Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-01-14 10:03:47
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጽዳት ዘመቻ አካሄዱ፡፡
//////////////////
የጽዳት ዘመቻውን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች እና የተማሪ ህብረት ተወካዮች አስጀምረውታል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) በማስጀመሪያው እንደተናገሩት ተማሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት የጽዳት ዘመቻ በማካሄዳቸው መልካም ነገር መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲተውን ጽዱ እና ለመማር ማስተማር ምቹ እንዲሆን የተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዶ/ር ወሀቤ አያይዘውም ግቢው አረንጓዴነቱን ጠብቆ እንዲቆይ ከጽዳት ባለፈ ተማሪዎች አረንጓዴ ቦታዎችን ባለመረገጥ እና በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በላይ ዘለቀ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው “አረንጓዴው ግቢ” የሚል መጠሪያውን ይዞ እንዲቀጠል የተማሪዎች ተሳትፎም አስፈላጊ በመሆኑ ተማሪዎች ያደረጉት ነገር መልካም መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ከተማሪዎች ጋር በርካታ ስራዎችን እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ዮሐንስ ጓዴ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ለማጽዳት ያሰብነው ከማጽዳት በተጨማሪ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር እና በጋራ ለመስራት በማሰብ ነው ብሏል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ በላይ ውብ እና ማራኪ እንዲሆን በቀጣይም በተከታታይነት የጽዳት ዘመቻ እንደሚያከናውኑ ተማሪ ዮሐንስ ተናግሯል፡፡
ጥር 6/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
288 views07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 22:02:19
1.1K views19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 22:02:19
በስጋዲ ሞዴል ችግኝ ጣቢያ የሥራ ጉብኝት ተካሄደ፡፡
----------------

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና፣ ምግብ እና አየር ንብረት ሳይንስ ኮሌጅ እየተሰራ በሚገኘው ጓንጓ ወረዳ ስጋዲ ሞዴል ችግኝ ጣቢያ ላይ የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ተካሂዷል።

በጉብኝቱ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመባቸው ሶስት ዋና ዋና ተልዕኮዎች አንዱ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ተልዕኮ ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር በአረንጓዴ ልማት ላይ በሰፊው እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል ።

ከዚህ አንጻር በስጋዲ ሞዴል የችግኝ ጣቢያ ላይ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ችግኝ የማፍላት ሂደት መጀመሩን የገለጹት ም/ፕሬዝደንቱ ቦታውን ለረዥም ጊዜ የሚጠቅም የአንድ ትልቅ የችግኝ ጣቢያ በማድረግ የምርምር እና የመማር ማስተማር ሥራዎች በተግባር የሚከወኑበት እንዲሁም ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችን አዘጋጅቶ ተደራሽ ለማድረግ በዘርፉ ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን በመመደብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚህየችግኝ ጣቢያ ላይ ለመስራት ዩኒቨርሲቲው ያቀረበውን የቦታ ጥያቄ ሳያቅማሙ ተቀብለው ላስተናገዱ የጓንጓ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
...

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0GEhfN8PaeKpo4MGEspYxeQcMTnj1nVMwxJXVfqZtya7Fx9SS2V56zSgFsaGNCgbNl/?app=fbl
ጥር 5/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.1K views19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 15:32:06
የገና 2015 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በድምቀት ተከበረ።

የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው መመገቢያ አዳራሽ ከተማሪዎች ጋር በዓሉ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ምክትል ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ተማሪዎች ከቤተሰብ ተለይተው እንደዚህ ዓይነት በዓላትን ሲያሳልፉ ብቸኝነት እንዳይሰማቸው ዩኒቨርሲቲው ለበዓል የሚሆን አስፈላጊውን ዝግጅት እንዳደረገ ገልፀው በዓሉ የሰላምና የፍቅር የአንድነት እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የገና በዓል አስመልክቶ ቀደም ብሎ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን በማድረግ በዓሉን ለማክበር በመመገቢያ አዳራሹ ውስጥ ልዩ ልዩ የበዓሉን ድባብ ለተማሪዎች የሚያስተጋቡ መስተንግዶዎች ቀርበው በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የግቢው የፀጥታና ደህንነት አባላትና በግቢው ውስጥ በፀጥታና ደህንነት ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላትም በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል፡፡

ታኅሳስ 29/2015፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.6K views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 08:32:24
እንጅባራ የኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
///////////////
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት ይሁንልን!
ታኅሳስ 28/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
2.4K views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 20:56:25
በስነ ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለ195 የግቢ ጸጥታና ደህንነት ሠራተኞች በሥነ ምግባር ምንነት፣ በሥራ ሥነ ምግባር እና በዩኒቨርሲቲው የአመራር አካላትና ሠራተኞች የሥነ ምግባር መመሪያ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ሥልጠናው የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና ከፍ በማድረግ የሙስና ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት አስቀድሞ ለመከላከል እንደሀገር የተያዘው የሙስና መከላከል ስትራቴጂ አካል መሆኑን ስልጠናውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲው የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ደሳለው ጌታሁን አስረድተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አያይዘውም ሙስና በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ሶስተኛው አንገብጋቢ ጉዳይ በመሆኑ መንግስት የችግሩን አሳሳቢነት ተረድቶ ችግሩን ለመከላከል እንዲሁም አጥፊዎችን ለህግ ለማቅረብ በሀገር ደረጃ ኮሚቴ አቋቁሞ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ እንቅስቃሴ ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም ዜጋ ተገቢውን ስነ ምግባር ከመላበስ ባሻገር በሙስናና ብልሹ አሰራር ላይ የተሰማሩ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ጥቆማ በመስጠት የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አስረድተዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ስልጠናውን ያስተባበሩት የዩኒቨርሲቲው የግቢ ፀጥታና ደህንነት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ፈንታ ስልጠናው ለግቢው የጸጥታና ደህነት ስራ አጋዥ ከመሆኑ ባሻገር ሁሉም ዜጋ ለሀገራዊ የፀረ ሙስና ትግል የድርሻውን እንዲወጣ የሚያስገነዝብ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ሙስናን ከመከላከል አንጻር ቀደም ሲል በየደረጃው ለሚገኙ የዩኒቨርሲቲው አካላት ተከታታይ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ማከናወኑ ይታወቃል።

ታኅሳስ 27/2014 ዓ.ም፤
2.4K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 21:36:30
"ለሀገር ግንባታ የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት፣ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ውይይት ተጠናቀቀ፡፡
////////////

ሀገርን ለመገንባት እና ህዝቦችንም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማስተዳደር በየደረጃው የሚካሄዱ ውይይቶች አስፈላጊ መሆኑን እና የምሁራንም ሚናም ጎልቶ መታየት እንዳለበት በመድረኩ ተገልጿል።

በዛሬው እለት በተካሄደው ውይይት ለመምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች በሀገር ግንባታ ላይ ያተኮረው ሰነድ ቀርቧል። ከመምህራንም ለሀገር ግንባታ ግብዓት የሚሆኑ በርካታ አስተያየት እና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል መንግስት ሰላምን በማስፈን የዜጎችን ደህንነት የማስጠበቅ (ህግ ማስከበር) ኃላፊነት እንዲወስድ፣ የሀገር ኢኮኖሚን ማሳደግ እና የኑሮ ውድነት እንዲያስተካክል፣ በተለያዩ ጊዜያት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ሲቀርቡ የቆዩ የደመወዝ እና ጥቅማ ቅጥም ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጥ እንዲሁም የተቋማት ግንባታ፣ የሚዲያ ነጻነት፣ የትምህርት ጥራት ችግሮች፣ ህገ- መንግስት የማሻሻል እና የሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ያተኮሩ ነጥቦች ተነስተዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0WT88wFD2qEQXB3LmSvAWVQFnH7a4ZjRYnB3r2iMA8pJHh3K6u2yMasybvm2vVQXKl/?app=fbl
1.0K views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-02 10:48:21
"ለሀገር ግንባታ የምሁራን ሚና" በሚል መሪ ሃሳብ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት ውይይት መደረግ ጀምሯል።
////////////

በውይይቱ አቶ ካሳሁን ጎፌ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ፣ ዶ/ር ሄኖክ ስዩም የስቴት ሚኒስቴር አማካሪ፣ አቶ እንግዳ ዳኛው የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ አባል እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እና ካውንስል አባላት ተገኝተዋል።

ታኅሳስ 24/2015 ዓ.ም
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02cdfALupmZMU5LeDnM3dae5RSdzNx9vx9SrimEzFfpUavj7faRhnBERWhwkL68keRl/?app=fbl
2.2K views07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 20:19:28
የአማራ ክልል ምክር ቤት ሰሠራተኞች በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ጉብኝት አደረጉ፡፡
------------
በጉብኝቱ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር እና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝደንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከተሰጠው ተልኮ አንፃር በመማር ማስተማር፣ በምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች የተከናወኑ ተግባራትን መሠረት አድርገው ገለፃ አድርገዋል።
በተጨማሪም የአረንጓዴ ልማት፣ የእንስሳት ምርምር ጣቢያ፣ ግንባታ ፕሮጀክቶች፣ ምቹ የሥራ ከባቢ በመፍጠር የህፃናት ማቆያ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ ቤት ግንባታ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ስላለው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለጎብኝዎቹ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ዶ/ር ወሀቤ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ አጋር ድርጅቶች ጋር የተለያዩ የውል ስምምነቶችን(MOU) በመፈራረም በመማር መስተማር ነጻ የትምህርት እድልን በማመቻቸት፣ የተለያዩ ሥልጠናዎችን በመስጠትና ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ተግባር ተኮር የሆነ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ለጎብኝዎቹ አብራርተዋል፡፡

በጉብኝቱ የተሳተፉት የአማራ ክልል ምክርቤት ህንጻ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዓለም ይታየው እንደተናገሩት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእድሜው አጭር ቢሆንም አስገራሚ ለውጥ ላይ እንደሚገኝ ተናግረው ምክር ቤቱ ከዩኒቨርሲተው ጋር በተለያዩ ዘርፎች ለመስራት ዝግጅት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የፋሲሊቲ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በጊዜው አበበ እና በዩኒቨርሲቲው የሆርቲካልቸር ትምህርት ክፍል ኃላፊና መምህር የሆኑት እጅጉ ጥላሁን ዩኒቨርሲቲው በአረንጓዴ ልማት ዘርፍ በግቢ ውስጥ እና ከግቢ ውጭ ስለሚያከናውናቸው ተግባራት ለጎብኝዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ታህሳስ 22/2015ዓ.ም
1.0K views17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 20:17:59
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሠራተኞች የማህጸን ጫፍ ቅድመ ካንሰር ምርምራ እና ህክምና ዘመቻ ተጀመረ፡፡
------------------------
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ሆስፒታል ጋር በመተባባር ከታህሳስ 20 እስከ ጥር 5/2015ዓ.ም የሚቆይ ለሁሉም የዩኒቨርሲቲ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች የነፃ የማህጸን ጫፍ ቅድመ ካንሰር ምርምራ እና ህክምና ዘመቻ ተጀምሯል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0hospqZa5ZL9kksahcvhg8yec3uXVbgWcu3rZsTsT1sqTx8N1rv9EwgCUkAMaFe7dl/?app=fbl
975 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ