Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.08K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 244

2022-06-05 11:07:12
#SPHMMC

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም የሕክምና ኮሌጅ 25 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ አሥር የአልትራ ሳውንድ ማሽኖች ተበረከተለት።

በጤና ሚኒስቴር አማካይነት የተገኙት ማሽኖች ከጀርመኑ ሲመንስ ሄልዝ ኬር ድርጅት የተለገሱ ናቸው።

ድጋፉ የጤና አገልግሎቶችን በብቃት ከመስጠት አኳያ በተለይም የእናቶችን ጤና ከማሻሻል አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ ገልጸዋል።

ማሽኖቹ ኮሌጁ የሚሰጠውን የሕክምና አገልግሎት ጥራት ከፍ እንደሚያደርገው የኮሌጁ ፕሮቮስት ዶ/ር ወንድማገኝ ገዛኸኝ ተናግረዋል፡፡

ኮሌጁ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል እና ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመመርመር የአልትራ ሳውንድ ማሽኖቹ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው ብለዋል።

@tikvahuniversity
15.3K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 19:28:18
#KiburCollege

ክቡር ኮሌጅ በተለያዩ መስኮች በአጫጭር ስልጠና ያሰለጠናቸውን ከ310 በላይ ተማሪዎች አስመርቋል።

ሠልጣኞቹ በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለመግባት ዝግጅት ላይ የሚገኙ ናቸው።

ከአዲስ አበባ እና ሰበታ ከተሞች ከሚገኙ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ500 በላይ ተማሪዎች በስልጠናው የተሳተፉ ሲሆን ከ310 በላዩ ስልጠናቸውን አጠናቅቀው የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

ተማሪዎቹ ለቀጣይ ሙያቸውና ህይወታቸው አስፈላጊ የሆኑ ክህሎቶችን ያገኙበት መሆኑን የክቡር ኮሌጅ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ መኩሪያ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰትን ተከትሎ በቂ የትምህርት እገዛ እንዳልተደረገላቸው ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ፤ ስልጠናው በዚህ ረገድ ያለውን ክፍተት ለመሙላት የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ከአንድ እስከ ሦሥት ሳምንት የቆዩ አጫጭር ስልጠናዎች በ12 የተለያዩ ዘርፎች እንደተሰጠ ገልጸዋል።

ከግንቦት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው ነጻ የክህሎት ስልጠና፤ ተማሪዎቹ የህይወትና የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ተደርጓል።

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ምሁራን እና የፈጠራ ባለሙያዎች በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዋል።

@tikvahuniversity
11.2K views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 17:03:21
"ግዕዝ ወጥበባት" በሚል መሪ ሀሳብ 7ኛው የግዕዝ ጉባኤ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤው በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ እና በአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ትብብር የተዘጋጀ ነው።

የጉባኤው መካሄድ መጀመር የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የግዕዝ ትምህርት ክፍል እንዲያቋቁሙ እያስቻለ መሆኑን የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ይኩኖ አምላክ ገልጸዋል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ጉባኤ፤ ግዕዝ ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርባሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity
13.0K views14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 13:30:39
#TikvahFamily

በጦርነት እና በኮቪድ-19 ሳቢያ ተቋርጦ የነበረው አቅም ለሌላቸው ከፍተኛ ነጥብ ላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የሚደረገው የመመረቂያ አልባሳት ስጦታ በዚህ ዓመት ይቀጥላል።

ከየት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደምንወስድ በቅርብ እናሳውቃለን።

የሚመረጡት 3 ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን አጠቃላይ 6 ከፍተኛ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው በምናገኘው ማስረጃ የመመረቂያ ስጦታቸውን እናበረክታለን።

በዚህ ስራ ላይ እንደከዚህ ቀደሙ ማገዝ የምትፈልጉ ድርጅቶች ማገዝ የምትችሉ መሆኑ እየገለፅን የተማሪዎች ቁጥር እንዲጨምር የራሳችሁን አስተዋፆ ማድረግ ትችላላችሁ።

@tikvahethiopia
14.3K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 12:11:28
#DebarkUniversity

በ2014 ዓ.ም በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ሰኔ 08 እና 09/2014 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው የሚገኝበት አካባቢ ቀዝቃዛ የአየር ንብረት እንዳለው ተማሪዎች ሊያውቁ እንደሚገባ ተቋሙ ገልጿል።

(ለምዝገባ የሚያስፈልጉ እና ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
15.8K viewsedited  09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 19:50:08
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት ጥራትና ማሻሻያ ዘዴዎችን በመተግበር ከጤና ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቷል።

ሆስፒታሉ በአዲስ አበባ በተካሄደው ሀገር ዐቀፍ የጤና ተቋማት ኳሊቲ እና ሴፍቲ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ነው ዕውቅናውን ያገኘው።

የምስክር ወረቀቱን የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ ለሆስፒታሉ ተወካይ አበርክተዋል።

@tikvahuniversity
10.6K views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 18:53:48
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱ በዋነኝነት ዩኒቨርሲቲው በሚያከናውናቸው የጥናትና ምርምር ሥራዎች ላይ በትብብር መስራት የሚያስችል ነው። የቱሪስት ሳይቶችን ካርታ ማንሳት ሌላው የስምምነቱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።

ተማሪዎች ለተግባር ትምህርት ወደ ተቋሙ በመሄድ ስልጠና እንዲወስዱ የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል።

የኢንስቲትዩቱ የስፔስ ዘርፍ ም/ዳይሬክተር ይሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) እና የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር) ስምምነቱን ፈርመዋል።

@tikvahuniversity
12.0K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 18:53:06
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለግብርና ምርምር ሥራ አገልግሎት የሚውል 270 ሄክታር መሬት ተረክቧል።

ዩኒቨርሲቲው ለምርምር ሥራ አገልግሎት የሚውል በዳባት ከተማ 70 ሄክታር እና በሁመራ 200 ሄክታር የእርሻ መሬት መረከቡን ገልጿል።

ማሳዎቹ ለአርሶ አደሩ የተሻሻሉ ዘሮችን ለማቅረብ የሚያስችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በደጋ እና በቆላ ግብርና ልህቀት ለማግኘት የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመጀመር እየሰራሁ ነው ብሏል።

@tikvahuniversity
10.1K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 17:24:32
#KiburCollege

ክቡር ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለመግባት ዝግጅት ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየውን ነጻ የክህሎት ስልጠና ነገ ያጠናቅቃል።

ከአዲስ አበባ እና ከሰበታ ከተማ ከሚገኙ ከ75 በላይ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ500 በላይ ተማሪዎች በስልጠናው ተሳትፈዋል።

College and Career Readiness Bootcamp የተባለው ስልጠናው፤ ተማሪዎቹ ለቀጣይ ሙያቸውና ህይወታቸው የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት ያገኙበት መሆኑን የክቡር ኮሌጅ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ መኩሪያ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።

ከግንቦት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው ስልጠና፤ ተማሪዎቹ በ12 የስልጠና አይነቶች የህይወት እና የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

የስልጠናው ማጠቃለያ ዝግጅት ነገ ግንቦት 27/2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ ይካሄዳል ተብሏል።

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ የፈጠራ ባለሙያዎች እና ሌሎችም በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ እንደሚገኙ ይጠበቃል።

በመድረኩ ምሁራን ልምዳቸውን የሚያካፍሉ ሲሆን ለሰልጣኞች የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ይሰጣል።

@tikvahuniversity
12.0K views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 16:50:24 #የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀው የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ማቋቋሚያ ደንብ ከዛሬ ግንቦት 26/2014 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ ውሏል።

16 አንቀጾች ያሉት የባለሥልጣኑ ደንብ 515/2014 በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ወጥቷል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የሥራ አመራር ቦርድ መመደቡ ይታወሳል።

( ደንቡ ከላይ ተያይዟል። )

@tikvahuniversity
11.2K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ