Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 249

2022-05-21 11:25:09 #Samara_University

10ኛው ሀገር ዐቀፍ የቱሪዝም ጥናት እና ምርምር ኮንፈረንስ በሠመራ እየተካሄደ ነው።

የክልሉን የቱሪዝም ሀብት ማስተዋወቅና በጦርነት እና በኮሮቪድ-19 ወረርሽኝ የተቀዛቀዘውን የጎብኚዎች ፍሰት ማነቃቃት የጉባኤው ዓላማ መሆኑ ተገልጿል።

በቱሪዝም የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች በመድረኩ ለውይይት እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።

ኮንፈረንሱን የኢትዮጵያ ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዮት፣ የአፋር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና የሠመራ ዩኒቨርስቲ በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡

@tikvahuniversity
15.1K viewsedited  08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 11:06:58
#Bahir_Dar_University

የጨርቃ ጨርቅ እና ፋሽን ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ፣ ባዛርና ኤግዚቢሽን በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።

በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ግቢ በተከፈተው አውደ ርዕይ ሸማች እና አምራቾች እየተገበያዩ ይገኛሉ።

በጉባዔው ጥናታዊ ፅሁፎችና የልምድ ተሞክሮዎች የቀረቡ ሲሆን የጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ውጤቶችም ለእይታ ቀርበዋል።

ዛሬ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ዓለም ዐቀፍ የፋሽን ትርዒት የሚቀርብ ሲሆን የመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ይሆናልም ተብሏል።

ጉባዔው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በኢትዮጵያ ቴክስታይል ኢንስቲትዩት በጋራ ተዘጋጅቷል።

@tikvahuniversity
17.1K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 22:18:07
#Addis_Ababa_Education_Bureau

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የአካዳሚክ ካላንደር ማሻሻያ አድርጓል።

የ8ኛ ክፍል ከተማ ዐቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29/2014 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።

የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 20 እስከ 23/ 2014 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል።

የውጤት ማስረጃ የሚሰጥበት ቀን ሐምሌ 05/2014 ዓ.ም።

(ዝርዝር መረጃው ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
8.5K views19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 21:16:02
#Werabe_University

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም መደበኛ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ ከ3 ሺህ 200 በላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበውለታል።

የመማር ማስተማር ሥራ ከጀመረ ወዲህ ዘንድሮ ለአምስተኛ ዙር አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የሚቀበለው ዩኒቨርሲቲው፤ መደበኛ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ግንቦት 15 እና 16/2014 ዓ.ም ለመቀበል ጥሪ አድርጓል።

ለአዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መኪናዎች መዘጋጀታቸውን የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት መሀመድ አዎል (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል።

በ2010 ዓ.ም የማስተማር አገልግሎት መስጠት የጀመረው ወራቤ ዩኒቨርሲቲ አሁን ላይ ከ5 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በተከታታይ መርሃ ግብሮች በማስተማር ላይ ይገኛል።

@tikvahuniversity
11.8K views18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:14:12
#የትምህርትና_ሥልጠና_ባለሥልጣን

በርካታ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የሚታደልባቸው እየሆኑ መምጣታቸው ተገለጸ።

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርጓል።

ሕገ-ወጥ የትምህርት ማስረጃ እና ሕገ-ወጥ ተቋማት መበራከታቸውን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አንዱዓለም አድማሴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ተቋሙ የተሰጠውን አገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ለመፈጸም የሚያስችል የሰው ኃይል አደረጃጀት አለመኖሩንም ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።

የቋሚ ኮሚቴው ስብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበርካታ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚታየውን የሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እደላ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ቀልጣፋና ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ከዓለም ባንክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ባለ ሰባት ወለል ህንጻ ለማስገንባት በሂደት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

@tikvahuniversity
14.5K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:58:13
#የኢንፎርሜሽን_ቴክኖሎጂ_ውድድር

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተሻለ የፈጠራ ሥራ ያላቸውን ባለሙያዎች እውቅና መስጠት እና ሥራዎቻቸውን ማስተዋወቅ እንደሚፈልግ ገልጿል።

ኅብረተሰቡን የሚጠቅምና ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸው የፈጠራ ሥራ ያላችሁ እስከ ግንቦት 19/2014 ዓ.ም አዲስ አበባ አምስት ኪሎ በሚገኘው የተቋሙ ቢሮ ማቅረብ ትችላላችሁ ተብሏል።

• በኢ-መንግስት ሶሉሽን፣
• በሶፍትዌር ልማት፣
• በሮቦቲክስ፣
• በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ/ዳታ ሳይንስ እና ሌሎችም መሰል ዘርፎች የፈጠራ ሥራ ያላችሁ ማመልከት ትችላላችሁ።

የፈጠራ ሥራዎቹ ቢሮው በሚያዘጋጀው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ላይ ይቀርባሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity
18.2K views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:06:06
#Haramaya_University

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን አዲስ የተመደቡ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች መግቢያ ከግንቦት 12 እስከ 14/2014 ዓ.ም መሆኑን የገለጸ ቢሆንም ከትላንት ምሽት ጀምሮ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው አዲስ አበባ እና አዳማ ከተሞች ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያስተባብሩ ሰዎች መመደቡን በዩኒቨርሲቲው የፍሬሽማን ፕሮግራም ዳይሬክተር ጌታቸው ተሾመ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ተማሪዎች የተመደቡትን ካምፓስ እና የመኝታ ክፍል በበይነ መረብ አማካኝነት እንዲያውቁ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከ5 ሺህ 100 በላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበውለታል።

@tikvahuniversity
18.8K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 13:45:40
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርትዎን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በ4 ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነውም ይመረቃሉ።

ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ መልክ የተደራጁ የመማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ-መፅሀፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ-ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982363636
0978028655

#BITSCollege
18.0K viewsedited  10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:30:44
#Ethiopian_Civil_Service_University

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በመደበኛ፣ በክረምት፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መእሃ ግብሮች ለመማር የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ግንቦት 20 እና 21/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል።

(የትምህርት ክፍሎች እና ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
18.9K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 11:59:12
#Fake_News_Alert

በ2015 ዓ.ም የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ባሉበት የትምህርት ደረጃ እንዲቀጥሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ተናገሩ በሚል በማኅበራዊ የትስስር ገጾች የሚዘዋወረው መረጃ #ሐሰት መሆኑን እንገልጻለን።

ቲክቫህ እንደዚህ አይነት ዘገባ አለመስራቱንም ልናረጋግጥ እንወዳለን።

ሀሰተኛ፣ የተዛቡ እና ያልተረጋገጡ መረጃ ከሚያሰራጩ የማኅበራዊ ሚዲያ አካውንቶች ራስዎን ይጠብቁ፡፡

ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስቴር አድራሻ፦

https://www.facebook.com/fdremoe

ትክክለኛው የቲክቫህ ኢትዮጵያ አድራሻ፦

https://t.me/tikvahethiopia

ትክክለኛው የቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድራሻ፦

https://t.me/TikvahUniversity

@tikvahuniversity
22.8K viewsedited  08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ