Get Mystery Box with random crypto!

በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የቴሌግራም ቻናል አርማ betremariyamabebaw — በትረማርያም አበባው
የሰርጥ አድራሻ: @betremariyamabebaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.25K
የሰርጥ መግለጫ

አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-26 10:27:26 _ዲድስቅልያ ክፍል ፪_
_አንቀጽ ፬_√
ይህ አንቀጽ ስለ ኤጲስ ቆጶስ ይናገራል።
፩-፬:- ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ የሚሾመው 50 ዓመት የሞላው፣ ነገር የማይሠራ ሊሆን ይገባል። ሀገሪቷ ትንሽ ብትሆንና 50 ዓመት የሞላው ባይገኝ አዋቂና ብልህ እድሜው ጥቂት የሆነ መሾም ይችላል።
፲-፲፩:- ኤጲስ ቆጶስ የሚሾም ሰው ቂም፣ ክፋትና ዐመፅ የሌለበት ልበ ንጹሕ ይሁን። የማይቆጣ፣ የማይሰክር፣ የማይበቀል፣ ጸብና ክርክር የሌለው፣ የማይሳደብ ይሁን።
፲፯:- የኤጲስ ቆጶስ ምግቡ የላመ የጣመ ይሁን። መጥኖ ይመገብ። ሕዝቡን መክሮ አስተምሮ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ይቻለው ዘንድ። ከክፉም ሁሉ ይርቅ ዘንድ መጻሕፍትን ሁልጊዜ ይመልከት።
፳፪:- ኤጲስ ቆጶስ ማንንም ቸል አይበል። መኳንንቱን አይከተል። እግዚአብሔርን ይፍራ።
፳፭:- የሚያስተምረውን የሚሠራ ሰው በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይሆናል።
፳፮:- ኤጲስ ቆጶሳት ሕዝቡን አስተምራችሁ ከስሕተት ታድኗቸው ዘንድ ለእናንተ ይገባል።
፵፪:- ሰው ሐሰትን በላዩ የተናገረበት ቢኖርም ብፁዕ ነው።
፵፮:- ለኤጲስ ቆጶሱ እውነትን ይመረምር ዘንድ ይገባዋል። ከማንም መማለጃን አይቀበል።
፵፱:- ኤጲስ ቆጶስ ባያስተምርና ባይገሥፅ በቅንነት መንገድም ባይሄድ ውግዘት ያገኘዋል።
፶:- በደል ሳይኖርባቸው ንጹሓንም ሲሆኑ በኤጲስ ቆጶሱ ላይ በሹማምንቱም ላይ የሚበድል ቢኖር ወደ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ሊገባ አይገባውም። ደፍሮ በራሱ ፈቃድ በስንፍና ኖሯልና።
፷፪:- ሰው ሆይ እወቅ አስተውልም። በዚህ ዓለም ብትበድል ኃጢአትንም ብትሠራ ንስሓም ባትገባ ድኅነት አይኖርህም።
፷፭:- ለኤጲስ ቆጶሱ በእውነት አስተውሎ ይፈርድ ዘንድ ይገባዋል። ፍርድ ለእግዚአብሔር ነውና።
፸፯:- ድል የነሣ ሰው የድል አድራጊነቱን አክሊል ይቀበላል። እግዚአብሔር ጻድቅን ከኃጥእ ጋር አይቀጣምና።
፸፱:- ኃጥአን በጻድቃን እንደማይቀጡ፣ ጻድቃንም በኃጥአን እንደማይቀጡ የታወቀ ነው።
_አንቀጽ ፭_√
፳፩:- ልጅ የአባቱን ኃጢአት አይሸከምም። አባትም የልጁን ኃጢአት አይሸከምም።
፴፩:- ከኃጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ።
_አንቀጽ ፮_√
፩:- እግዚአብሔር ያለምሕረት በማክበድና በልብ ተንኮል የሚፈርዱትን አይወድም።
፫:- አሁንም ወደ እግዚአብሔር የተመለሱትን በደስታና በፍቅር ንስሓቸውብ እንቀበል። የበደሉትንም ለንስሓ እንደሚገባ በፍቅርና በምሕረት እንፍረድላቸው።
፬:- ኀጢአትን የሚሠራ በስሕተትም የሚሰነካከል ሰው ብታይ ከወደቀበት አንሣው። ሥራውን ብታጣጥምለት ግን እነሆ ወንድምህን ገደልከው።
፱:- ለኃጢአተኛ ሰው ያዝንና ይተክዝ ራሱንም ይንቅ ዘንድ ይገባዋል
፲፫:- ያገኘውን ሁሉ የሚነክስ እብድ ውሻ ካልገደሉት የነከሳቸው ሁሉ በአንድነት ከእርሱ ጋር እንደሚያብዱ እንዲሁ የሚዘብት፣ የሚያስት፣ ክርክርንም የሚያመጣ፣ በሕግ ያለውንም ትእዛዝ የሚያፈርስ ሰው ቢኖር የእግዚአብሔርን ቤት እንዳያጠፋ ከቤተክርስቲያን ወደ ውጭ ያውጡት።
፲፬:- ስለ ኃጥአንና ስለ ዐመፀኞች ዝም እንል ዘንድ አይገባንም። ነገር ግን ክፉ ሥራቸውን ይተው ዘንድ እንምከራቸው። እግዚአብሔርንም መፍራትን ይማሩ ዘንድ እንዘዛቸው።
፲፭:- ኤጲስ ቆጶስ ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ያዝን ዘንድ ይገባዋል።
፲፯:- ሕዝቡን በሰላም ይጠብቃቸው ዘንድ ለኤጲስ ቆጶሱ አግባብ ነው።
፳፰-፳፱:- ቸር እረኛን የማይከተል ይጠፋ ዘንድ ለጅብ እንደሚሆን እንደዚሁ ሰነፍና ክፉ እረኛን የሚከተል ለሞት ይሆናል። ራሱ እረኛው ይውጠዋልና። ስለዚህ ከማይራሩና መንጋቸውን ከማያድኑ ከክፉዎችና ከከዳተኞች እንርቅ ዘንድ አግባብ ነው። ነገር ግን የሚራሩና መንጋቸውን የሚያድኑ ቸሮች እረኞችን እንከተላቸው።
፴፩:- ኤጲስ ቆጶሱ ሕዝቡን እንደ ልጆቹ ሊወዳቸው ይገባል። እነርሱ ልጆቹ ናቸውና። የእግዚአብሔርን ቃል ያስተምራቸው። ሥርዓትን አያክብድባቸው።
፵:- ለኤጲስ ቆጶስ ኀጢአት በመሥራት የታመሙ ድውያንን ያድን ዘንድ፣ ይጎበኛቸውና ያጽናናቸው ዘንድ ቁስላቸውንም ያድናቸው ዘንድ ይገባዋል።
፵፩:- የክርስቶስን መንጋዎች ሳትቆጣ በሥልጣንህም ሹመት ሳትታበይ በትሕትናና በፍቅር ጠብቅ። የክርስቶስ መንጋዎች ጠባቂ አንተ ነህና።
++++
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፫ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.6K views07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 09:55:52 _ዲድስቅልያ ክፍል ፩_
ስምንቱ የሕግና የሥርዓት መጻሕፍት የሚባሉት:-
፩) ሥርዓተ ጽዮን
፪) ትእዛዝ
፫) ግጽው
፬) አብጥሊስ
፭) ፩ኛ መጽሐፈ ኪዳን
፮) ፪ኛ መጽሐፈ ኪዳን
፯) ቀሌምንጦስ
፰) ዲድስቅልያ
ናቸው። አራቱን ከዚህ ቀደም ተማምረናቸዋል። ዲድስቅልያ ማለት ትምህርት ማለት ነው። የጽርእ ቃል ነው። ዮሐንስ ቅዱስ ጴጥሮስን አበ ዓለም ይለው ነበር። ይህንን ዲድስቅልያ የተባለ መጽሐፍ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም ከተማ ተሰብስበው ሠርተውታል።
_አንቀጽ ፩_√
፪:- በቤተክርስቲያን ያሉ የሹመት መዓርጋት በሰማያት ባለው አምሳል እንዲሆን አዘዝን።
፬:- ኤጲስ ቆጶሱ እንደ ጠባቂ ነው። ቀሳውስትም መምህራን ናቸው። ዲያቆናትም አገልጋዮች ናቸው። ንፍቀ ዲያቆናትም ረዳቶች ናቸው። አናጉንስጢሳውያንም በማስተዋል የሚያነቡ ናቸው። አብስሊድሳውያን መዘምራን ናቸው።
፭:- (ምእመናን) የትምህርቱን ቃል ያስተውሉ።
፱:- ለእግዚአብሔር ደስ የማያሰኘውን ሥራ አትሥራ።
፲:- ለራሳችሁ የሚበልጠውን ክፍል መውሰድን፣ ለወንድሞቻችሁ ግን ጥቂት መስጠትን አትውደዱ።
፲፰:- የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው ብሩህ ሕጉን የሚጠብቁ ሰዎች ይቅርታንና ምሕረትን ያገኛሉ። ለራስህ የምትጠላውን በባልንጀራህ ላይ አታድርግ። አንተ ሌላው ሰው ሚስትህን ያይ ዘንድ ማንም በተንኮል ያስታት ዘንድ እንደማትወድ እንደዚሁ አንተም የሌለውን ሚስት በክፉ ሕሊና አታስብ። ለራስህም መርገምን ስድብንና መመታትን እንደማትወድ እንደዚሁ አንተም በሌላው አታድርግ።
፲፱:- የረገመህም ቢኖር አንተ ግን መርቀው።
፳፪:- ወዳጆቻችን ሆይ የብርሃን ልጆች እንሆን ዘንድ ትእዛዛትን እናስተውል። እርስበእርሳችን ትዕግሥትን እንያዝ።
፳፫:- ወንድ ሚስቱን ይታገሣት። ትዕቢተኛና ግብዝም አይሁን። ነገር ግን የሚራራና ቅን ይሁን። ለብቻዋም በፍቅርና በትሕትና ደስ ያሰኛት።
፳፮:- የራስህን ጠጉር አታሳድግ፣ ጠጉርህን ቁረጥ።
፳፱:- ጽሕማችንን እንላጭ ዘንድ ለእኛ አይገባም።
፴:- እግዚአብሔርን ደስ ታሰኘው ዘንድ ከወደድህስ ክፉ ሥራን አትሥራ። ፈጣሪህም የሚጠላውን ሁሉ ከአንተ አርቅ። ሰካራም አትሁን። በእጆችህ ሥራ ትረህ ግረህ ተመገብ።
_አንቀጽ ፪_√
፩:- ሥራ ፈት ሆነህ አትኑር። በነገሥትና በነቢያት መጽሐፍ ውስጥ ያለውንም ተመልከት። የምስጋና መዝሙርን ዘምር። የሕግ ሁሉ ፍጻሜ የሚሆን የወንጌልንም ቃል ስማ።
፪:- ለማይረባ ለማይጠቅም ለከንቱ ነገር ሁሉ አትጨነቅ። ከወንጌል ልዩ የሚሆን ሕግንና ሃይማኖትን ለውጠው የሚያጠፉ ሐሰተኞች መምህራንን አትሻ።
፴፰:- በሃይማኖትና በጎ በመሥራትም እንጽና። ከክፉ ሥራም ሁሉ እንራቅ።
_አንቀጽ ፫_√
፩:- ሴት ለባሏ በትሕትና ትታዘዝ።
፳፰:- ክፉ ሴት ለራሷ ውርደትን ታመጣለች።
፴፪:- ያመኑ ሴቶች ራሳቸውን በንጽሕና ሊከናነቡ ይገባል። የፊታቸውን ውበት በማሳመርና ቀለም በመቀባት አይደለም። እግዚአብሔር በፈጠረው መልክ ውስጥ ጥቅም በሌለው ኩል መኳልና ማጌጥም አይደለም። እንዲህ ያለውን ሁሉ አይሥሩ። ነገር ግን እነርሱ ተከናንበው በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፪ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.6K views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 16:27:54 _የመበለት ዱላ_
መበለት ማለት አሮጊት ሴት ማለት ነው። የኔታ ቡሩክ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የነበሩ የመጽሐፍና የቅኔ መምህር ነበሩ። እና አንድ ቀን "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለ" ብለው ይናገራሉ። ይህን የሰሙ መበለቶች ዱላቸውን ይዘው የኔታን ሊደባደቡ ግርርርርር ይላሉ። ይህንን የተመለከቱ አንድ ሸምገል ያሉ ሰውየ "ቆይ እስኪ ከዱላው በፊት እንጠይቀው" ይሉና። ሄደው አንተን ብሎ መምህር ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለ ብለሃል አሉ እውነት ነው ይሏቸዋል። የኔታም "አዎ እውነት ነው ለእግዚአብሔርኮ የሚሳነው ነገር አለ" ብለው ይደግሙታል። የሰው ብስጭት ጨመረና "ምንድን ነው እግዚአብሔርን የሚሳነው?" ይሏቸዋል። የኔታም ሲመልሱ "ውሸት ነዋ" ብለው መለሱ። እግዚአብሔር ጻድቅነት የባሕርይው ነው ካልን ውሸት ይሳነዋል ማለት ነው ብለው ሲናገሩ ዱላ ይዞ የመጣው መበለት ሁሉ አፍሮ ወደየቤቱ ሄደ ብሎ አንድ የኔታን በቅርበት የሚያውቃቸው ሰው ነግሮኛል።

እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ ያለ ምሉዕ ነው፣ ጻድቅ ነው፣ ኃያል ነው ወዘተ ካልን ይህ የባሕርይው ስለሆነ አይለወጥም ማለት ነው። ምክንያቱም የባሕርይ ማለት የማይለወጥ የራስ የሆነ ነገር ማለት ነው። እግዚአብሔር አይለወጥም። እንደማይለወጥም በትን. ሚል. ፫፣፮ እንዲሁም መዝ. ፩፻፩፣፳፯ ተገልጿል። እግዚአብሔር ምሉዕነት የባሕርይው ከሆነ ምሉዕነቱን መተው አይችልም ማለት ነው። እግዚአብሔር ኃያልነት የባሕርይው ነው ካልን ኃያልነቱን አይተውም ማለት ነው። ነገረ ሥጋዌን ስንናገር እንኳ ቃል ቃልነቱን ሳይለቅ ሥጋን ሆነ ሥጋም ሥጋነቱን ሳይለቅ ቃልን ሆነ ነው የምንለው። ኃያሉ ኃያልነቱን ሳይለቅ ድኩም ሥጋን ተዋሐደ። የማይሞተው የማይሞትነትን ሳይለቅ የሚሞት ሥጋን ገንዘቡ አደረገ። ይህንም ተዐቅቦ በተዋሕዶ እንለዋለን። የአንድን ሰው ሐሳብ ምክንያቱን እና የሐሳቡን መነሻ ሳይረዱ በግምት መናገር አይገባም። ዱላን ከማንሳት መጠየቅ ይቀድማል። በተለይ ሴት ልጅ ጭምት ዝም ያለች በትሕትና የምትኖር መሆን አለባት። ፈጠን ፈጠን የምትል ቀባጣሪ መሆን የለባትም።
2.3K views13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 14:37:12
እስካሁን 92 ሰው ከፌስቡክ ገጼ unfriend አድርጌያለሁ። ወደፊትም ሥርዓት የሌለውን ሥርዓት የማስያዝ ሥራ እቀጥላለሁ።

ምእመናን ወምእመናት block መሸነፍ ነው። ብሎክ አላደርግም። unfriend ማድረግ ግን ሌላ ጓደኛ ለመቀበል ስለሆነ እንዳትቀየሙኝ። ዛሬ እጀምራለሁ። ከአስተያየታችሁ እንደተረዳሁት በእኔ ያዘናችሁ ሰዎች ካሁን በኋላ እንዳታዝኑብኝ ስል unfriend አደርጋችኋለሁ። ምክንያቱም ተረት ተረትን ወንጌል አስመስለው የሚያቀርቡትን እስከ መጨረሻው የምቃወም ነኝና።

ስለዚህ ፈቃደኛ የሆነ በራሱ መውጣት ይችላል። ያልሆነ ደግሞ እኔው እየመረጥኩ እለየዋለሁ። መልካም ቀን።

የፌስቡክ ገጼ https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው። ከዚህ ያላችሁ ከዚያ የሌላችሁ መቀላቀል ትችላላችሁ።
2.2K views11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 14:37:00 __ጦማር ዘጴጥሮስ__
ቁጥር ፬:- ለጥምቀት በዋጋ መማለጃ የተቀበለ የተሻረና የተወገዘ ነው።

ቁጥር ፭:- ልጄ ሆይ የክህነትን ስጦታና የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በገንዘብ አትሽጥ። በክህነት ላይ አትነግድ።

ቁጥር ፮:- በክህነት መማለጃ የሰጠም የተቀበለም ክህነት የለውም።

ቁጥር ፯:- የበደለህን በየሰባቱ ሰባ ጊዜ ይቅር በለው።

ቁጥር ፰:- ከኃጢአቱ ንስሓ የሚገባን ተቀበለው የበደለውንም ይቅር በለው። በእጅህም አንሣው ገሥጸውም። የታመሙትን ጎብኝ፣ የተራቡትን አብላ፣ የተጠሙትን አርካ፣ የተራቆቱትን አልብስ፣ ወደታሠሩትም ሂድ።

ቁጥር ፱:- ከእግዚአብሔር ቅዱሳት መጻሕፍትን ስማ።

ቁጥር ፲፩:- አባት እናት ለሌለው እራራለት። በራስህ ላይ ለሰይጣን መንገድ አትስጥ።

ቁጥር ፲፫:- ችግረኛ ካህን ካየህ ከተቀበልከው ገንዘብ እርዳው።

ቁጥር ፲፬:- ለአብያተ ክርስቲያናት፣ ለአድባራትና ለገዳማት ግንባታ ራስህን አትጋ።

ቁጥር ፲፯:- ችግረኛን ከቤትህ በር ላይ አታባረው። ቸል ቸል አትበለው። አትናቀው። አታቃለው። ከአንተ ጋርም በማዕድህ እንዲቀመጥ አድርገው።

ቁጥር ፲፱:- ምእመናንን ለመጥቀም ካልሆነ በስተቀር ወርቅና ብር አትሰብስብ።

ቁጥር ፳-፳፩:- ለምእመናን ልጆች ሰላምን አብዛ። ልጄ አረጋውያንን አክብራቸው። ነገራቸውንም ስማቸው። ገሥፀው ንገረው እንጂ በኃጢአቱ ምክንያት በሰው ላይ አትሳለቅ። እግዚአብሔርን ወደ መፍራትም በየዋህነት መልሰው።

ቁጥር ፳፪:- ቀጥተኛ በሆነ ነገር ነገሥታትን እዘዛቸው። በመጥፎ ሥራቸው ውቀሳቸው። ቁርባን መቁረብ ጥፋትን ይከላከላል።

ቁጥር ፳፫:- በ3ኛው፣ በ7ኛው፣ በ12ኛው፣ በ30ኛው፣ በ40ኛው፣ በ60ኛው ቀን ሙታንን አስቧቸው። ልጄ ሆይ የተጠመቀ ኃጢአተኛ ነፍሱ በሞተ በ40ኛው ቀን ከክርስቶስ ፊት እንደምትቀርብ እወቅ። እንደ ሥራውም ይከፈለዋል።

ቁጥር ፳፬:- ምእመናን የመለኮትን የተቀደሱ መጻሕፍት ለመስማት በእግራቸው ይቁሙ። ለመጠመቅ የሚፈልግን ሰው በውኃ ከመጠመቁ በፊት የደስታ ቅባት ቀባው። ከተጠመቀ በኋላ ደግሞ ቅብዐ ሜሮን ቀባው።

ቁጥር ፳፱-፴:- ያልተጠመቀ ሰው ያረደውን አይብሉ። የአይሁድን ቂጣ አትብሉ። ከእነርሱ ጋር አትጋቡ።

ቁጥር ፴፪:- አማኝ ሆይ መተኛት በፈለግህ ጊዜ ፊትህን አማትብ። ከሰማዕታት አፅም ተባረክ።

ቁጥር ፴፫:- ካህን ሆይ ከንጹሕ ስንዴ በቀር በመሥዋዕቱ ላይ ስብና ሥጋ አታቅርብ። በመሠውያው ላይም አታስቀምጥ። ከወይን ፍሬ በስተቀርም ከጠጅ መሥዋዕት አትሥራ። የስንዴ እሸት በደረሰ ጊዜ የተለቀመ ይሁን።

ቁጥር ፴፭:- የፋሲካ በዓል ከሁሉም በዓላት ይበልጣል። ይከብራልም። ከደስታ በስተቀር ሐዘን አይደረግበትም።

ቁጥር ፴፮:- በቅዳሴ ጊዜ ሙታንን ሁልጊዜ አስታውሱ። እጅግ ይጠቅማቸዋልና።

ቁጥር ፴፯:- ከቂጣ በዓል በኋላ በሚውለው እሑድ የፋሲካን በዓል አክብሩ።

ቁጥር ፵፬:- የሕጉን ታቦት ሁሉ ባርክ። በእግዚአብሔር ማኅተም አትመው። በምትባርከው ጊዜ ሰባት ቀሳውስት ከአንተ ጋር ይኑሩ። ክህነትን ለመስጠትም በቅብዐ ሜሮን አትም። እንዲሁም ንጉሥን ለማንገሥ አትም።

ቁጥር ፶፩:- ከሊቀ ካህናት ሳያገኝ ክህነትን ነጥቆ የወሰደ ሰው ቢኖር ከእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ይሰናበት።

ቁጥር ፶፪:- በሰንበታትና በበዓላት የዮሐንስን ወንጌል በመሠውያው ላይ ያንብቡ። እርሱ የመለኮትን ምሥጢር የሚናገር ነውና።

ቁጥር ፶፫:- በሁሉም ቤተ መቅደስ ውስጥ ሁለት መሠውያ ይኑር። አንዱ ከቦታ ወደቦታ የሚንቀሳቀስ፣ ሁለተኛው ከቦታው የማያነቃንቁት ይሁን።

ቁጥር ፶፯:- ሕዝባዊ ካህንን ቢሰድበው ወይም ቢረግመው እግዚአብሔር ከሚመለክባቸው አገሮችና ከቤተክርስቲያኑ ይሰደድ።

ቁጥር ፷:- ከምእመናን ኃጢአቱ የበዛ ሰው ቢኖርና እንዲወገድለት ቢፈልግ ኃጢአቱን ለካህን እና የእግዚአብሔርን መጻሕፍት ለሚያውቁ ሊቃውንት ይግለጣት።

ቁጥር ፷፪:- የክህነት ልብስ ከሌሎች ሕዝባውያን ልብሶች የተለየ ይሁን። ልብሱ ከመጠምጠሚያው በስተቀር ሰፊ ይሆን ዘንድ ይገባል።

ቁጥር ፷፬:- ካህን ቀን መዝሙረ ዳዊትን ያንብብ፣ ሌሊት ደግሞ የነቢያትን ምስጋና ያንብብ።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.9K views11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 14:18:47
እስካሁን 92 ሰው ከፌስቡክ ገጼ unfriend አድርጌያለሁ። ወደፊትም ሥርዓት የሌለውን ሥርዓት የማስያዝ ሥራ እቀጥላለሁ።

ምእመናን ወምእመናት block መሸነፍ ነው። ብሎክ አላደርግም። unfriend ማድረግ ግን ሌላ ጓደኛ ለመቀበል ስለሆነ እንዳትቀየሙኝ። ዛሬ እጀምራለሁ። ከአስተያየታችሁ እንደተረዳሁት በእኔ ያዘናችሁ ሰዎች ካሁን በኋላ እንዳታዝኑብኝ ስል unfriend አደርጋችኋለሁ። ምክንያቱም ተረት ተረትን ወንጌል አስመስለው የሚያቀርቡትን እስከ መጨረሻው የምቃወም ነኝና።

ስለዚህ ፈቃደኛ የሆነ በራሱ መውጣት ይችላል። ያልሆነ ደግሞ እኔው እየመረጥኩ እለየዋለሁ። መልካም ቀን።

የፌስቡክ ገጼ https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው። ከዚህ ያላችሁ ከዚያ የሌላችሁ መቀላቀል ትችላላችሁ።
1.7K views11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 12:40:34 __ቀኖና ቀሌምንጦስ ክፍል ፪_
ቀኖና ፶፰:- ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን ወይም ከካህናት ሌላው ያልታረደ ሥጋ የበላ፣ ወይም ተኩላ የነከሰው ወይም በክት ወይም ሌላ የሞተ ነገር የበላ ከሹመቱ ይሻር። ሕዝባዊ ከሆነም ይባረር።

ቀኖና ፶፱:- ከቀዳም ስዑር ውጭ ቅዳሜ እና እሑድ ሲጾም የተገኘ ካህን ከሹመቱ ይሻር። ሕዝባዊ ቢሆን ከቁርባን ይከልከል።

ቀኖና ፷፩:- ከሌላ ሰው ጋር የተጣላ ካህን ቢኖር ቢመታውና ቢሞትበት ከሹመቱ ይሻር። ሕዝባዊ ቢሆን ደግሞ ከቤተክርስቲያን ይሰናበት።

ቀኖና ፷፫:- ዳግመኛ የተሾመ ካህን ካለ ከሹመቱ ይሻር። የሾመውም ይሻር። [ቀድሞ የተሾመው ከከኃድያን ከሆነ ግን ያ ስለማይቆጠር ሁለተኛ ነው አይባልም]።

ቀኖና ፷፬:- ከአይሁድ በበዓላቸው ቂጣና የመሳሰሉ ስጦታዎችን የሚቀበል ካህን ከሹመቱ ይሻር። ሕዝባዊ ከሆነ ከሕዝብ ይለይ።

ቀኖና ፷፮:- ከካህናት ወይም ከምእመናን ለአይሁድ ምኩራብ ወይም ለአማልክት መስገጃ ቦታ ወይም ለጠንቋዮች ወይም ለከኃድያን አብያተ ክርስቲያን የሚያበሩት ዘይት ወይም መብራት ቢልክ ከቤተክርስቲያን ይሰናበት።

ቀኖና ፷፰:- ከተቀደሰ ልብስ ጀምሮ ሁሉም የቤተክርስቲያን ሀብት ወይም የብር ገንዘብ ሰው በቤቱ ሊሠራባቸው አይገባም።

ቀኖና ፸፩:- ኤጲስ ቆጶስ ክህነትን መውረስ ወይም ማውረስ አይገባውም።

ቀኖና ፸፰:- ወታደር ሆኖ የቤተክርስቲያን ሹም ለመሆን የሚፈልግ ካህን ካለ ይሻር።

ቀኖና ፸፱:- ከመሳፍንት አንዱ በፍርድ ሳይገፋው ያለ አግባብ ንጉሥን የሰደበ ወይም የረገመ ካህን ከሆነ ይሻር። ሕዝባዊ ከሆነ ይባረር።

ቀኖና ፹:- ለቀሌምንጦስ የነገርነው ፹፩ መጽሐፍ ነው። እነዚህም:-
፩) ኦሪት ዘፍጥረት
፪) ኦሪት ዘጸአት
፫) ኦሪት ዘሌዋውያን
፬) ኦሪት ዘኍልቍ
፭) ኦሪት ዘዳግም
፮) መጽሐፈ ኢያሱ
፯) መጽሐፈ መሳፍንት
፰) መጽሐፈ ሩት
፱) መጽሐፈ ዮዲት
፲) መጽሐፈ ጦቢት
፲፩) መጽሐፈ አስቴር
፲፪) መጽሐፈ መቃብያን (፫)
፲፫) መዝሙረ ዳዊት
፲፬) መጻሕፍተ ሰሎሞን (፭)
፲፭) መጻሕፍተ ነገሥት (፬)
፲፮) መጽሐፈ ሲራክ
፲፯) መጽሐፈ ኢዮብ
፲፰) መጽሐፈ ዕዝራ (፫)
፲፱) ትንቢተ ኢሳይያስ
፳) ትንቢተ ኤርምያስ
፳፩) ትንቢተ ሕዝቅኤል
፳፪) ትንቢተ ዳንኤል
፳፫) ትንቢተ አሞጽ
፳፬) ትንቢተ ዮናስ
፳፭) ትንቢተ ዕንባቆም
፳፮) ዖዝያ (ትንቢተ ሆሴዕ?)
፳፯) ትንቢተ ናሆም
፳፰) ትንቢተ ሶፎንያስ
፳፱) ትንቢተ ዘካርያስ
፴) ትንቢተ ሚኪያስ
፴፩) ትንቢተ ሚልክያስ
፴፪) ወንጌል (፬)
፴፫) መልእክታተ ሐዋርያት (፯)
፴፬) የጳውሎስ መልእክታት (፲፬)
፴፭) የሐዋርያር ሥራ
፴፮) ራእየ ዮሐንስ
፴፯) መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
ቀኖና ፹፩:- እንድትቀበሏቸው በቀሌምንጦስ እጅ ያዘዝናችሁ መጻሕፍት 8 የቀኖና መጻሕፍት ናቸው።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
መ/ር በትረማርያም አበባው
1.8K views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 12:21:20 __ቀኖና ዘቀሌምንጦስ ክፍል ፩__
ቀኖና ፩:- ሊቀ ጳጳሳት ያለ ኤጲስ ቆጶሳት ጉባኤና ያለ ጳጳስ መኖር አይሾምም።

ቀኖና ፪:- ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ እንዲሾም ያመጡት (የመረጡት) ሰው ሹመቱ የሚሰጠው በአገሩ ሰዎች ስምምነት ይሁን። የሚሾመው ጳጳስ ወይም ሊቀ ጳጳስ ይሁን። በሹመቱ ጊዜ ሁለት ወይም ሦስት ኤጲስ ቆጶሳት መኖር አለባቸው። ቄስና ዲያቆንን እንዲሁም ከዚያ በታች ያሉትን ኤጲስ ቆጶሱ ብቻውን ይሹማቸው።

ቀኖና ፫:- በቁርባን ጊዜ ሕግ ተላልፎ በመሥዋዕቱ ላይ ማር ወይም ወተት ወይም በወይን ፋንታ ስኳር ወይም ጠጅ ያቀረበ ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ቄስም ቢሆን ዲያቆንም ቢሆን ከክህነቱ ይሻር። ንጹሕ ከሆነ ስንዴ ኅብስትና ከጠራ የወይን ፍሬ በስተቀር ከአዕዋፍም ቢሆን ከእንስሳትም ቢሆን ይህን ያደረገ ከሹመቱ ይሻር። ስንዴው ያልከረመና የመጀመሪያ ፍሬ የሆነ ይሁን። የወይኑ ፍሬም ያልቆየ ፍሬውን ውኃ የሞላውና የሚጣፍጥ ይሁን።

ቀኖና ፮:- ቤተክርስቲያንን ለማገልገል የተመደበ ከዓለም ሥራ ምንም አይሥራ። እንደዚህ ቢሠራ ይሻር።

ቀኖና ፯:- ፋሲካን ከአይሁድ ፋሲካ ቀጥሎ ባለው ከእሑድ በስተቀር በአንድ ቀን ከእነርሱ ጋር ያደረገ ከሹመቱ ይሻር።

ቀኖና ፱:- በቅዳሴ ጊዜ ከምእመናን ወደ ቤተክርስቲያን የገባ ሰው ቢኖር ቅዱሳት መጻሕፍትንም ቢሰማ ቅዳሴ እስከሚጨርሱ ድረስ ባይታገሥ ቁርባንም ባይቀበል ከቤተክርስቲያን ይውጣ። በሰማያዊ ንጉሥ ፊት መቆምን አቃሏልና።

ቀኖና ፲:- በውግዘት ምክንያት እንዳይቆርብ ከተከለከለና ከተባረረ ሰው ጋር የተነጋገረ ወይም በጸሎት የተሳተፈ ወይም ለምሳ ወደ ቤቱ የጠራው ሰው ቢኖር ይባረር።

ቀኖና ፲፪:- ካህኑን የሾመው ኤጲስ ቆጶስ ሳይፈቅድለት አገሩን ትቶ ወደሌላ ሀገር የሄደ ካህን ቢኖር እንደካህን ቆጥረው አይቀበሉት። ቢቀበሉት ግን የተቀበለውም ይባረር። እርሱም ይባረር።

ቀኖና ፲፯:- ካህን ድንግል ያልሆነችውን ቢያገባ በማናቸውም የክህነት መዓርግ ላይ ሊሾም አይገባም።

ቀኖና ፲፰:- የእኅቱን ልጅ ወይም የወንድሙን ልጅ ያገባ ካህን ቢኖር ከክህነት መዓርግ በየትኛውም ላይ ሊሾም አይገባውም።

ቀኖና ፳፫:- ራሱን የሰለበ ምእመን ቢኖር ለሦስት ዓመታት ከቤተክርስቲያን ይታገድ። ካህን ቢሆን ከሹመቱ ይሻር።

ቀኖና ፳፬:- ካህን ቢሰርቅ፣ በዝሙት ቢገኝ፣ በሐሰት ሲምል ቢገኝ ከክህነቱ ይሻር።

ቀኖና ፳፮:- ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን አንድን አማኝ ቢማታ ከመዓርጉ ይሻር።

ቀኖና ፳፯:- ባደረሰው በደል ምክንያት ወይም በትክክል በሥልጣነ ክህነት ከእርሱ በሚበልጠው ሰው ሥልጣኑ በመያዙ ከቤተክርስቲያን የተባረረ ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ዲያቆንም ቢሆን ይህ የሥልጣን መያዝና ግዝት ሳያግደው ያለፍርሀትና ያለመገረም በግድ አገልግሎቱን ቢቀጥል ውግዘቱን አቃሎም ቢያገለግል እስከ መጨረሻው ከቤተክርስቲያን ይወገድ።

ቀኖና ፴፪:- አንድ ኤጲስ ቆጶስ ከሩቅ ሀገር የመጡ ሌላ ኤጲስ ቆጶስን ወይም ቀሳውስትን ወይም ዲያቆናትን አይቀበል። ማንነቱን የሚገልጽ ደብዳቤ ያለው ካልሆነ በስተቀር እንደ ካህናት አያድርጉት። ደብዳቤ ካላቸው ምግባራቸውን ይጠይቁ።

ቀኖና ፴፬:- ጳጳስ ባልተሾመበት ሀገረ ስብከት ቀሳውስትንና ዲያቆናትን መሾም አይገባውም። ሕግ ከተላለፈና ያለዚያ ሀገረስብከት ሰዎች ፈቃድ እንደዚህ ካደረገ ይሻር። የሾማቸውም ይሻሩ።

ቀኖና ፴፭:- ኤጲስ ቆጶስ ከግማሽ በላይ ያሉ ምእመናን ከመረጡት ይሾም። ከዚህ በኋላ የሚቃወሙ ካህናት አይኑሩ። ካሉ ግን አልተስማሙምና ይሻሩ።

ቀኖና ፵፪:- ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ቄስም ቢሆን ዲያቆንም ቢሆን ከአበደረው ገንዘብ ወለድ የሚፈልግ ከሆነ ይህን ሥራውን ካልተወና ካልተመለሰ በስተቀር ከመዓርጉ ይሻር።

ቀኖና ፵፭:- ያለምክንያት ሚስቱን ከቤቱ ያስወጣት ወይም ሌላዋን በዝሙት የተፈታችውን ሴት ያገባ ሕዝባዊ ሰው ቢኖር ከቤተክርስቲያን ይሰናበት።

ቀኖና ፵፮:- እግዚአብሔር የፈጠረው ጥሩ እንዳልሆነ የሚሳደብና የሚክድ ከእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ይሻር።

ቀኖና ፶:- ኤጲስ ቆጶስን የሰደበ ወይም የረገመ እንደ ሰነፍም የቆጠረ ከመዓርጉ ይሻር። እንደዚሁም ኤጲስ ቆጶስ ካህንን ቢረግም ወይም ቢሳደብ እርሱም ይሻር።

ቀኖና ፶፩:- ከካህናት ወገን ወይም ከምእመናን ቄስን ወይም ዲያቆንን የሰደበ ወይም የረገመ ቢኖር አስቀድመን እንደተናገርነው ይለይ።

ቀኖና ፶፪:- ከካህናት ወገን ወይም ከሕዝባውያን መስማት በተሳነው ሰው ላይ ወይም በዕውር ወይም በአንካሳ ወይም ድውይ ወይም ሽባ ላይ የተሳለቀ ወይም የሳቀ ሰው ቢኖር ይሻር።

ቀኖና ፶፫:- ኤጲስ ቆጶስ ሕዝቡን ባያስተምራቸው ይሻር።

ቀኖና ፶፬:- በአንድ አገር ላይ የተሾመ ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ቢኖርና ከካህናት የተቸገረ ሰው አይቶ የሚፈልገውን ባይሰጠው ችግሩንም ባያስወግድለት በአጋጠመው ችግርም ባይረዳው ይሻር።

ቀኖና ፶፯:- ከካህናት ወገን ወይም ከሕዝባውያን አይሁድን ወይም አረመኔን በመፍራት የእግዚአብሔርን ሕግ የካደ የሕጉን ሥራም ያልገለጸ የክርስቶስን ስም ለመካድና ለመበደልም መርሕ የሆነ ከመዓርጉ ይሻር። ንስሓ ከገባ ግን ከምእመናን ወገን አድርገው ይቀበሉት።


ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
መ/ር በትረማርያም አበባው
2.0K views09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 18:38:34 __ቀኖና ዘስምዖን ቀነናዊ__
ቁጥር ፫:- ኤጲስ ቆጶስ ይባርክ እንጂ አይባረክ። በሰዎች ራስ ላይ እጁን ይጫን። በእርሱ ላይ ግን ከሊቀ ጳጳሳት በስተቀር ማንም እጁን የሚጭን የለም።

ቁጥር ፬:- ቄስ ካህናትን አይሹም። ግን ቀሳውስትና መነኮሳት የገዳማት አስተዳዳሪዎች ከሆኑ ወደእነርሱ ለምንኩስና የመጣውን በገዳማቸው የፈለጉትን በአንድነት ያመንኩሱ።

ቁጥር ፭:- ሊቀ ጳጳሳት መሻር የሚገባቸውን ሁሉ ይሽራል። ሊቀ ጳጳሳትን ግን መሻር የሚቻለው እንደእርሱ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳትና የኤጲስ ቆጶሳት አንድነት ባሉበት ነው።

ቁጥር ፮:- ቄስ በዲያቆናትና ከእነርሱ በታች በሆኑ ሕዝባውያን ራስ ላይ እጁን ይጫን ይባርክም።

ቁጥር ፯:- ዲያቆን አይባርክም። በመዓርግ ከእርሱ በላይ ለሆኑት ደሙን ሊያቀብል አይችልም። በቤተክርስቲያን አገልግሎት ዲያቆን ከእርሱ የሚያንሰውን ማዘዝ ይችላል። በመዓርግ ከእርሱ የሚበልጠውን ግን ማዘዝ አይችልም። ዲያቆን ቀድሞ ጸሎት ማስጀመር አይገባውም።

ቁጥር ፱:- በቤተክርስቲያን ካለው ሁሉ አራት እጁ ለኤጲስ ቆጶስ ነው። ሦስት እጁ ለቄስ፣ ሁለት እጁም ለዲያቆን ነው። ለሌሎች ሰዎች አንድ አንድ እጅ ነው።የእንስሳት በኩር ለካህናት ብቻ ይገባል

ቁጥር ፲:- በነጋ ጊዜ ምእመናንና ምእመናት ሳይታጠቡ ምንም ሥራ አይሥሩ። ከዚያም ራስን በማስገዛት ወደ ፈጣሪያቸው ይጸልዩ።

ቁጥር ፲፪-፲፬:- ሠራተኞች በየሳምንቱ ሁለት ቀን እንዲያርፉ አዘዝን። እነርሱም ቅዳሜና እሑድ ናቸው። ቤተክርስቲያንን ለማገልገልና እግዚአብሔርን ለመፍራት ለመዘከር ይገናኙባቸው። ቅዳሜ የምታርፉት እግዚአብሔር ያረፈባት ቀን ስለሆነች ነው። እሑድ የምታርፉት የዕለታት መጀመሪያ ስለሆነች ነው። በተጨማሪም የትንሣኤው ዕለት ስለሆነች ነው። በመጨረሻው ሰዓት ፍርድና ኩነኔ የሚሰጥባትም ዕለት ናት።

ቁጥር ፲፭:- ምእመናን በሰሙነ ሕማማትና በሰሙነ ትንሣኤ እስከ ዳግማይ ትንሣኤ ድረስ ዕረፍት ያድርጉ። ሰሙነ ሕማማት ጌታ በሰውነቱ መከራ የተቀበለባትና የኀዘን ሳምንት ናትና። ሰሙነ ትንሣኤም የደስታ ሳምንት ነውና።

ቁጥር ፲፮-፳፫:- ምእመናን በዕርገት በዓል ይረፉ። በጰራቅሊጦስም ይረፉ። በዕለተ ብሥራትም (መጋቢት ፳፱) ይረፉ። በዕለተ ልደትም (ታኅሣሥ ፳፱) ይረፉ። በጥምቀት ዕለትም (ጥር ፲፩) ይረፉ። በዕለተ ስምዖንም (ግዝረተ ኢየሱስ) (የካቲት ፰) ይረፉ። በዕለተ ደብረ ታቦርም (ነሐሴ ፲፫) ይረፉ። በሐዋርያት የመታሰቢያ ቀንም ይረፉ። በእስጢፋኖስ በዓልም ይረፉ። በሌሎች ሰማዕታትና ቅዱሳን በዓልም ይረፉ።

ቁጥር ፳፭-፴፩:- የጸሎት ጊዜያት (ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት፣ ጸሎተ ሠለስቱ ሰዓት፣ ጸሎተ ነግህ፣ ጸሎተ ስድስቱ ሰዓት፣ ጸሎተ ተስዓቱ ሰዓት፣ ጸሎተ ሠርክ፣ ጸሎተ ምሴት፣ ጸሎተ መንፈቀ ሌሊት)። ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት የምንጸልየው ጌታ ለመፍረድ ይመጣል ብለን ተስፋ ስለምናደርግ ነው። ጠዋት የምንጸልየው ጨለማውን አስወግዶ ብርሃኑን ስላመጣልን ነው። ሦስት ሰዓት የምንጸልየው በክርስቶስ ላይ ሞት ስለፈረዱበት ነው። ስድስት ሰዓት የምንጸልየው ጌታ ስለተሰቀለባት ነው። ዘጠኝ ሰዓት የምንጸልየው የጌታ ነፍስ ከሥጋው ስለተለየባት ነው። በሠርክ የምንጸልየው ዕረፍትን ስላመጣልን ነው። በመኝታ ሰዓት የምንጸልየው ከጨለማ ፍጥረታት እንዲጠብቀን ነው።

ቁጥር ፴፫:- ምእመናን ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ባይቻላቸው በኤጲስ ቆጶሱ ቤት ይሰብሰቡ። በኤጲስ ቆጶሱ ቤት መሰብሰብ ባይችሉ እያንዳንዱ በያለበት ይጸልይ። ወይም ሁለትም ሦስትም ሆነው ይጸልዩ። አማኝ ከማያምኑ ሰዎች ጋር በአንድ ቤት ይጸልይ ዘንድ አይገባውም።

ቁጥር ፴፭-፴፮:- ለሞቱ ሰዎች በሦስተኛው ቀን፣ በሰባተኛው ቀን፣ በሠላሳኛው ቀን፣ በዓመቱ መታሰቢያ ያድርጉላቸው። ለሙት ዓመቱ ዕጣን ያሳርጉለት፣ ከገንዘቡም ለድሆችና ለምስኪኖች ይመጽውቱለት። ለዓላውያን ለከኃድያን ግን ይህን ሊያደርጉላቸው አይገባም።

ቁጥር ፴፱:- ለቀደሙት አባቶቻችን መጽሐፍ ወይን እንዳይጠጡ አላዘዛቸውም። ነገር ግን ለመስከር ወይን አትጠጡ ይላል።

ቁጥር ፵፪:- በሃይማኖት ምክንያት ካሳደዷችሁ ወደሌላኛዋ ሀገር ሽሹ።

ቁጥር ፶፬:- ዲያቆን በእጁ ያቆርብና ያጠምቅ ዘንድ ሕዝብንም ይባርክ ዘንድ አይገባውም።

ቁጥር ፶፮:- ከእኛ ከሐዋርያት ሊቃነ ካህናት ሦስት ወገን ነን፣ ቀሳውስትም በልዩ ሦስት ወገን ናቸው፣ ዲያቆናትም ሦስት ወገን ናቸው እነዚህም ዲያቆናት ንፍቅ ዲያቆናትና አናጉንስጢስ ናቸው።

ቁጥር ፶፱-፷:- ቅዱስ እስጢፋኖስ እስከ ዕለተ ሞቱ በዲቁናው ጸንቷል። ፈጽሞ ቁርባን አላቆረበም። በማንም ላይ እጁን አልጫነም።

ቁጥር ፷፪:- ኢትዮጵያዊው ጃንደረባን ያጠመቀው ፊልጶስና ጳውሎስን ያጠመቀው ሐናንያ ክህነትን ከሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀብለው አጠመቁ።

ቁጥር ፷፮:- ጋኔን ላደረበት ሰው ጋኔኑ እስኪተወው ድረስ ቁርባን አያቁርቡት። ለሞት የሚደርስ ከሆነ ግን ይቀበሉት። ቁርባንም ያቁርቡት።

ቁጥር ፷፰:- ሴት ዘማዊት ብትሆን የዝሙት ሥራን ትተው። እምቢ ካለች ከእኛ ትባረር።

ቁጥር ፷፱-፸:- ወንድ ወይም ሴት ወደ ሕጋችን መግባት ቢፈልጉ ሰካራም ወይም ጣዖት አምላኪ፣ ተዋናይ ወይም ዘፋኝ፣ ወይም ዘፈን የሚያስተምር፣ ወይም ወደዝሙት የሚገፋፋ ቢሆን ሥራውን ይተው። እምቢ ካሉ ግን ከማኅበራችን ወጥተው ይባረሩ።

ቁጥር ፸፩:- ወታደር ከዝርፊያ፣ ከቅሚያና ከበደል ይራቅ። በሚሰጡት ደመዎዝ ይኑር። ከዝርፊያ ከቅሚያ ከበደል ካልራቀ ግን ይባረር።

ቁጥር ፸፯:- ወደ ዘፈንና ወደ ዳንኪራ በጭፈራ ቤትም ወደሚደረገው ፉከራ ወይም ወደሚገዳደሉበት የሚሄድ ካለ ይመለስ። ሥራውንም ይተው የአረመኔ ሥራ ነውና። እምቢ ካለ ይለይ።

ቁጥር ፸፰:- ለሰው መልካም ነገርን የሚያስተምር ሕዝባዊ ቢኖር በቃሉ ጭምት ይሁን። በሥጋው ደግ ይሁን። አይኩራራ። አንደበተ ርቱዕ ይሁን። ከዚያ በኋላ ሰውን ያስተምር።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
መ/ር በትረማርያም አበባው
2.4K views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 17:00:26
2.2K views14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ