Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-14 19:35:42
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
2.3K viewsedited  16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 06:06:05
ለልዩ ፍላጎት መምህራን የብሬል ኮንትራክሽን ስልጠና ተሰጠ
***********
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አስተባባሪነት በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር አምስት ወረዳዎች ለሚገኙ የልዩ ፍላጎት መምህራን የብሬል አህጽሮተ ጽሑፍ በዩኒቨርሲቲው የትምህርት እና ሥነ ባህርይ ኮሌጅ መምህራን አማካኝነት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የስልጠናው ዓላማ የልዩ ፍላጎትን የሙያ ብቃት ማሳደግ፣ የተማሪዎችን ትክክለኛ የብሬል ጽሑፍ ስርዓት እንዲያውቁ ማስቻል እና የመማር ማስተማሩን ሂደት የተሳለጠ ማድረግ እንዲሁም በልዩ ፍላጎት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ የሚያስገነዝብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ቃላትን በፊደል ማሳጠር፣ ሀረግ እና አረፍተነገርን በቃላት ማሳጠር፣ የተለያዩ ስርዓተ-ነጥቦችን ትክከለኛ አጠቃቅም እና መሰረታዊ የሂሳብ ስሌቶች የሚሉ አርዕስቶች በስልጠናው ተዳሰዋል፡፡

ስልጠናው ከእንጅባራ ከተማ አስተዳድር፣ ባንጃ፣ ጓጉሳ፣ አንከሻ እና አየሁ ወረዳዎች የተውጣጡ 30 (ሰላሳ) የልዩ ፍላጎት መምህራን የተሳተፉበት ሲሆን መ/ር ሀብታሙ ዓለምነህ፣ መ/ር ሀብታሙ ገኔ፣ መ/ር ካሳሁን አንተነህ እና መ/ርት ጥሩዬ አብዲ በተለያየ ጊዜ ለአራ ቀናት ያክል ስልጠናውን ሰጥተዋል፡፡
መጋቢት 4/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
179 views03:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 16:39:51

1.2K views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 15:54:16
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም የተመደቡለትን ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው፡፡
------------------
በትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ውጤታቸው ከ50% በታች የሆነባቸው እና የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መውሰድ የሚችሉ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች በመግባት ላይ ናቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡለትን 1900 (አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ) በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡ ከሚገቡ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ተጠቃሚ ተማሪዎች መካከል ከ5መቶ በላይ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡
የተማሪዎች ቅበላ መርሐ ግብር ም በነገው እለትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡
መጋቢት 4/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.4K views12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 15:53:19
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ፦

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከታች በተዘረዘሩት የሥራ መስኮች በወጣው መስፈርት መሰረት አመልካቾች በተጠቀሰው ቀን ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
1.2K views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 15:52:48
ለ "STEM" ፕሮግራም ተማሪዎች የህይወት ክህሎት ሥልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ "STEM" ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሶስቱም የእንጅባራ ከተማ አጠቃላይ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተመረጡ ተማሪዎች መደበኛ የሳይንስ ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት የህይወት ክህሎት ሥልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡
የሥልጠናውን ላይ የዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ ሽፈራው ፕሮግራሙ ተማሪዎች በመደበኛው የትምህርት ጊዜያቸው በክፍል ውስጥ በቲዎሪ ደረጃ የሚማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር ቀይረው ለማየት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር መልካም አባተ ፕሮግራሙ የትምህርት ጥራትን ከማሻሻል አንጻር ከታች ክፍል መጀመሩ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ከሶስቱም ትምህርት ቤቶች የተሻለ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች በመምረጥ በተለይ በሳይንስ ትምህርቶች ዙሪያ ያላቸውን የእውቀት ክፍተት ለመሙላት ልምድ ባላቸው የዩኒቨርሲቲው ሙህራን የተግባር-ተኮር ትምህርት የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ፕሮግራም እንደ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓም በክረምት መርሃ ግብር (Summer outreach) የተጀመረ መሆኑን ጠቅሰው እና በበጋው ደግሞ ቅዳሜ እና እሁድን በመጠቀም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።


https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0BGXg5xPxN4xVqsVtc4CS56qYGmpGYHMmsQQsfQ9tF54eMe6rRL7ScfSPfUtQYtcxl/?app=fbl

"Every Child is a Scientist"
የካቲት 2/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.2K views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 17:40:44
የዓድዋ ድል የነጮችን የበላይነት ያከሰመ እና ለአፍሪካዊያን የነፃነት ትግል መሰረት የኾነ ነው ፡- የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን
1.3K viewsedited  14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 13:01:53
ማስታወቂያ፡-
በ2015 ዓ.ም የማካካሻ ትምህርት (Remedial) ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፦
የማካካሻ ትምህርት(Remedial) ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች መጋቢት 4 እና 5/2015 ዓ.ም የምዝገባ ጊዜ እንዲሁም መጋቢት 6/2015 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምርበት ጊዜ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ
 የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክርቢት እና የ12ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውን እና ፎቶ ኮፒ፤
 ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፤
 3*4 የሆነ 4 ጉርድ ፎቶግራፍ እና
 አጋዥ የትምህርት መጽሓፍትን ይዘው መምጣት የሚችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡
ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የካቲት 24/2015 ዓ.ም ፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ለተጨማሪ መረጃ/ for more Information
ለቴሌግራም-https://t.me/injiuniversity
ለኢንስታግራም -https://www.instagram.com/injibara12
ለዌብ ሳይት- https://www.inu.edu.et/
ለፌስ ቡክ ገፃችን- https://www.facebook. Com/injibaruni
ለኢሜይል- injibarau@gmail.com
ለInstitution Email -injibarauniversity@inu.edu.et
ለትዊተር- Twitter (https://twitter.com/injibara_Inu/)
በተጨማሪም የዩቱዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ይቀላቀሉን!
https://www.youtube.com/c/injibarauniversity
Explore Your Creative Potential!
1.8K viewsedited  10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 05:30:19
የዓድዋ ድል በዓል በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡

“አንድነት፣ጀግነትእና ፅናት” በሚል መሪ ቃል 127ኛው የዓድዋ ድል በዓል የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራን እና ተማሪዎች የሃይማኖት አባቶች የአገው ፈረሰኞች አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡

የካቲት 23/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የህዝብ እና ውጭ ግንኙነት ከታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር በጋራ ባዘጋጀው የዓደዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ”የዓድዋ ድል እና የሴቶች ሚና ” የሚል መነሻ ጽሑፍም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በበዓሉ ዝግጅት የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር እና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው የዓድዋ ድል የጥቁር ህዝቦች ሁሉ ድል መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ድል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከጫፍ እስከ ጫፍ በአንድ ዓላማ በመሳተፍ ጠላትን ድል አድርገው ያስረከቡን ታሪክ በመሆኑ ሁላችንም አንድነትን፣ ጀግነንት እና ጽናትን ይዘን በጋራ መስራት እና ታሪካችንን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02edtfbDcb2czue1zosTpnPAKappKCchCkQjejk7QRGxqwk9KHvGxAhddUkaa5J5d7l/?app=fbl
2.0K views02:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 05:27:43
ማስታወቂያ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሐ ግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ( በመደበኛ ፕሮግራም ብቻ) መማር ለምትፈልጉ በሙሉ፦
2.0K views02:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ