Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-12-02 22:38:33
19ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡

"ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ቃል በሀገራችን ለ18ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ደግሞ ለ5ኛ ጊዜ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋርዳቸወው ወርቁ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው በዘንድሮው ዓመት የህዝቡን ሮሮ እና ጥያቄ መሰረት በማድረግ ከጸረ ሙስና ኮሚሽን ባሻገር በሀገር አቀፍ ደረጃ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በተግባር የታገዘ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል። እንደ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ነባራዊ ሁኔታ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የሥራ ክፍሎችን በመለየትና ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ያለውን ክፍተት ለመሙላት በተግባር የታገዘ እንቅስቃሴ ከሁሉም ሠራተኛ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል።

የዕለቱን የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የፀረ-ሙስናና ሥነ- ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደሳለው ጌታሁን የፀረ ሙስና ቀን በየዓመቱ ኅዳር ወር እንደሚከበር ጠቅሰው የሁሉም ሀገራት ከፍተኛ ተግዳሮት የሆነው ሙስና እጅግ በረቀቀ መንገድ የሚፈፀም ወንጀል በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ነቅቶ በመታገል የበኩሉን ሀገራዊ ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በመነሻ ጽሑፉም የሙስና ምንነት፣ የሙስና ወንጀል ልዩ ባህሪያት፣ የፀረ-ሙስና ትግል በኢትዮጵያ አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችና የባለድርሻ አካላት ሚና የሚሉ አርዕስቶች የተዳሰሱ ሲሆን የሥራ ክፍሉ ባለፉት አራት ዓመታት ውስጥ ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በበዓሉ አከባበር የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅቶች እንዲሁም የዕለቱን በዓል የተመለከቱ የጥያቄና መልስ ውድድር በተማሪዎች የተካሄደ ሲሆን ለአሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
ኅዳር 23/2015 ዓ.ም
608 views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 22:29:28
የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ና አካል ጉዳተኞች ቀን በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡

“ራሳችንን እናስመርምር፤ ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ኤች. ኤ.ቪን እንግታ” በሚል መሪቃል የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ፣ በኢትዮጵያ ለ34ኛ ጊዜ፣ እንዲሁም “የፈጠራ ሥራ ሽግግራዊ መፍትሄ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ተደራሽነት” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ31ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ30ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ደግሞ ለ5ኛ ጊዜ በልዩ ልዩ መርሐ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ደብሪቱ ምናየሁ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው ኤች.አይ.ቪ ኤድስ በሀገራችን እየተስፋፋ መምጣቱን ጠቅሰው የወረርሽኙን ስርጭትን ለመግታትና ለመቆጣጠር እንዲሁም የአካል የአካል ጉዳተኞች እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉም የመሪነት ሚናውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭት ላይ ከፍተኛ የሆነ መዘናጋት እየታዬ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡ ማህበረሰቡ ስለአካል ጉዳተኞች ያለውን አመለካከት እንዲቀየር ተከታታይ የሆኑ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የህክምና ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ቃል-አብ እሱባለው በጽሑፋቸው የኤች.አይ .ቪ ኤድስ ሥርጭትን ለመከላከል በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሊሰራበት እንደሚገባ አሳስበዋል። የልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ክፍል መምህር አቶ ሀብታሙ አለምነህ በበኩላቸው ደግሞ ማህበረሰቡ በአካል ጉዳተኝነት ዙሪያ ስላለው አመለካከት አካል ጉዳተኞችን ወክለው ዘርዘር ያለ ሙያዊ ማብራሪያ የያዘ ፅሑፍ አቅርበዋል፡፡
ኅዳር 23/2015 ዓ.ም
671 views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 14:48:27
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ከተማ ለሚገኙ አትሌቶች የትጥቅ ድጋፍ አደረገ፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ በእንጅባራ ከተማ ለሚገኙ 40 አትሌቶችና ለ2 አሰልጣኞች 480 ሽህ ብር ግምት ያለው የትራክ መሮጫ ጫማና የልምምድ ትጥቅ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸዉ ወርቁ (ዶ/ር) በልምምድ ቦታው ተገኝተው ድጋፉን ባስረከቡት ወቅት ዩንቨርሲቲው ስልጠና ከሚሰጥባቸዉ ዘርፎች አንዱ የስፖርት ትምህርት ክፍል መሆኑን ጠቅሰው ይህን የትምህርት ክፍል ለማጎልበት በግቢ ከሚሰጠዉ ስልጠና በተጨማሪ በእንጅባራ ከተማና አካባቢዋ የሚገኙ ተሰጥኦ ያላቸዉን አትሌቶች መደገፍና ማበረታታት የሁልጊዜ ተግባራችን ሊሆን ይገባል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በዚህ ተግባር ስንበረታ ሀገራችንን በዓለም አደባባይ ሰንደቋን ከፍ የሚያደርጉ አትሌቶችን ማፍራት እንችላለን ብለዋል፡፡
የእንጅባራ ከተማ አስተዳድር ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸዉ ጥላሁን በበኩላቸላው በእንጅባራ አትሌቲክስ ክለብ ጥሩ ዉጤት ያላቸዉ አትሌቶችን ከማፍራት አንጻር ከተማ አስተዳደሩ እያገዘ መሆኑን ጠቅሰው በዛሬው እለት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ያደረገው ድጋፍ ግን እፎይታን የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዩንቨርውቲዉ ይህን በጎ ተግባርም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
አሰልጣኝ አሸብር አንበሉ እንደገለጹት የልምምድ ቦታ፣ የዉድድር መሮጫ ትጥቅ/አልባሳት የመሳሰሉትን ችግሮች ከመቅረፍ አንፃር ዩንቨርሲቲው ባደረገላቸው ድጋፍ ችግራቸው መቀረፉን አንስተው የተሻለ ልምምድ በማድረግ ጥሩ ዉጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
Injibara Communication.
2.2K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 17:06:43
በድጋሜ የወጣ የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ፦
*******
ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረ አመልካቾች ከኅዳር 20-22/2015 ዓ.ም በወጣው የፈተና ፕሮግራም መሰረት በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን።
2.0K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 17:04:45
በግብርና፣ ምግብና አየር ንብረት ሳይንስ ኮሌጅ የምርምር ሥራዎች አፈጻጸም እና የወደፊት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ።
በውይይት መድረኩ በኮሌጁ የተከናወኑ የግብርና ምርምር ሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በከፍተኛ አመራሩ ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች ተነስተው የወደፊት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
የኮሌጁ ዲን ሀብታሙ አድማስ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው በግብርናው ዘርፍ በተካሄዱ ምርመሮች ላይ ያለውን አፈፃፀም በመገምገም ግብዓት የሚገኝበት መድረክ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ግብርና የማህበረሰቡ ህልውና እንዲሁም የሀገር ኢኮኖሚ ዋልታ መሆኑን የገለጹት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከለያቸው የትኩረት መስኮች በቀዳሚነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል።
"የምርምር አብዮት" ያስፈልገናል ያሉት ፕሬዝደንቱ ከዚህ በፊት በተካሄዱ የምርምር ሥራዎች ላይ የነበሩትን ክፍተቶች በማሻሻል ለወደፊቱ በማህበረሰቡ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ችግር ፈቺና በሁሉም የግብርና ዘርፎች ውጤታማ የሚያደርጉ ጥናትና ምርምሮችን ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው የምርምር ሃሳቦችን ተገቢነት ከመቅረፅ ጀምሮ ሁሉም ተመራማሪ ሃላፊነት እንዳለበት ተናግረው ተናገረው በቅርቡ ወደ ዩኒቨርሲቲው የተቀላቀሉ የካበተ ልምድ ያላቸው መምህራንም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ እምነታቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
በውይይት መድረኩ የኮሌጁ የምርምር ሥራዎች ግምገማ ሪፖርት በአቶ ዮናስ ደረበ እና የመስክ ጉብኝት ግምገማ ብርሃኔ (ዶ/ር) አማካኝነት የቀረበ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና መምህራን በተነሱ አስተያየቶች ዳብሮ በከፍተኛ አመራሩ የወደፊት አቅጣጫም ተቀምጧል።
ኅዳር 16/2015 ዓ.ም
1.9K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 12:39:16
2.1K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 12:39:15
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሳምንታዊ የቴሊቪዥን ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ስለዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ መረጃ ገለጻ አድርገዋል። የዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ እንዲሁም የትኩረት መስክ አድርጎ በለያቸው ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚያከናወናቸውን ተግባራት፣ ተሞክሮዎችን ለማስፋት ተጨማሪ ጉልበት የሚሆን በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በየ15 ቀኑ የሚተላለፍ ፕሮግራም መጀመሩን አብስረዋል።
በመርሐ-ግብሩ የዩኒቨርሲቲው የህዝብ እና የውጭ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መ/ርት ይርጋ ታደሰ የፕሮግራሙ አስፈላጊነት መሰረት ያደረገ ገለፃ አድርገዋል።
ከዚህ በፊት በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎች ተደራሽ ሲደረጉ መቆየታቸውን ጠቅሰው ከዩኒቨርሲው ማስፋፊያ ሥራዎች አንጻር በቴሌቪዥን አየር ሰዓት ተደራሽ ለማድረግ መሰራቱን ገልፀዋል።
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተወካይ እና የብራንዲንግና ሁነት ዝግጅት ም/ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሰረት አስማረ በበኩላቸው የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ስራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተደራሽ ለማድረስ እንሰራለን ብለዋል።
ተሳታፊዎችም ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን ተግባራት ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ ያለበትን ሂደት አድንቀው በፕሮግሙ መደሰታቸውንም ገልጸዋል።

በመርሐ-ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የአዊ ብሄ/አስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የካውንስል አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በየ15 ቀኑ የሚተላለፍባቸው ቀናት፦
ቅዳሜ ምሽት፡ 1፡30-2፡00
ማክሰኞ ረፋድ፡ 5፡30-6፡00
ሐሙስ ቀን፡ 10-30-11-00 ናቸው

ህዳር 15/2015ዓ.ም
2.2K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 21:10:32
እንኳን ደስ አላችሁ!
///////////////////
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር በየ 15 ቀኑ ለ30 ደቂቃ የሚተላለፍ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ወደ ተመልካች ለማድረስ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቋል።

ይህን ፕሮግራም በይፋ ለማስጀመር ኅዳር 15/2015 ዓ.ም ልዩ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል።

ቦታ፡ በዩኒቨርሲቲው ሴሚናር አዳራሽ
2.0K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 21:09:51
በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ላይ ጉብኝት ተካሄደ፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና፣ ምግብና አየር ንብረት ሳይንስ ኮሌጅ ከፋሲሊቲ ማኔጅመንት ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በተዘጋጀው ችግኝ ጣቢያ የተለያየ ዝርያ ያለቸውን ችግኞች በማፍላት ለተለያዩ ተቋማት፣ ለተራቆቱ ቦታዎች ለውበትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚሆኑ ችግኞች ተሰራጭተው መተከላቸው ይታወሳል፡፡

በጉብኝት መርሐ ግብሩ የግብርና፣ ምግብና አየር ንብረት ሳይንስ ኮሌጅ ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) ከኮሌጁ መምህራን ጋር በመሆን በየወረዳዎቹ በማህበረሰብ አገልግሎት በኩል ተሰራጭተው የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን ሁኔታ በመጎብኘትና በመገምገም ከቀበሌ ሥራ አስኪያጆችና የተቋም መሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ የተተከሉት ችግኞች በጥሩ እንክብካቤና አያያዝ ላይ ያሉ መሆናቸውን በመጎብኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ዩኒቨርሲቲው በአረንጓዴ ልማት ዘርፍ በትብብር ከሚሰሩ አካላት ጋር እነዚህን መሰል ተግባራት በቀጣይነት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የአረንጓዴ ልማት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፈቃዱ ጥሩነህ በበኩላቸው በዞኑ ውስጥ ያለውን የደን ሽፋን ከፍ ለማድረግ በዩኒቨርሲቲው የችግኝ ጣቢያ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሚተከሉ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ገልፀው በችግኝ ጣቢያው ውስጥ ከሚሰሩት በርካታ ሥራዎች በተጨማሪ በተለያዩ ጊዜያት ተሰራጭተው የተተከሉ ችግኞችን በቅርብ ርቀት በየጊዜው የክትትልና ቁጥጥር ተግባራትን እንደሚያከናወን ተናግረዋል፡፡
በጉብኝቱ መርሐ ግብሩ ዳንግላ ከተማ 02 ቀበሌ ለመንገድ ዳር ውበት የተተከሉ ችግኞች፣ አዲስ ቅዳም ከተማ የአረንጓዴ ልማት ክልል ውስጥ የተተከሉ ችግኞች፣ እንጅባራ አጠ/1ኛ ደ/ት/ቤትን ለማስዋብ የተተከሉ ችግኞችና በባንጃ ወረዳ የገጠር ቀበሌ የተተከሉ ችግኞች ተካተዋል፡፡
ኅዳር 13/2015 ዓ.ም
1.9K views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 21:06:07
ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡

ዓለም አቀፍ የሕፃናት ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ፤ በሀገራችን ለ17ኛ ጊዜ እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህፃናት ማቆያ ማዕከል ተከብሯል፡፡

በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ለቤተሰቦቻቸው በማሰብ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ህፃናት ጤንነታቸው ተጠብቆ፣ እድገታቸው ዳብሮ አዕምሯቸው ጎልብቶ በሰላም እንዲያድጉ፤ ወላጆችም ያለምንም ችግር በተሳካ ሁኔታ ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት ደረጃውን የጠበቀ የኅጻናት ማቆያ ማዕከል መክፈቱን ተናግረዋል፡፡
አያይዘውም ማዕከሉ መከፈቱ ብቻ ግብ አለመሆኑንና ህፃናት የሚያስፈልጋቸውን ነገር እንዲያገኙ የማዕከሉ ሠራተኞች፣ ወላጆችና ዩኒቨርሲቲው የሚጠበቅቸውን ኃላፊነት መወጣት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የማዕከሉ ሠራተኞችም ለህፃናት የሚገባውን እንክብካቤ መስጠት እንዳለባቸው በማሳሰብ የዩኒቨርሲቲው አመራር ለህጻናት ማቆያ ማዕከሉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ አስፈላጊውን ግብዓት እንደሚያሟላ ገልፀዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች፣ ኅፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ደብሪቱ ምናየሁ በበኩላቸው የዩቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር ኃላፊነት ወስዶ በቁርጠንኝነት ይህን ማእከል በመገንባቱ ምስጋናቸውን አቅርበው ዓለም አቀፍ የኅፃናት ቀን ሲከበር ለህፃናት የሚያስፈልገውን እንክብካቤ በማድረግ ኃላፊነት ሁሉም ሊወስድ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ኅዳር 13/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.9K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ