Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.08K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 245

2022-06-03 16:23:30
#የመምህራን_የሙያ_ብቃት_ምዘና

በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች የሙያ ብቃት ምዘና የጽሑፍ ፈተና ተሰጥቷል።

ከ8 ሺህ 500 በላይ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም የተጠበቀውን ያህል ተመዛኞች አልተገኙም ተብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ የትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በስምንት ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ት/ቤቶች ምዘናው እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።

የምዘና ፈተናውን ወስደው ማለፍ ያልቻሉ እስከ ሦሥት ጊዜ መፈተን የሚችሉ ሲሆን ሦሥት ጊዜ ተፈትኖ ማለፍ ያልቻለ መምህር ከማስተማር ሥራ እንደሚገለል ባለስልጣኑ ያዘጋጀው መመሪያ ያዛል።

"የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የሌላቸው መምህራን ማስተማር እንደማይችሉ" መመሪያው ይገልጻል።

በአዲስ አበባ የመምህራን የብቃት ምዘና መሰጠት የተጀመረው በ2005 ዓ.ም ነበር።

@tikvahuniversity
12.2K views13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 15:58:02
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የአገልግሎት ጥራትና ማሻሻያ ዘዴዎችን በመተግበር ከጤና ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቷል።

ኮሌጁ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ባለው ሀገር ዐቀፍ የጤና ተቋማት ኳሊቲ እና ሴፍቲ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ነው ዕውቅናውን ያገኘው።

የምስክር ወረቀቱን የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ ለኮሌጁ ተወካይ አበርክተዋል።

በሌላ ዜና ኮሌጁ 6ኛ ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንሱን በማድረግ ላይ ይገኛል።

በጉባኤው የመጀመሪያ ቀን ውሎ ከ250 በላይ ከኮሌጁ የተወከሉና ተጋባዥ ተሳታፊዎች ታድመዋል።

ዛሬ የሚጠናቀቀው ጉባኤው፤ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል 75ኛ ዓመት ምስረታን ዘክሯል።

የተለያዩ የፓናል ውይይቶች እየተደረጉ ሲሆን ሳይንሳዊ ጽሁፎችም በጉባኤው ቀርበዋል።

@tikvahuniversity
13.4K views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 16:50:17
የኮንሶ ዞን አስተዳደር እና የኮንሶ ህዝብ ለጂንካ ዩኒቨርስቲ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ያደረገው ደማቅ አቀባበል

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
10.8K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 15:36:14
#ማስታወሻ
#ScholarshipTip

መልቲቾይስ አፍሪካ/DSTV በየዓመቱ ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የአንድ ዓመት የፊልም ጥበብ ስኮላርሺፕ ይሰጣል።

የመልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ የስኮላርሺፕ ዕድል ወጣት ባለሙያዎችን ኬንያ በሚገኘው የመልቲቾይስ አካዳሚ የፊልም ጥበብ እውቀታቸውን የሚያጎለብቱበት ዕድል ይፈጥራል።

እድሚያችሁ ከ18-30 የሆነ ወጣቶች በተከታዩ ሊንክ ማመልከት ትችላላችሁ፦

www.multichoicetalentfactory.com

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው ነገ ግንቦት 26/2014 ዓ.ም

ለበለጠ መረጃ፦

https://cte.multichoicetalentfactory.com/Master/entrycriteria

(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
12.6K viewsedited  12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 12:31:32
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ማሪታይም አካዳሚ በማሪን ሜካኒካል ምህንድስና ያሰለጠናቸውን 69 ተማሪዎች አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ ላለፉት ስድስት ወራት ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

አካዳሚው በባሕር ላይ ምህንድስና በተለያዩ ዘርፎች እያሰለጠነ ሲያስመርቅ ይህ ለ19ኛ ጊዜ ነው፡፡

አካዳሚው ባለፈው የካቲት 40 የማሪን ኤሌክትሪካል መሀንዲሶችን ማስመረቁ ይታወሳል።

አካዳሚው በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው የመርከብ ባለሙያዎች ማሰልጠኛ ሲሆን እስካሁን 1 ሺህ 870 መርከበኞች አስመርቋል።

@tikvahuniversity
14.6K views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 12:08:27
ኢትዮ ቴሌኮም 66 ትምህርት ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የዲጂታል ትምህርት ማዕከል ፕሮጀክት አስጀምሯል።

ፕሮጀክቱ በአገር ዐቀፍ ደረጃ 66 ትምህርት ቤቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን 48 ትምህርት ቤቶች በክልሎች እና 18 ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

Bridging Divide Digital Center የተባለው ፕሮጀክቱ፤ 140 ሺህ 596 ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የኢትዮ ቴሌኮም ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቶቹ የመሠረተ ልማት ችግር ያለባቸው መሆኑን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ለትምህርት ቤቶቹ የኮምፒውተር፣ የኢንተርኔት እና የትምህርት መሠረተ ልማቶች የተሟላላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

@tikvahuniversity
15.1K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 12:09:37
#WoldiaUniversity

በ2014 ዓ.ም በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ግንቦት 30 እና ሰኔ 01/2014 ዓ.ም
እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ተቋሙ ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

• የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ ዋናውና ኮፒው
• ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና
ኮፒው
• የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት
ዋናውና ኮፒው
• 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ (4)
• ብርድልብስ፣ አንሶላና የትራስ ልብስ
• የስፖርት ትጥቅ

በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ የነበራችሁና በተለያየ ምክንያት ዳግም ቅበላ የሞላችሁ ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት ከአዲስ ገቢ ተማሪዎች ጋር ምዝገባ ማድረግ አለባችሁ ተብሏል።

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

@tikvahuniversity
15.0K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:50:48
#SPHMMC

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ 6ኛ ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንሱን ነገ ማድረግ ይጀምራል።

ለሁለት ቀናት የሚደረገው ጉባኤ፤ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል 75ኛ ዓመት ምስረታን "ከአገልግሎት ሰጪ ወደ ትምህርት፣ ምርምር እና አደጋ አስተዳደር የተደረገ ጉዞ" በሚል ጭብጥ ይዘክራል።

የፓናል ውይይት እና ሳይንሳዊ ጽሁፎችም በጉባኤው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።

በጉባኤው ለመሳተፍ በተከታዩ ሊንክ ይመዝገቡ፦

http://197.156.83.153/conference-reg/

@tikvahuniversity
13.9K views08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:30:19
#FreelanceEthiopia

በትርፍ ሰዓትዎ ከሚሰርዋቸው ሥራዎች ጀምሮ እንደ ትምህርት ደርጃዎ፣ የሥራ ልምድዎ እና ፍላጎትዎ በሁሉም አይነት ዘርፎች ሁሉንም አይነት ሥራዎች በአንድ ቦታ ያገኛሉ።

ለመቀላቀል ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦

https://t.me/+HZktkFNrwzg3Y2Fk
13.4K viewsedited  08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 11:09:57
#AASTU

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሀገረኛ የመጠጥ አይነቶችን በማዘመን ለገበያ ለማቅረብ እየሠሩ መሆናቸው ተገለጸ።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች "ማሬ ባህላዊ ጠጅ እና ጠላ መጠጦች አምራች ድርጅት" በሚል ስም ተደራጅተው በዘመናዊ መልኩ በላብራቶሪ የተሠራ ጠላ እና ጠጅ አምርተዋል፡፡

መጠጦቹ የጥራት ደረጃቸው ተወስኖ፤ የግብዓት አይነታቸውም በግልፅና በውል ታውቆ በዘመናዊ መልክ የተመረቱ መሆናቸው ተገልጿል።

ተማሪዎቹ ባደረጉት ጥናትና ምርምር ባህላዊው አዘገጃጀት የሚወስደውን የጊዜና የጉልበት መጠን በመቀነስ ከእጅ ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ ለማምረት የሚያስችል የሙከራ ጥናት አድርገዋል።

ሙከራው የምርቶቹ የመቆምጠጥ፣ ጌሾ የመብዛበት ወይም ቶሎ ያለመፍላት የጥራት ጉድለቶችን ያስቀራል ተብሏል።

በዚህም በየትኛውም ስፍራና በሁሉም የአይር ፀባይ በዕኩል ደረጃ ሊጠጣ የሚችልና ለረጅም ጊዜ ሊቆይ የሚችል ጠጅ እና ጠላ በማምረት ላይ ይገኛሉ፡፡

የኬሚካል ምህንድስና ተማሪዎች የሆኑት ኤርሚያስ ዋቅሹማ፣ ሀመረ ጋሻው፣ ማርታ ሳሙኤል እና ኬብሮን ግዛቸው በዘመናዊ መልክ የተመረቱትን ጠጅ እና ጠላን በቅርቡ ለገበያ እንደሚያቀርቡ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ፕሮጀክቱን ስኬታማ ለማድረግና ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ይደርስ ዘንድ የባለሀብቶች፣ የተቋማት፣ የመጠጥ ፋብሪካዎች እና ሌሎች ተባባሪ አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል።

ለማንኛውም ጥያቄዎችና አስተያየቶች በዩኒቨርሲቲው ኢሜል አድራሻ pir@aastu.edu.et መልዕክታችሁን ማድረስ ትችላላችሁ፡፡

@tikvahuniversity
14.4K views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ