#Bahir_Dar_University
የጨርቃ ጨርቅ እና ፋሽን ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ፣ ባዛርና ኤግዚቢሽን በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።
በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ግቢ በተከፈተው አውደ ርዕይ ሸማች እና አምራቾች እየተገበያዩ ይገኛሉ።
በጉባዔው ጥናታዊ ፅሁፎችና የልምድ ተሞክሮዎች የቀረቡ ሲሆን የጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ውጤቶችም ለእይታ ቀርበዋል።
ዛሬ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ዓለም ዐቀፍ የፋሽን ትርዒት የሚቀርብ ሲሆን የመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ይሆናልም ተብሏል።
ጉባዔው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በኢትዮጵያ ቴክስታይል ኢንስቲትዩት በጋራ ተዘጋጅቷል።
@tikvahuniversity