Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-10-28 21:10:24
ለአማራ ፖሊስ ኮሌጅ መምህራን ከፍተኛ ዲፕሎማ (HDP) ስልጠና መስጠት ተጀመረ፡፡
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአማራ ፖሊስ ኮሌጅ 40 መምህራን የከፍተኛ ዲፕሎማ ፕሮግራም (HDP) ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀምሯል፡፡
በስልጠናው የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ(ዶ/ር) የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ስለ ዩኒቨርሲቲው አጭር ገለጻ ያደረጉ አድርገዋል፡፡ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ አጋር አካላት ጋር በጋራ ለመስራት የተለያዩ የመግባቢያ ስምምነቶችን እንደተፈራረመ ጠቅሰው ከአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረትም ይህን የከፍተኛ ዲፕሎማ (HDP) ስልጠና ለኮሌጁ መምህራን እንዲሰጥ ማድረጉን ተናግረው ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
ስልጠናውን ያስጀመሩት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር እና የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ም/ኮሚሽነር አንማው አለሜ እንደተናገሩት ኮሌጁ ባለፈው ዓመት ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን ገልጸው ኮሌጁ በከፍተኛ ዕድገት እንዲሸጋገር ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ድጋፎችን ለኮሌጁ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው ለኮሌጁ የተሻለ የሰው ኃይል እንዲኖረው የሚያደርግ በመሆኑ ሰልጣኝ መምህራን ስልጠናውን በመውሰድ ወደ ተግባር መቀየር ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ለተከታታይ 16 ቀናት የሚቆየው ስልጠና ለ40 መምህራን የሚሰጥ ሲሆን አሰልጣኞችም ስንታየሁ በላይ(ዶ/ር) ስርዓተ ትምህርት መምህር፣ አበበ ፈንታሁን (ረ/ፕሮፌሰር) ታሪክ እናቅርስ አስተዳደር መምህር፣ ታደለ ሽፈራው(ረ/ፕሮፌሰር) የፊዚክስ መምህር እና አስናቀ ተሻገር(ረ/ፕሮፌሰር) እንግሊዝኛ መምህር ናቸው፡፡
ጥቅምት 18/2015 ዓ.ም ፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
3.2K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 17:56:43
ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያው ዙር ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ፡፡
---------
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የማኅበራዊ ዘርፍ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂ ፈተና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዛሬ መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ ፈተናውን የወሰዱት ከ9ሺ በላይ ተማሪዎች ሲሆኑ ቀድሞ በተደረገላቸው ገለፃ እና አቅጣጫ ስድስቱንም ፈተና በሰላም አጠናቀዋል፡፡
ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘው እንደገለጹት የፈተና ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የፈተና ግብረ ኃይል ኮሚቴዎች፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተላኩ ፈተና አስፈጻሚዎች እና የፀጥታ ኃይሎች በጋራ የመሥራት ውጤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፈተናቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ጥቅምት 2 እና 3/2015 ዓ.ም መኪና ተዘጋጅቶላቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተሸኙ ሲሆን ጥቅምት 4/2015 ዓ.ም የሚገቡትን የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ተቀብሎ ለማስፈተን ዩኒቨርሲቲው ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቁንም አክለው ገልጸዋል፡፡
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ውጤት ይመኛል!
መስከረም 2/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.2K views14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 18:30:44 https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0NWXyk5eefZQFxLACNdkmmK8HMg4RNzpnSNu7NsnR6UiUK9HmYfMBAaBwHoTpVPTKl/?app=fbl
1.9K views15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 18:30:50
1.0K views15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 18:30:50
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለፈተና የተመደቡለትን ተማሪዎች መቀበል ጀመረ፡፡

ተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን ደህና መጣችሁ!

አዲናስ!

በዛሬው እለት ከቻግኒ፣ ከጃዊ፣ ከዚገምና ጓንጓ ወረዳዎች 3,884 ተፈታኝ ተማሪዎች በሰላም ወደ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት አዕምሮ ታደሰ (ዶ/ር) እና የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝደንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) በተማሪዎች ማደሪያ እና መመገቢያ አካባቢያ ያለውን ዝግጅት አድንቀ ተማሪዎች ግቢ ውስጥ በሚቆዩበት ጊዜ የዩኒቨርሲቲውን ህግና ደንብ አክብረው በመልካም ስነ ምግባር እንዲቆዩ አሳስበዋል፡፡
ተማሪዎችም በተደረገላቸው አቀባበል እና የሚፈልጉትን መረጃ በቀላሉ ማግኘት በመቻላቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡

መስከረም 26/2015 ዓ.ም፣ የህዝብና ውጭ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
1.0K views15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:41:28
1.6K views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:40:51
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ የተመደቡለትን ተፈታኝ ተማሪዎችን
ተቀብሎ ለማስተናገድ አስፈላጊ ዝግጅቶችን ያጠናቀቀ ሲሆን እንኳን ደህና መጣችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲያችን ከገባችሁ በኋላ የመኝታ ህንጻ ቁጥር ከታች በተገለጸው የስም ቅደም ተከተል መሰረት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካም የፈተና ጊዜ!
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.6K views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 16:05:34

1.1K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 08:38:28 ቦርዲንግ ፓስ አውሮፕላን ስትሳፈሩ አየር መንገድ የሚሰጣችሁ ነው፣ ከቦርዲንግ ፓስ በተጨማሪ ትኬት ስትቆርጡ ደረሰኝ መያዛችሁን እንዳትረሱ
2.0K views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 08:33:54 ሰላም ውድ ለብሔራዊ ፈተና የምትሳተፍ  መምህራን ፣
ከታች የምትመለከቱት ከሀገረ አቀፍ ፈተናዎች አግልግሎት ዋና  ዳይሬክተር  ዶ/ር  እሸቱ ከበደ የተላከ ነው( so you shall act as soon as possible)
@@@@

ክቡራን የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች
ጤና ይስጥልኝ

ፈታኞች ( Invigilators)  ወደ ተመደቡበት ሲጓዙ መደበኛና ልዩ የህዝብ ማመላለሻ መኪናዎችን እና የአየር መንገዶችን መጠቀም የሚችሉ ይሆናል። በሚያመጡት ህጋዊ ደረሰኝ ይወራረዳል። አየር መንገድ የተጠቀሙ ከሆነ ቦርድንግ ፓስ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

ለተሻለ ውጤት በጋራ እንተጋለን። በፈጣሪ እርዳታ እንችላለን።

እሸቱ ከበደ
ዋና ዳይሬክተር
2.9K views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ