Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-03-28 21:21:19
"አገው ድጋግ" (የአገው ዣንጥላ) አሠራር ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ አገልግሎት እና የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ከአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ እንዲሁም ከእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር "አገው ድጋግ" (የአገው ዣንጥላ)አሰራር ለተከታታይ ሰባት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የተግባር ስልጠና ተጠናቀቀ።

በስልጠናው የማስጀመሪያ መረሃ ግብር የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ም/ማ/አገ/ም/ፕሬዚዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ስልጠናው የሀገር በቀል እውቀትን በመጠበቅ እንዲሁም በቀጣይነት ባህልን እና እሴትን አስጠብቆ የማቆየት ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል። የሙያ እና ቴክኒክ ኮሌጆችም በእደ ጥበብ የተለዩትን የሀገር በቀል እውቀቶችን ከማልማትና ከማስጠበቅ አንጻር እንደ አንድ የትምህርት አይነት አድርጎ ለተማሪዎች በማስተማር ወደ ትውልድ የማስተላለፍና ጠብቆ የማቆየት ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።

የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ለይኩን ሲሳይ በበኩላቸው "አገው ድጋግ" /የአገው ዣንጥላ/ከድሮ ጊዜ ጀምሮ በአዊ ማህበረሰብ ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ዘመናዊ ጥላ እስኪመጣ ድረስ ሴቶች እንዲሁም በዕድሜ የገፉ ወንዶች በዚህ ጥላ ከፀሐይና ከዝናብ ይጠለሉ እንደነበር እና ሠርግም የሚከናወነው በዚህ ጥላ እንደነበር ታሪኩን አስታውሰዋል።
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02ZotesaDsEjJcTCAtX6MAerwrKf9C4gf4wXLMBqfLyKVHKuJtxPgBB5GTZaDCC6Z9l/?app=fbl
2.5K views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 20:18:47

2.5K views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 16:25:03

3.1K views13:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 20:36:16
ማስታወቂያ

በሪሚዲያል ፕሮግራም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በቅዳሜ እና እሁድ ትምህርት ፕሮግራም መማር ለምትፈልጉ
5.6K views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 08:14:01
610 views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 08:13:55
የፋይናንስ ስርኣቱን ለማዘመን የሚያስችል የተደራጀ የፋይናንስ አስተዳደር መረጃ ስርዓት (Integrated Financial Management Information System) “IFMIS” ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት “IFMIS” ሀገር አቀፍ ፕሮጀክት ሲሆን መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅቶ ለማስቀመጥ፣ በእቅድ ለመመራት እና የፋይናንስ ስርዓቱን ከንብረት፣ ከግዥ እና ከሰው ሀብት ጋር አቀናጅቶ ለመስራት እንዲሁም ዓመታዊ ፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብን ለማሻሻል የሚያስችል፤ ወጪን በመቀነስ ጊዜን እና ጉልበትን የሚቆጥብ ስርዓት ነው፡፡
የውይይቱ መነሻ ሀሳቡ የቀረበው የገንዘብ ሚኒስተር ልዑካን በሆኑት በአቶ ዳንኤል ቸርነት አማካኝነት እንዲሁም አቶ ሰሎሞን ከበደ ደግሞ የዘመነ ፋይናንስ ስርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚተገበሩ የአይ.ሲ.ቲ መሰረተ ልማቶች እና ኔትወርክ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ተወካዮች ተሳትፈውበታል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) የፋይናንስ ስርዓቱን ማዘመን አስፈላጊ በመሆኑ በዩኒቨርሲቲው ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲያደረግ እና ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲሟሉ አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን ከተሳታፊዎች በተነሱ አስተያየት እና ጥያቄዎች ዳብሮ ውይይቱ ጠጠናቋል፡፡
መጋቢት 7/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
567 views05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 08:13:03
ለአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ።

በ2015 ዓ.ም ወደ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚተገበሩ ህግና ደንቦች ላይ ያተኮረ ገለፃ ተደርጓል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ዲን የሆኑት ጌታየ ሙሉጌታ ገለፃው ዩኒቨርስቲው በዚህ ዓመት ለተቀበላቸው የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የማሻሻያ ትምህርት ከመጀመራቸው በ4ወር በግቢ ቆይታቸው ስለሚኖራቸው እንቅስቃሴ ያተኮረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ዲኑ አያይዘውም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የአቅም ማሻሻያ ትምህርታቸውን በአግባቡ ተከታትለው በስኬት እንዲያጠናቅቁ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን ህግ እና ደንብ በማክበር መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡

የቤተ መጽሃፍት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ የኔወርቅ በላይነህ የቤተ-መጽሐፍት አጠቃቀም ህግና ደንቦች፣ በላይ ዘለቀ (ዶ/ር) የተማሪዎች መኝታ እና ምግብ አገልግሎት አሰራር ሂደት ላይ የተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።

መጋቢት 6/2015ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
510 views05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 08:12:06
የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ዘመቻ በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል መካሄድ ጀምሯል፡፡
ከመጋቢት 05-10/2015 ዓ.ም የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሂማልያ ካታራክት ፕሮጀክት (HCP) ጋር በመተባበር በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ዘመቻ በማካሄድ ላይ ሲሆን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይን ህክምና ስፔሻሊስቶችም ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በጥምረት በህክምና ዘመቻው እያገለገሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid05XfDudoVjTcaQAGZt1PFKT9XDWnzH9jV3quQn5vYi9ebUXhgNTfXRf5iti2bTbo7l/?app=fbl
556 views05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 17:19:55
you are all invited.
1.7K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 19:40:00
አንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከ አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ (Agri service Ethiopia) ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
---------------
ዩኒቨርሲቲው ስምምነቱን የተፈራረመው አንከሻ ወረዳ ከሚገኘው እና ማህበረሰብ ልማት ላይ ከተመሰረተው “አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ” ከተሰኘ ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር ሲሆን በግብርና እና በተለያዩ የሙያ መስኮች ላይ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ተግባራትን ለማከናወን በሚያስችል አቅጣጫ ነው፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ ዶ/ር አግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ በዘረጋው ሥርዓት ዩኒቨርሲቲው ያለውን ኃይል በመጠቀም በምርምር ታግዞ በርካታ ችግር ፈቺ ተግባራትን በማከናወን በግብርና፣ በጤና እና በትምህርት እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች የማህበረሰቡን ችግሮች መፍታት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡

የአግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ ከአንከሻ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በወረዳው ውስጥ ካሉ ቀበሌዎች ስድስቱን በመምረጥ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያሉን የማህበረሰብ ክፍል ቅድሚያ ዕድሉን በመስጠት እና በመለየት የስንዴ፣ የጤፍ እና የበቆሎ ምርጥ ዘር በማቅረብ፣ ለእንስሳት እርባታ የሚሆኑ በጎችን እና ዶሮዎችን በመስጠት፣ የጓሮ አትክልት ዘሮችን በማቅረብ፣ ለአሲዳማ መሬት ማከሚያ የሚሆን ኖራ በነጻ በመስጠት ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ የተለያዩ ልማታዊ እና ግብረገባዊ ስልጠናዎችን እየሰጠ የሚገኝ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid034nQeCkvv2zXv5YqYARXSsdBP7EYHWiR3Nx9E9oHHrTbHqeuihnDLRWfQq2zXKfzLl/?app=fbl
መጋቢት 5/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
2.3K views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ