Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.08K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 247

2022-05-29 14:44:31
#OdaBultumUniversity

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የኮምፒዩተርና ቨርቺዋል ኤሌክትሮኒክስ ማዕከላት አስመርቋል።

ማዕከላቱ ስቴም ፓወር በተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ድጋፍ የተደራጁ መሆኑ ተገልጿል።

ድርጅቱ 31 ኮምፒዩተሮች ከ3ዲ ማተሚያና ቨርቺዋል ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ጋር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ለሁለት ዓመት ሥራ ማስኬጂያ የሚሆን የበጀት ድጋፍም አድርጓል።

እያንዳንዱ ማዕከል በአንድ ግዜ ከ30 ለሚበልጡ ተማሪዎች አገልግሎት መስጠት ይችላል።

ማዕከላቱ ተማሪዎች የሚማሩትን በተግባር እንዲሞክሩና ወደ ፈጠራ ሥራ እንዲቀይሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
14.4K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 11:21:44
የቴክኒክና ሙያ ምዘናን ወደ ዓለም ዐቀፍ ደረጃ የሚያሸጋግር ስምምነት ተፈረመ።

በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ መካከል ሲደረግ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ምዘናን ወደ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያሳድጋል የተባለው ፕሮጀክት በሦሥቱ አገሮች ተፈርሞ ጸድቋል።

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና የሚመረቁ ተማሪዎችና መምህራን በሦሥቱ አገሮች ተንቀሳቅሰው የመስራት ዕድል ይፈጠርላቸዋል ተብሏል፡፡

ስምምነቱ በዘርፉ ቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ ተወዳዳሪነት ያላቸው ምሁራንን ለማፍራት ያስችላል መባሉን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

የሦሥቱ አገሮችን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለማሳደግ በዓለም ባንክ የሚደገፍ "የምስራቅ አፍሪካ አገሮች የክህሎት ሽግግር (EASTRIP)" የተባለ ፕሮጀክት ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል፡፡

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ባዘጋጀው ዓውደ ጥናት ላይ እንደተገለጸው፤ ሦሥቱ አገሮች የተስማሙበት ወጥ የሆነ የጋራ የምዘና ሥርዓት ሲሠራ ቆይቶ የኬንያ እና ታንዛኒያ ሚኒስትሮች በተገኙበት ስምምነት ሆኖ ጸድቋል፡፡

በስምምነቱ መሠረት ኢትዮጵያ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ቀጠናዊ የምዘና መስጫ ማዕከል እንደምትሆን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አሰግድ ጌታቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እስካሁን በቴክኒክና ሙያ እስከ ደረጃ ስምንት ሥልጠና ትሰጥ የነበረ ሲሆን ስምምነቱ እስከ 10 እና 11 ደረጃዎች ከሚሰጡ አገሮች ጋር መደረጉ በኢትዮጵያ የሚሰጠውን ደረጃ እንደሚያሳድገው ሪፖርተር ዘግቧል።

@tikvahuniversity
16.0K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 10:58:09
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲያካሂድ የቆየውን የመጀመሪያ ሀገር ዐቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አጠናቋል።

ጉባኤው "መቻቻል እና አብሮ መኖር ለዘላቂ ልማት" በሚል ጭብጥ እንዲሁም በአገው ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክ ላይ መክሯል።

በኮንፈረንሱ በአዊኛ ቋንቋ ላይ ያተኮሩ የምርምር ሥራዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የአዊኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል ከመክፈት ባለፈ የአዊ ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክ ተቋም ማቋቋሙን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በተደረገው ሀገር ዐቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ 13 የምርምር ሥራዎች ቀርበዋል።

@tikvahuniversity
14.0K views07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 10:46:25
#ማስታወሻ
#ScholarshipTip

መልቲቾይስ አፍሪካ/DSTV በየዓመቱ ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የአንድ ዓመት የፊልም ጥበብ ስኮላርሺፕ ይሰጣል።

የመልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ የስኮላርሺፕ ዕድል ወጣት ባለሙያዎችን ኬንያ በሚገኘው የመልቲቾይስ አካዳሚ የፊልም ጥበብ እውቀታቸውን የሚያጎለብቱበት ዕድል ይፈጥራል።

እድሚያችሁ ከ18-30 የሆነ ወጣቶች እስከ ግንቦት 26/2014 ዓ.ም ተከታዩን ሊንክ በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ፦

www.multichoicetalentfactory.com

ለበለጠ መረጃ፦

https://cte.multichoicetalentfactory.com/Master/entrycriteria

(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
12.8K viewsedited  07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 10:44:25
#FreelanceEthiopia

በትርፍ ሰዓትዎ ከሚሰርዋቸው ሥራዎች ጀምሮ እንደ ትምህርት ደርጃዎ፣ የሥራ ልምድዎ እና ፍላጎትዎ በሁሉም አይነት ዘርፎች ሁሉንም አይነት ሥራዎች በአንድ ቦታ ያገኛሉ።

ለመቀላቀል ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦

https://t.me/+HZktkFNrwzg3Y2Fk
12.1K views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 10:42:15
#Golden_Sales_and_Marketing_Institute

ቢዝነስዎን ማሳደግ ይፈልጋሉ?
ክህሎትዎንስ ማዳበር ይፈልጋሉ?

ጎልደን የሽያጭ እና ማርኬቲንግ ተቋም

ፕሮፌሽናል የሽያጭና ክህሎት ስልጠና
ቢዝነስዎን ለማሳደግ የሚያስችል
ስልጠና
ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና
የሥራ እድሎች
የሙያ ብቃት COC ማረጋገጫ
አዲስ ክህሎት ለመገንባት

አድራሻ፦ ቦሌ፣ መገናኛ፣ ፒያሳ እና ሜክሲኮ ያገኙናል

ለበለጠ መረጃ፦

0941552035
0941811825

#Golden_Sales_and_Marketing_Institute
14.1K viewsedited  07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 22:29:46
#ስፖርት ፦ ዛሬ ምሽት በመላው ዓለም የእግር ኳስ ወዳጆች ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ይካሄዳል።

የዚህ የዋንጫ ፍልሚያ የሚካሄደው በሊቨርፑል እና ሪያልማድሪድ መካከል ሲሆን በመላው ዓለም ሚሊዮኖች ይህንን ጨዋታ ይከታተሉታል።

የስፖርት ወዳጅ የሆናችሁ የቤተሰባችን አባላት ጨዋታውን የተመለከቱ መልዕክቶች እንዲሁም ጎሎች በቲክቫህ ስፖርት በኩል ይደርሳችኃል https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport
5.8K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 17:11:52
ዲላ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የምርምር መፅሔት ይፋ አድርጓል።

ጆርናሉ በተለያዩ መስኮች በተለይ ትምህርት ላይ በማተኮር የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮችን ተቀብሎ በመመዘን የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

Dilla Journal of Education የተሰኘው የምርምር ህትመት፤ በዩኒቨርሲቲው የትምህርት እና ስነ-ባህሪ ተቋም የሚዘጋጅ ነው።

መፅሔቱ ከቀናት በፊት አምስት ምርምሮችን ለንባብ ማብቃቱን የተቋም ዲን መስፍን ሞላ (ዶ/ር) ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በተለይም የማስተማር ስነ-ዘዴ፣ የትምህርት ጥራት፣ የትምህርት ልማት እና መሰል ጉዳዮች ላይ የሚያከናውናቸውን ጥናትና ምርምሮች የሚወጡበት ጆርናል ያስፈልገው እንደነበር ገልጸዋል።

የትምህርት እና ስነ-ባህሪ ተቋም ሦሥተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የሚሰሯቸውን ምርምሮች ለህትመት ለማብቃት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።

የምርምር መፅሔቱ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ በትምህርት ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን ከሚያትሙ አምስት መፅሔቶች አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
15.9K views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 15:26:29
የሰላም ሚኒስቴር ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሰላም ኮንፈረንስ በባሌ ሮቤ አካሂዷል፡፡

ኮንፈረንሱ “የብሔራዊ ምክክሩ እድሎችና ፈተናዎች” በሚል መሪ ሀሳብ ላይ መክሯል፡፡

ጉባኤው አካታች ብሔራዊ ምክክሩን ለማሳካት ምሁራን የሚኖራቸው ሚና ላይም መክሯል፡፡

በኮንፈረንሱ ላይ ማኅበራዊ ሀብቶቻችን ለሰላም ዕሴት እና ለሀገር ግንባታ መጠናከር እንዲሁም ለብሔራዊ ምክክሩ በግብዓትነት መዋል በሚገባቸው ሁኔታዎች ላይም ምክክር አድርጓል፡፡

@tikvahuniversity
15.3K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 12:19:11
#WachemoUniversity

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 243 ተማሪዎች አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ ግብሮች
በኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ፣ በተፈጥሮ ቀመር ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍሎች ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው ከሦሥተኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ27 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል።

@tikvahuniversity
17.4K viewsedited  09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ