2022-05-31 11:16:56
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 'የቃልኪዳን ቤተሰብ' ፕሮጀክት ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የ"አንድ ተማሪ አንድ ቤተሰብ" የቃልኪዳን ፕሮጀክት ከጀመረ ሦሥት ዓመታትን አስቆጥሯል።
"የቃልኪዳን ቤተሰብ" በመባል የሚታወቀው ፕሮጀክቱ፤ በዩኒቨርሲቲው አዲስ ገቢ ተማሪዎች እና በጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መካከል ጥብቅ ትስስር የሚፈጥር ነው።
ፕሮጀክቱ ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች የእንግድነት ስሜት እንዳይኖራቸው እና የባህልና ቋንቋ ትስስርን ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።
በተማሪዎች እና በቃልኪዳን ቤተሰባቸው መካከል የትስስርና የቤተሰብነት የቃልኪዳን የስምምነት ፊርማ ይከናወናል።
የስምምነት ውሉ የሚደረገው በተማሪው እና ፍቃደኛ በሆነው ቤተሰብ መካከል ሲሆን በሦሥት ቅጅ ተሞልቶ አንዱ ቅጅ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛው ቅጅ ለቃልኪዳን ቤተሰብ እንዲሁም ሦሥተኛው ቅጅ ለቃልኪዳን ተማሪ የሚሰጥ ነው።
ፕሮጀክቱ ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ወቅት የብቸኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን ከ5 ሺህ 300 በላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎች መቀበሉ ይታወሳል።
@tikvahuniversity
16.4K viewsedited 08:16