Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 248

2022-05-22 14:26:17
#Update
#WollegaUniversity

በ2014 ዓ.ም ወደ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከግንቦት 15 እስከ 17/2014 ዓ.ም እንደሆነ መገለጹ ይታወቃል።

ዩኒቨርሲቲው ለአዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የትራንስፖርት አገልግሎት ማዘጋጀቱን ገልጿል።

• መነሻ ከተማ፦ ደምቢ ዶሎ
መነሻ ሰዓት፦ ከጧቱ 12:00
ጉዞ ወደ ነቀምቴ፦ በ15/09/2014 ዓ.ም
አስተባባሪዎች፦
ለገሰ ግርማ ~ 0916640790
ዱሬሳ አለማየሁ ~ 0919521309

• መነሻ ከተማ፦ መንዲ
መነሻ ሰዓት፦ ከጧቱ 12:00
ጉዞ ወደ ነቀምቴ፦ በ15/09/2014 ዓ.ም
አስተባባሪዎች፦
መሀመድ ዑመር ~ 0912700614
ሚልኬሳ ታከለ ~ 0935063833

• መነሻ፦ አያና ከተማ
መነሻ ሰዓት፦ ከጧቱ 12:00
ጉዞ ወደ ነቀምቴ፦ በ15/09/2014 ዓ.ም
አስተባባሪዎች፦
ገመቹ ገለታ ~ 0930770690
ኒሞና ከበደ ~ 0918171173

• መነሻ፦ ሻምቡ ከተማ
መነሻ ሰዓት፦ ከጧቱ 12:00
ጉዞ ወደ ነቀምቴ፦ በ15/09/2014 ዓ.ም
አስተባባሪዎች፦
ሸሚን ኢብራሂም ~ 0917434355
አዳነች ደገፋ ~ 0964629049

• መነሻ፦ አዲስ አበባ (አስኮ)
መነሻ ሰዓት፦ ከጧቱ 12:00
ጉዞ ወደ ነቀምቴ፦
በ15/09/2014 ዓ.ም (2 አውቶቡሶች)
በ16/09/2014 ዓ.ም (1 አውቶቡስ)
አስተባባሪዎች፦
ጀማል አደም ~ 0916700774
ደጋጋ ፈቀደ ~ 0917033569
ጃቤሳ አመንቴ ~ 0912290387
ቦንቱ ተመስገን ~ 0917675546

@tikvahuniversity
18.3K views11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 13:22:56
#Bule_Hora_University

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ለሚከፍተው ማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ የስቱዲዮ ግንባታ አስጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ለመክፈት
ባለፈው ዓመት ከኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን ፈቃድ አጊኝቷል።

ይህንን ተከትሎም የማሰራጫ ማዕከል/ስቱዲዮ ግንባታ ለማከናወን የወጣውን ጨረታ ያሸነፈው ድርጅት ሥራ መጀመሩን የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ዳንኤል ሰይፉ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

የሬዲዮው መጀመር ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበረሰብ አገልገሎት ሥራዎችን በተለይ በጉጂ እና በምዕራብ ጉጂ ዞን ተደራሽ ለማድረግ ያስችለዋል ብለዋል።

የማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮው በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋዎች ሥርጭቱን ያስተላልፋል።

የማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮው (ኤፍ.ኤም 99.0 MHz) በቅርቡ የሙከራ ስርጭት እንደሚጀምር ይጠበቃል።

@tikvahuniversity
17.9K views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 12:20:52
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርትዎን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በአራት ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነውም ይመረቃሉ።

ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ መልክ የተደራጁ የመማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ-መፅሀፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ-ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982363636
0978028655

#BITSCollege
16.0K viewsedited  09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 12:13:54
#Dilla_University

3ኛው አገር ዐቀፍ የሕግ ጥናትና ምርምር ጉባኤ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

ጉባኤው "የታክስ ስርዓትና የሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ" በሚል ጭብጥ ላይ እየመከረ ነው።

በጉባኤው የተለያዩ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ የፌዴራል ፍትህና ሕግ ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶች ኅብረት የሁለት ቀናት ጉባኤውን በጋራ አዘጋጅተውታል።

@tikvahuniversity
15.0K views09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 12:05:12
#Wollo_University

ወሎ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 823 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና በእንስሳት ሕክምና ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ከዛሬ ተመራቂዎች ውስጥ 106ቱ በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠኑ መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ከደረሰበት ውድመት መልሶ በመቋቋም የመማር ማስተማር ሥራውን ዳግም በማስጀመር፤ ለተማሪዎቹ ቅዳሜ እና እሁድ የማካካሻ ትምህርት በመሰጠት ለምርቃት እንዲበቁ መደረጉን ገልጿል።

@tikvahuniversity
16.7K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 20:48:04
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት በፍተሻ ላቦራቶሪ የISO/IEC 17025 ዓለም ዐቀፍ ዕውቅና አገኘ።

ኢንስቲትዩቱ ዓለም ዐቀፍና ብሔራዊ መሥፈርት  ማሟላቱ በፊዚካልና ኬሚካል ፍተሻዎች መረጋገጡን ተከትሎ በኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዕውቅና ተሰጥቶታል።

ኢንስቲትዩቱ ዕውቅና ማግኘቱ በአማራ ክልል ለሚገኙ እና በጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች ለሚያመርቷቸው ምርቶች የጥራት የላቦራቶሪ ፍተሻ ውጤት መስጠት ያስችለዋል።

በ2003 ዓ.ም የተቋቋመው የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልገሎት፤ መስፈርቶችን ላሟሉ 13 ተቋማት የአክሪዲቴሽን አገልግሎት ዕውቅና መስጠቱን በዚህ ሳምንት መግለጹ ይታወቃል፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥቁር  አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሌላው በሕክምና ላቦራቶሪ ዕውቅና የተሰጠው የትምህርት ተቋም ነው።

@tikvahuniversity
11.7K views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 19:47:56
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ማቋቋሚያ ደንብን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

ምክር ቤቱ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ በቦርድ እንዲመራም ወስኗል።

በዚህም ለባለሥልጣኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሹመዋል፦

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የቦርድ ሰብሳቢ ሆነዋል።

ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ ተስፋዬ ዳባ፣ ሹመቴ ግዛው (ዶ/ር) እና ሳህረላ አብዱላሂ በአባልነት ተመድበዋል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አንዱዓለም አድማሴ (ዶ/ር) የሥራ አመራር ቦርዱ አባል እና ፀሀፊ ሆነዋል።

@tikvahuniversity
13.3K views16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 13:26:29
#Update
#Mizan_Tepi_University

በ2014 ዓ.ም ወደ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ግንቦት 17 እና 18/2014 ዓ.ም እንደሆነ መገለጹ ይታወሳል።

አዲስ ገቢ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቦታ፦

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ~ ቴፒ ግቢ

የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ~ ሚዛን ግቢ

ዩኒቨርሲቲው ሚዛን አማን እና ቴፒ ከተሞች ላይ ወደየካምፓሶቹ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አውቶብሶች እንደተዘጋጁ ገልጿል።

ተጨማሪ መረጃ እና ድጋፍ ለማግኘት፦

ለሚዛን አማን
• 09-28-03-95-25
• 09-67-94-52-86
• 09-17-86-53-07
• 09-21-29-18-36

ለቴፒ
• 09-25-01-88-58
• 09-30-63-63-73

@tikvahuniversity
18.1K viewsedited  10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 11:53:50
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርትዎን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በአራት ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነውም ይመረቃሉ።

ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ መልክ የተደራጁ የመማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ-መፅሀፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ-ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982363636
0978028655

#BITSCollege
17.4K viewsedited  08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 11:51:26
#Update

በሰሜን ጎንደር ዞን በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያልወሰዱ እና ፈተናውን ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች በሙሉ በቀጣይ ዓመት ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

የዞኑ ትምህርት መምሪያ ተማሪዎቹ በቀጣይ ዓመት ለሚሰጠው ፈተና ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።

በዚህም የማጠናከሪያ ትምህርት ከግንቦት ወር ጀምሮ ለሁለት ወራት እንደሚሰጥ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ገልጿል።

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያልወሰዱ እና ፈተናውን ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች ከ2014 ዓ.ም ተፈታኞች ጋር በድጋሚ ፈተናውን እንዲፈተኑ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ መወሰኑ ይታወሳል።

(በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ስለጉዳዩ የጻፈው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
15.7K views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ