Get Mystery Box with random crypto!

#ጥቆማ ጤና ሚኒስቴር የሚያስተዳድራቸውን አዲስ የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NMEI) ትምህርት | Tikvah-University

#ጥቆማ

ጤና ሚኒስቴር የሚያስተዳድራቸውን አዲስ የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NMEI) ትምህርት ቤቶች መቀላቀል የምትፈልጉ ዕጩዎች ማመልከት ትችላላችሁ፡፡

ሚኒስቴሩ በNMEΙ ስርዓተ ትምህርት የቅበላ ፖሊሲ መሰረት፣ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ህክምና ኮሌጅ አዲሱን የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NMEI) ለመቀላቀል ፍላጎት ያላቸውን ዕጩዎች እንዲመለምል፣ የመግቢያ ፈተና እንዲሰጥ እና ውጤት እንዲያሳውቅ ውክልና ሰጥቶታል። ውጤት ከተገለፀ በኋላ ቀሪ ጉዳዮች በሚኒስቴሩ የሚከናወን ይሆናል፡፡

ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦

➤ የመጀመሪያ ዲግሪ በጤና ሳይንስ እንዲሁም በባዮሎጂ እና በኬሚስትሪ

➤ CGPA ለሴቶች 2.75 እና ለወንዶች 3.0 ፤ ለአዳጊ ክልሎች ለሴቶች 2.5 እና ለወንዶች 2.75

➤ ከምርቃት በኋላ ቢያንስ ሁለት ዓመት የሥራ ልምድ

➤ ዕድሚያችሁ ከ35 ያልበለጠ

➤ የፖንሰርሺፕ ደብዳቤ ከምትሰሩበት የመንግሥት ተቋም ማምጣት የምትችሉ

➤ ራሳችሁን ስፖንሰር ማድረግ የምትችሉ ማመልከት ትችላላችሁ

የፅሁፍ ፈተና 60% የሚይዝ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡ 260 አመልካቾች 30% ለሚይዘው ቃለመጠይቅ ይመረጣሉ፡፡

ተከታዩን ሊንክ በመጫን ያመልክቱ፦
https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement/List?studyLevel=Undergraduate&instructionId=dc716240-4408-46d0-8da6-4ea0bf659bae

Note:

➧ ማመልከት የሚቻለው በኦንላይን ብቻ ነው፡፡
➧ የምዝገባ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 10-22/2016 ዓ.ም
➧ የፅሁፍ ፈተና፦ ግንቦት 4/2016 ዓ.ም
➧ ቃለመጠይቅ፦ ግንቦት 11/2016 ዓ.ም
➧ ውጤት የሚገለፀው፦ ግንቦት 14/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity