Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.08K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 253

2022-05-20 20:14:12
#የትምህርትና_ሥልጠና_ባለሥልጣን

በርካታ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የሚታደልባቸው እየሆኑ መምጣታቸው ተገለጸ።

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርጓል።

ሕገ-ወጥ የትምህርት ማስረጃ እና ሕገ-ወጥ ተቋማት መበራከታቸውን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አንዱዓለም አድማሴ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ተቋሙ የተሰጠውን አገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ለመፈጸም የሚያስችል የሰው ኃይል አደረጃጀት አለመኖሩንም ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።

የቋሚ ኮሚቴው ስብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበርካታ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚታየውን የሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እደላ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ቀልጣፋና ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ከዓለም ባንክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ባለ ሰባት ወለል ህንጻ ለማስገንባት በሂደት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

@tikvahuniversity
14.5K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:58:13
#የኢንፎርሜሽን_ቴክኖሎጂ_ውድድር

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተሻለ የፈጠራ ሥራ ያላቸውን ባለሙያዎች እውቅና መስጠት እና ሥራዎቻቸውን ማስተዋወቅ እንደሚፈልግ ገልጿል።

ኅብረተሰቡን የሚጠቅምና ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸው የፈጠራ ሥራ ያላችሁ እስከ ግንቦት 19/2014 ዓ.ም አዲስ አበባ አምስት ኪሎ በሚገኘው የተቋሙ ቢሮ ማቅረብ ትችላላችሁ ተብሏል።

• በኢ-መንግስት ሶሉሽን፣
• በሶፍትዌር ልማት፣
• በሮቦቲክስ፣
• በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ/ዳታ ሳይንስ እና ሌሎችም መሰል ዘርፎች የፈጠራ ሥራ ያላችሁ ማመልከት ትችላላችሁ።

የፈጠራ ሥራዎቹ ቢሮው በሚያዘጋጀው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ላይ ይቀርባሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity
18.2K views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:06:06
#Haramaya_University

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን አዲስ የተመደቡ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች መግቢያ ከግንቦት 12 እስከ 14/2014 ዓ.ም መሆኑን የገለጸ ቢሆንም ከትላንት ምሽት ጀምሮ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው አዲስ አበባ እና አዳማ ከተሞች ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያስተባብሩ ሰዎች መመደቡን በዩኒቨርሲቲው የፍሬሽማን ፕሮግራም ዳይሬክተር ጌታቸው ተሾመ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ተማሪዎች የተመደቡትን ካምፓስ እና የመኝታ ክፍል በበይነ መረብ አማካኝነት እንዲያውቁ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከ5 ሺህ 100 በላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበውለታል።

@tikvahuniversity
18.8K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 13:45:40
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርትዎን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በ4 ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነውም ይመረቃሉ።

ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ መልክ የተደራጁ የመማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ-መፅሀፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ-ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982363636
0978028655

#BITSCollege
18.0K viewsedited  10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 12:30:44
#Ethiopian_Civil_Service_University

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በመደበኛ፣ በክረምት፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መእሃ ግብሮች ለመማር የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ግንቦት 20 እና 21/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል።

(የትምህርት ክፍሎች እና ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
18.9K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 11:59:12
#Fake_News_Alert

በ2015 ዓ.ም የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ባሉበት የትምህርት ደረጃ እንዲቀጥሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ተናገሩ በሚል በማኅበራዊ የትስስር ገጾች የሚዘዋወረው መረጃ #ሐሰት መሆኑን እንገልጻለን።

ቲክቫህ እንደዚህ አይነት ዘገባ አለመስራቱንም ልናረጋግጥ እንወዳለን።

ሀሰተኛ፣ የተዛቡ እና ያልተረጋገጡ መረጃ ከሚያሰራጩ የማኅበራዊ ሚዲያ አካውንቶች ራስዎን ይጠብቁ፡፡

ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስቴር አድራሻ፦

https://www.facebook.com/fdremoe

ትክክለኛው የቲክቫህ ኢትዮጵያ አድራሻ፦

https://t.me/tikvahethiopia

ትክክለኛው የቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድራሻ፦

https://t.me/TikvahUniversity

@tikvahuniversity
22.8K viewsedited  08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 17:49:02
#Update

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችው ፅጌሬዳ ግርማይን በመግደል የተከሰሰው ተማሪ ለውሳኔ ለግንቦት 19/2014 ዓ.ም ተቀጥሯል።

ተከሳሹ የመከላከያ ምስክሮች በማቅረብ ራሱን ሲከላከል ቆይቷል።

ፍርድ ቤት የቀረቡ ምስክሮች "ሟች እና ተከሳሾች ጓደኛሞች እንደነበሩ እንደሚያውቁና ከዚያ ውጪ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ" ገልጸዋል።

በሕግ ጥላ ስር በሚገኘው ተከሳሽ ብሩክ በላይነህ ላይ የፍርድ ማቅለያ እና ማክበጃ መቅረቡን የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ መርኪያ መንገሻ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

ተከሳሹ በአርባ ምንጭ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን እየተከታተለ ይገኛል።

ፍርድ ቤቱ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ተለወጫ ቀጠሮ ለግንቦት 19/2014 ዓ.ም ሰጥቷል።

ጥር 23/2014 ዓ.ም የተገደለችው የ20 ዓመቷ ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት የ2ኛ ዓመት ተማሪ ነበረች፡፡

@tikvahuniversity
16.7K views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:40:48
#Jinka_University

በ2014 ዓ/ም በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 25-26 /2014 ዓ/ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ሂደቱንና ሌሎች ተጨማሪ መረጀዎችን በዩኒቨርሲቲው ድረገፅ www.jku.edu.et እና በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/178538809733160/posts/1039175540336145/ ላይ ስለሚለቀቅ በዛ መከታተል ትችላላችሁ።

@tikvahuniversity
18.8K viewsedited  12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 17:51:27 የሥራ ፈጠራ በኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲ ውስጥ እንዲካተት ተጠየቀ።

ትኩረቱን የሥራ ፈጠራን ማሳደግ ላይ ያደረገው "ብራይት ፊውቸር ኢን አግሪካልቸር" ፕሮጀክት እ.አ.አ. ከ2019 ጀምሮ በኢትዮጵያ በመተግበር ላይ ይገኛል። 

በተለይም በግብርና ዘርፍ ያለውን የሥራ ፈጠራ ለማሳደግ እየሠራ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ሰለሞን ሞገስ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

በአራት ሚሊዮን ዩሮ በጀት ለ4 ዓመታት የሚተገበረው ፕሮጀክቱ፤ በተለይም የቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማት መምህራን በሥራ ፈጠራ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ ይሠራል። ይህም ከቴክኒክና ሙያ ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ድክመት የሆነውን የዕውቀት ችግር ለመፍታት የመጀመርያ ዕርምጃ መሆኑን አክለዋል።

በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልሎች በሚገኙ ሰባት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚተገበረው ፕሮጀክቱ፤ በእስካሁኑ ቆይታው የሥራ ፈጠራን በተመለከተ መምህራን የዕውቀት ችግር እንዳለባቸው ለይቷል ብለዋል።

በተጨማሪም ለቴክኒክና ሙያ የሚመደበው በጀትና የሚሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ በሚፈለገው ልክ ውጤታማ አለመሆኑን ይናገራሉ። በፕሮጀክቶች ከሚገኘው ድጋፍ በተለየ በዘላቂነት አቅማቸውን ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የሥራ ፈጠራ ግንዛቤ ለማሳደግ ብሔራዊ የሥራ ፈጠራ ትምህርት ፖሊሲ ሊኖር እንደሚገባም ሰለሞን (ዶ/ር) ጠቁመዋል።

ትምህርቱ ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ ራሱን ችሎ መሰጠት እንዳለበትም አክለዋል። #ሪፖርተር

@tikvahuniversity
24.8K viewsedited  14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 10:43:00
ዳሸን ባንክ የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜን አራዝሟል።

ባንኩ የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ተማሪዎች 'ዳሸን ከፍታ' በተሰኘው የባንኩ 2ኛ ዙር የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ለማሳተፍና ለማሰልጠን ሲመዘግብ ቆይቷል።

ማንኛውም የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ያለው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ በአቅራቢያው በሚገኝ ዳሸን ባንክ በመሄድ
መመዝገብ እንደሚችል መገለጹ ይታወሳል።

ምዝገባና ስልጠናው እስከ ግንቦት 17/2014 ዓ.ም ተራዝሟል።

በውድድሩ የሚያሸንፉ የገንዘብ ሽልማት፣ የብድር አቅርቦት፣ ሙያዊ ድጋፍ እና የገበያ ትስስር ያገኛሉ።

@tikvahuniversity
26.3K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ