Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2022-08-03 16:53:07 https://www.linkedin.com/posts/stempower_insideabreveryabrchildabrisabraabrscientist-activity-6960575272576245760--kNB?utm_source=linkedin_share&utm_medium=android_app
1.3K views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:54:04
በፕሬዝደንት ጽ/ቤት ሥር ያሉ የሥራ ክፍሎች ዓመታዊ የሥራ ሪፖርት ግምገማ አካሄዱ፡፡
ተጠሪነታቸው ለፕሬዝደንት ጽ/ቤት የሆኑ የሥራ ክፍሎች የ2014 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በማቅረብ ግምገማ አካሂደዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ ዶ/ር ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በማንሳት የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ለይቶ ለቀጣይ እቅድ መነሻ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚህም መሰረት የኢንፎርሜሽን ኮምውኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፣ የህዝና ውጭ ግንኙነት፣ የውስጥ ኦዲት፣ የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ፣ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና፣ የህግ አገልግሎት፣ የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡
በተመሳሳይ ቀደም ሲል የቤተ መጻሕፍት ዳይሬክቶሬት ዓመታዊ ሪፖርት ቀርቦ ከሥራ ክፍሉ ሠራተኞች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡
በቀረበው ሪፖርት መሠረትም ግምገማ በማድረግና ለቀጣይ ግብዓት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማው ተጠናቋል፡፡
ሐምሌ 25/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.7K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 18:48:07
የSTEM የአሌክትሮኒክስ ቤተ-ሙከራዎች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ፡፡
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ STEM Power ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውሥጥ ለሳይንስ፣ቴክኖሎጅ፣ኢንጅነሪንግ እና ሂሳብ ትምህሮቶች የሚያገለግሉ የቬርቹዋል እና ኤሌክትሮኒክስ ሁለት ቤተ-ሙከራዎችን ስራ አስጀምሯል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ (ዶ/ር) ያደጉ ሀገራት አሁን ያሉበት ደረጃ የደረሱት በሳይንስ ዘርፍ ከፍተኛ ስራ በመስራታቸው መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው ለዚህ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኤሌክትሮኒክስ ቤተ-ሙከራዎች ከ STEM Power ጋር በመተባበር ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም በዩኒቨርሲቲው በኩል የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ስለተሟሉ ተማሪዎች በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የእንጅባራዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) ይህ ፕሮግራም እንዲሣካ ከፍተኛ ጥረት ላደረጉ ለተፈጥሮ እና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ እና ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሩክቶሬትን አመስግነው STEM ቤተ-ሙከራዎች ንድፈ ሃሳብን በተግባር ለመስራት የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የSTEM ኦፕሬሽን ማኔጀር የሆኑት አቶ አንተነህ ፍስሃ በበኩላቸው ድርጅቱ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ቤተ-ሙከራዎችን መስራት እና ስለ ቤተ-ሙከራዎቹ አስፈላጊውን ስልጠና በመስጠት ለተለያዩ ተቋማት እንደሚያስረክብ ተናግረው “Inside every child is A scientist'' በሚል መሪ ቃል በሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ኢንጅነሪንግ እና ሂሳብ ዘርፎች አተኩሮ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ሐምሌ 25/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.8K views15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 09:47:22
የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመራሮች ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል አመራር እና ሰራተኞች ጋር ዉይይት አካሄዱ!!
.....
የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ እና የእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል አብረው ለመስራት ቀደም ሲል የጋራ መግባቢያ ሰነድ(MOU) መፈራረማቸው ይታወሳል። በዚህም መሰረት የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን እና የጤና ባለሞያዎች ተግባር ተኮር የመማር ማስተማር ሂደትን ለማስቀጠል ከሆስፒታሉ አስተዳደሮች እና ሠራተኞች ጋር ዉይይት አድርገዋል።

በዉይይቱም የመማር ማስተማርን ፣ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች ግንኙነት ፣ የግብአት እና የቁሳቁስ ድጋፍ፣ የሰዉ ሀይል ስምሪት፣ የስልጠናዎችን እና የትምህርት እድሎችን የተመለከቱ ሀሳቦች ተነስተዋል።
ለተነሱ ሀሳቦችም በሁለቱም ተቋማት በኩል ያሉ አመራሮች ማብራሪያ እና ምላሽ ሰጥተዉባቸዋል።
በዚህም የጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን ቀጣይነት ባለው መንገድ ከሆስፒታሉ ጋር የሚሠሩበት መንገድ ተመቻችቷል።

በተያያዘም ዩኒቨርሲቲው ግምታቸው ከ 50,000 በላይ ብር የሚገመቱ ለሆስፒታሉ ግቢ ማስዋቢያ አግልግሎት የሚውሉ 12 አይነት በጠቅላላ 59 ያህል ቁሳቁሶችን በስጦታ አበርክቷል።
የጠቅላላ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶር ዜናው አብሮነታችን የሚቀጥል ቢሆንም እየተደረገልን ላለው ትብብር ዩኒቨርሲቲያችንን እጅግ እናመሰግናለን ብለዋል።

ሐምሌ23/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.3K views06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 16:44:41
1.6K views13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 16:44:40
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም በጀት አጠቃቀምና የ2015 ዓ.ም የቸመደበ መደበኛ በጀት እና ወጪ መረጃ
1.6K views13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 20:58:41
የኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሃጂ ኢብሳ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አደረጉ፡፡

አቶ ሃጂ ኢብሳ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ም/ፕሬዝደንቶች እንዲሁም የግንባታ ፕሮጀክት ባለሙያዎች በተገኙበት እየተከናወኑ ያሉ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) ስለ ዩኒቨርሲቲው ገፅታ አጭር ገለፃ በማድረግ በ2014 ዓ.ም የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አፈፃፀም አቅርበዋል፡፡
አቶ ሃጂ በቀረበው ገለፃ እና ባደረጉት ጉብኝት በዩኒቨርሲቲው ሥራ አፈፃፀም መደሰታቸውን በመግለፅ በቀጣይም ኤጀንሲው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲውም ከዋና መስሪያ ቤቱ እየተደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና የሚሆን የአካባቢውን ባህል የሚገልፅ የጋቢና ጭራ ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ በተመሳሳይ በጉብኝቱ ለተሳተፉት የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ጀጃው ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

ሐምሌ 21/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ለተጨማሪ መረጃ የሚከተሉትን የመረጃ መረቦች ይጠቀሙ!
ለቴሌግራም-https://t.me/injiuniversity
ለኢንስታግራም -https://www.instagram.com/injibara12
ለዌብ ሳይት- https://www.inu.edu.et/
ለፌስ ቡክ ገፃችን -https://www.facebook. Com/injibaruni
ለኢሜይል- injibarau@gmail.com
ለInstitution Email -injibarauniversity@inu.edu.et
ለትዊተር- Twitter (https://twitter.com/injibara_Inu/)
ለዩቱዩብ-https://www.youtube.com/c/injibarauniversity

Explore Your Creative Potential.
1.9K views17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 18:17:55
ለአዲስ ገቢ የክረምት ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ።

በእንጅባራ ዩኒቨርስቲ በክረምት መርሐ ግብር ለሚማሩ ከ1,500 በላይ አዲስ ተማሪዎች በተከታታይ ትምህርት አሰራር ፣ በተማሪዎች አገልግሎት መመሪያ፣ በቤተ-መጻሕፍት አጠቃቀም እና በምዝገባ ሂደት ላይ ያተኮረ ገለጻ ተደርጓል።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሽዋስ ፈንታሁን ተማሪዎች ስለሚኖራቸው ቆይታ፣ ስለ ተከታታይና ርቀት ትምህርት መመሪያ፣ ስለ ተማሪዎች መብትና ግዴታ፣ ስለቤተ-መጽሐፍት አጠቃቀም እና ክፍያን በተመለከተ ገለፃ ሰጥተዋል።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በላይ ዘለቀ(ዶ/ር) ደግሞ ተማሪዎች በግቢ ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ ስለተማሪዎች ዲስፕሊን መመሪያ፣ ስለ ምግብና ምኝታ አጠቃቀም ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ትኩረት ሰጥተው መከታተል እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በተጨማሪም የሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ይመር ቸኮል በበኩላቸው የአካዳሚክ ካሌንደር፣ የተከታታይ ትምህርት ውጤት አሰጣጥ፣ የፈተና ጊዜ ህግና ደንብ፣ የተማሪ ዝውውር እና ውጤት አመዘጋገብ ሥርዓት ላይ አተኩረውገለፃ አድርገዋል።

ሐምሌ19/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.3K views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 18:17:01
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከባህርዳርና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን በታላቁ አባይ ወንዝ መነሻ ግሽ አባይ ተራራን ለማልማት ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ችግኝ ተከላ አካሂዷል።

ሐምሌ 18/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የታላቁን አባይ ወንዝ አካባቢ ለማልማት አንዱ ትኩረት በሆነው የተፈጥሮ ጥበቃን መሠረት ያደረገ በሦስቱም ዩኒቨርሲቲዎች እና በአካባቢው ማህበረሰብ ቅንጅት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ተካሂዷል።

ወደፊት በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በቱሪዝም፣ በአትሌቲክስ መንደር ምስረታ አካባቢውን ለማልማትና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ሦስቱም ዩኒቨርሲቲዎች በቅንጅት እንደሚሰሩ በመርሐ ግብሩ ተገልጿል።

በዚህ መርሐ ግብር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) እና ሌሎች ልዑካን እንዲሁም የባህርዳርና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዝደንቶችና አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።
1.2K views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 20:56:33
389 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ