#Samara_University 10ኛው ሀገር ዐቀፍ የቱሪዝም ጥናት እና ምርምር ኮንፈረንስ በሠመ | Tikvah-University
#Samara_University
10ኛው ሀገር ዐቀፍ የቱሪዝም ጥናት እና ምርምር ኮንፈረንስ በሠመራ እየተካሄደ ነው።
የክልሉን የቱሪዝም ሀብት ማስተዋወቅና በጦርነት እና በኮሮቪድ-19 ወረርሽኝ የተቀዛቀዘውን የጎብኚዎች ፍሰት ማነቃቃት የጉባኤው ዓላማ መሆኑ ተገልጿል።
በቱሪዝም የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች በመድረኩ ለውይይት እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።
ኮንፈረንሱን የኢትዮጵያ ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዮት፣ የአፋር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና የሠመራ ዩኒቨርስቲ በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡
@tikvahuniversity