይማኖት አጽናቸው እያሉ ይጸልዩላቸው።
_
፲፭) አበምኔት እግዚአብሔር የሚመሰገንበትን ሥራ ይሥራ (ቁጥር ፫፻፸፫)። ዕረፍት ወዳጅ አይሁን። ወደ ገዳም ከሚመጡ ሰዎች አንዱንስ እንኳ አይናቅ አያቃል።
_
፲፮) የገዳሙን በር የሚጠብቀው ሰው ቃለ ሻካራ ሳይሆን ቃለ ልዝብ ይሁን። ግንባረ ቆጣራ አይሁን። ፈጽሞ ትሁት ይሁን። ሲረግሙት ሲሰድቡት የሚታገሥ ይሁን። በረኛው ከገዳሙ ወጥቶ ይሄድ ዘንድ ለማንም ለማን ሥልጣን አይስጥ።
_
፲፯) መነኮሳት ዘወትር የሚጾሙ የሚጸልዩ ክቡራት መጻሕፍትን የሚመለከቱ ሊሆኑ ይገባል።
_
፲፰)መነኮሳት ሥጋዊ ጌጥ አያጊጡ፣ ሽቱ አይቀቡ።
_
፲፱) በገዳም ያሉትን ሰዎች ለመርዳት ፈጽመው ሠራተኞች የሆኑ መነኮሳት በአንድ ቀን ሁለት ጊዜ መመገብ ይገባቸዋል። ይኽውም በ፮ ሰዓትና በሠርክ ነው። ሠራተኞች ካልሆኑ ግን በ፱ ሰዓት ወይም በሠርክ አንድ ጊዜ ይብሉ።
_
፳) መነኮሳት ከበዓታቸው ከመሬት ላይ ይተኙ። አበ ምኔቱ እና የታመሙ መነኮሳት ግን ከአልጋ ላይ ሊተኙ ቢወዱ አበምኔቱ ስለክብሩ ታማሚዎች ስለሕመማቸው መተኛት ይገባቸዋል።
_
፳፩) የሹመት ፍቅር ሰይጣን ያለማው ደዌ ነው። ሐዋርያት በይሁዳ ክፋት ከአንድነታቸው አልተለዩም። እንዲሁ መነኮሳት አንዱ ክፉ ቢሆን ከአንድነታቸው አይለዩ።
_
፳፪) እውነተኛ ምንኩስና አስቀድመህ ዓይንህን ክፉ ከማየት ጆሮህን ክፉ ከመስማት ወስነህ ገትተህ ትይዝ ዘንድ ነው። ከዚህ በኋላ ልቡናህን ክፉ ነገር ከማሰብ አንደበትህን ክፉ ነገር ከመናገር ወስነህ ገትተህ መያዝ ነው።
_
፳፫) በሥራው ሁሉ በጎ ብንሠራ እግዚአብሔር ያይልናል ብለን እንዲያይልን አድርገን መሥራት አንድም ክፉ ብንሠራ እግዚአብሔር ያይብናል ብለን እንዳያይበን አድርገን ክፉውን መተው ይገባናል። ፈሪሀ እግዚአብሔር በልቡናችን ጸንታ ትኑር።
_
፳፬) ታመህ ሥጋ ብትበላ ለትሩፋት መሰናክል ይሆንብሃል እንጂ ኃጢአት ተብሎ አይቆጠርብህም።
_
፳፭) መነኩሴ መነኩሴን ቢደበድበው 40 ቀን ከማኅበሩ ይለይ። እርስ በእርስ ከተደባደቡ ሁለቱም 40 ቀን ከማኅበሩ ይለዩ።
_
፳፮) ድንግል ሴት አካለ መጠን ካደረሰች በኋላ ብቻዋን መሄድ አይገባትም። ፀሐይ ከገባ በኋላ ከደጅ ወጥታ ለሰው መታየት አይገባትም [ማንም ይንጠቀኝ ማለት ነውና] ስትናገርም ቃሏን ከፍ ከፍ አድርጋ መናገር አይገባትም።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፲ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
782 views04:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 21:28:05 የትምህርት ሰዓቱ ስንት ሰዓት ይሁን?

ሀ) ከ2 ሰዓት ጀምሮ
ለ) ከ3 ሰዓት ጀምሮ
1.7K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 20:01:31 Live stream started
17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 15:45:08 "ተቀመጠ" ማለትና "ተጠመቀ" ማለት ይለያያሉ። መረጃን በደንብ ማጥራትን እንልመድ። ግርርርርርርር ማለት አኮ ሠናይ።
1.3K views12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 14:11:00 ፩) ሴት ልጅ ወንዶች ባሉበት በዓውደ ምሕረት መዘመር አትችልም። ይህንን ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ነግሮናል። 1ኛ ቆሮ. ፲፬፣ ፴፬ "ሴቶችም በቤተክርስቲያን ዝም ይበሉ። ሊታዘዙ እንጂ ሊናገሩ አልተፈቀደምና። ኦሪትም እንዲህ ብሏልና። ለሴት በቤተክርስቲያን መናገር ክልክል ነው" እንዲል። በተጨማሪም 1ኛ ጢሞ. 2፣11 "ሴት ግን በጸጥታ ትኑር እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ እንድትሰለጥን አንፈቅድም" እንዲል። የሙሴ እኅት ማርያም እንኳ በሴቶች መካከል ዘመረች ይላል እንጂ በወንዶች መካከል አልዘመረችም። ዘጸ. ፲፭፣፳ "የአሮን እኅት ነቢይቱ ማርያምም ከበሮ በእጇ ወሰደች። ሴቶችም ሁሉ በከበሮና በዝማሬ በኋላዋ ወጡ። ማርያምም አስቀድማ ለእግዚአብሔር እንዘምር አለች" እንዲል። ሴት ሴቶችን ማስተማር ትችላለች። ቲቶ ፪፣፫ "ባልቴቶችም___በጎ የሆነውንም ትምህርት ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ለሴቶች ያስተምሩ" እንዲል። ሴቶች ዘማርያት ሆነው በዓውደ ምሕረት ሲዘምሩ ጳጳሱ ዝም ስላለ ልክ ነው አይባልም። ይህ በቸልተኝነት የመጣ ክፉ ልማድ ነው።

ወደፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት፣ ከሥርዓት የተጣላ ትውልድ እንዳይፈጠር እሰጋለሁ። ምክንያቱም አሁን አሁን በተለይ ከ1900 ዓ. ም ወዲህ ብዙ ነገሮች ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጡ ናቸው። ልምድ ሆነው ሰውም ዝም ብሏል። ክፉ ልማድ ሥር ሳይሰድ ካልነቀልነው የወደፊት ምእመናን ሃይማኖታቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጠ እየመሰላቸው ይቸገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት የተጣሉ የልማድ ሰዎች ይሆኑብናል። በእርግጥ አንዳንድ ታላላቅ አድባራት ላይ አሁንም ቢሆን ሴቶች በዓውደ ምሕረት አይዘምሩም። ይህ በሁሉም ሊሆን ይገባል።

፪) የጾም ሰዓት ከዐቢይ ጾም ውጭ ያሉት እስከ ፱ ሰዓት ይጾማሉ። ሰው ግን ጾሞ ግን 7 ሰዓት ላይ ይበላል። ከየት የመጣ ሥርዓት ነው ይሄ??? ጾሙን ሳይጨርሰው ገደፈኮ?። ይህ ሊስተካከል ይገባል።

አንድ ቀን ቆማ ፋሲለደስ አቡነ እንድርያስ ዐቢይ ጾም ሊገባ ሲል ዘወረደ እስከ ፲፪ ሰዓት ይጾማል፣ ሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ ፩ ሰዓት ይጾማል። ከቅድስት እስከ ኒቆዲሞስ ዓርብ እስከ ፲፩ ሰዓት ይጾማል ብለው አስተማሩና እንኳን እውነቱን ነገርኳችሁ እንጂ ከዚህ በኋላ የራሳችሁ ውሳኔ ነው አሉ።

እና ብዙ እውነታዎች አሉ። ያው መረር ቢላችሁም እውነታዋን መናገር ይሻላል። አንዳንዱ ይህ አንገብጋቢ ጉዳይ አይደለም ይልሀል። የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ካለመጠበቅ በላይ አንገብጋቢ ጉዳይ አለ ወይ? በሉ ደህና ዋሉ።
1.8K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ