Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-09-29 19:15:05
የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቅድመ እና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞችን ማጽደቅን ጨምሮ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ።

ዩኒቨርሲቲው ከ2015 ዓ.ም በፊት ከነበሩት 46 የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች ላይ ተጨማሪ 14 እንዲሁም በነበሩት 13 የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ላይ ተጨማሪ 29 አዳዲስ ፕሮግራሞችን አፅድቋል።

በተያያዘም አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ሰባት ትምህርት ክፍሎችን በመያዝ የኢንጅነሪግ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ እንዲከፈት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

በሌላ በኩል ሴኔቱ በተለያዩ ጊዜያት በውስጥና በውጭ ገምጋሚዎች ሲታይ የነበረውን "Injibara Journal of Business and Social sciences" የተሰኘ ጆርናል እንዲቋቋም የወሰነ ሲሆን የጆርናሉን ፖሊሲም አጽድቋል።

በመጨረሻም "የአዊ ባህል፣ ቋንቋ እና ታሪክ ኢንስቲትዩት" የሚል ስያሜ የነበረውን ኢንስቲትዩት ግልጽ፣ ቀላልና አካታች በሆነ ስያሜ እንዲቀጥል ለማድረግ ይቻል ዘንድ "የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት" በሚል እንዲጠራ ወስኗል።

መስከረም 19/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
894 views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 15:19:35
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁ ተገለጸ፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ፈተናውን በተሳካ መንገድ ለማጠናቀቅ በፕሬዝዳንቱ የሚመራ አብይ ኮሚቴ እና በሥሩ የተለያዩ ኮሚቴዎችን በማዋቀር የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህም መሰረት በአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት የሚመራ የፈተና አሰጣጥ ግብረ ኃይል ተዋቅረዋል።
አያይዘውም ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም በመጀመሪያው ዙር 9,661 የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እንዲሁም በሁለተኛው ዙር 6,323 ተማሪዎች በድምሩ 15,981 ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ገልጸው የፈተና አሠጣጡን የተሳካ ለማድረግ ሁሉም የመፈተኛ ክፍሎች እና የፈተና ማስቀመጫ ቦታዎች ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በአገልግሎት አሠጣጥ ግብረ ኃይል በኩል በአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝደንት በወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) የሚመራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ልዩ ልዩ ተግባራትን ማከናወኑ ተገልጿል፡፡ በዚህ ዘርፍም ተማሪዎች በምቹ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አስፈላጊው የምግብ ግብዓት እና ቁሳቁስ የተሟላ ሲሆን በቂ የመኝታ ክፍሎችንም ማዘጋጀት የጤና ችግር ለመፍታት የተማሪዎች ክሊኒክ የተሟላ የ24 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጥ ከመዘጋጀቱም ባሻገር የሳይኮሎጂና የጤና ባለሙያዎች ያቀፈ የጤና ቡድን መዋቀሩን ተናግረዋል፡፡ የፀጥታ ግብረ ኃይልም የተዋቀረ ሲሆን አንቡላንስን ጨምሮ በቂ የትራንስፖርት አቅርቦት መዘጋጀቱን ዶ/ር ወሀቤ አክለው ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በላከው ማንዋል መሰረት ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመሆን ሙሉ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ አጠናቋል።

መስከረም 19/2015 ዓ.ም
1.3K views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 11:49:16
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም መስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት ይሁንልን
መልካም በዓል!
2.5K views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 11:48:37
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአዊን ባህል ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ዩኒቨርሲቲው የአዊ የመስቀል ደመራ በዓል አካባበርን ለማስተዋወቅ እየሰራ መሆኑን የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአዊን ባህል፣ ቋንቋ እና ታሪክ ማጥናት እና መሰነድ አንድ የትኩረት መስክ አድርጎ እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው የ2015 ዓ.ም የመስቀልን በዓል በአዊ ብሄረሰብ በልዩ ድምቀት ለማክበርና ለማስተዋወቅ በኢቲቪ መዝናኛ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ በማድረግ በኩል ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የአዊ ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክ፣ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ አከባበር መረጃ በጽሁፍ፣በድምጽ እና በምስል ተሰንዶ እንዲቀመጥ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2015 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የአዊ ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክ ጥናት ኢንስቲዩት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳየ(ረ/ፕሮፌሰር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የአዊ ቋንቋ፣ ባህል እና ታሪክን ከስሩ ለማጥናት የአጭር እና ረጅም ጊዜ ዕቅድ ነድፎ ወደ ሥራ መግባቱን ጠቅሰው ቋንቋውን እና ባህሉን በማሳደግ የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
የመስቀል ደመራ በዓል በአዊ ዞን ከሚከበሩ ታላላቅ በዓላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው የበዓሉን አከባበር ስነ ስርዓት ለማስተዋወቅም እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
2.4K views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 20:43:18
781 views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 20:43:18
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የመንግስት እና የቢዝነስ ተቋማት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡
-------
ስምምነቱን የተፈራረሙት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣አማራ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኮሙኒኬሽን ኮሚሽን፣ የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣ ልማት ባንክ፣ የአማራ ክልል ስራ እና ስልጠና ቢሮ፣ WA ዘይት ፋብሪካ፣ ፊቤላ እና ሪችላንድ የዘይት ፋብሪካ ጋር ነው፡፡

ይህ የጋራ ስምምነት ፊርማ የተካሄደው ባህርዳር እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጁት የጋራ የምክክር አውደ ጥናት ላይ ሲሆን ፕሮጀክቱ በስራ ዕድል ፈጠራና የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና (Partneship in Business Entrepreneurship and Leadership Transformation (PiBELT Ethiopia) ላይ ያተኮረ ነው፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፐሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) (PiBELT Ethiopia) ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ ከባህርዳርና ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ይህን PiBELT Ethiopia ከተቋማት ጋር መስራቱ ለአካባቢውን ማህበረሰብ የስራ ዕድል ፈጠራን ለማሻሻል እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡
የPiBELT Ethiopia አስተባባሪ የሆኑትና በኢንዲያና ዩኒቨርሲቲ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር እንዲሁም የቀድሞው የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ተሾመ ይዘንጋው (ዶ/ር) እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ ስልጠና የተሰጣቸው 98 ወጣት ስራ ፈጣሪዎች እና 56 የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ያሉት ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
835 views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 08:47:52
ለዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና አስተዳደር ቢሮ ፀሐፊዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡

ጸሐፊዎች በመደበኛ ሙያቸው ያገኙትን እውቀት ለማዳበርና ተጨማሪ ክህሎት እንዲኖራቸው ለማድረግ ታቅዶ የተዘጋጀ ሲሆን
Advanced Computer technical Skill, preventive Maintenance for Computers and Office Machines እንዲሁም በመረጃ አያያዝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዋና ትኩረቱን በማድረግ በዳይሬክቶሬቱ የድጋፍና ቴክኒካል ጥገና ቡድን እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ስልጠናው ከዚህ በፊት መሰጠቱን የጠቀሱት የአይ.ሲ.ቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳውድ ዑመር ዋና ዓላማው የጸሀፊዎችን የኮምፒውተር ቴክኒካል ክህሎት በማዳበር መረጃ አያያዝን በማዘመን የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ነው ብለዋል።

ሥልጠናው በተግባር የኮምፒውተር ልምምድ ታግዞ መሰጠቱ ለፀሐፊዎች ተጨማሪ ክህሎትን ለመስጠትና የመረጃ አያያዝ ሥርዓታቸውን ለማሻሻል ብሎም ለማዘመን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የገለፁት ደግሞ የዳይሬክቶሬቱ የድጋፍና ቴክኒካል ጥገና ቡድን ባለሙያዎች ናቸው።

ለወደፊቱም እንደዚህና መሰል የሆነ መያዛቸውን ገልፀዋል፡፡
መስከረም 11/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
2.1K views05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 17:59:18
የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር (Ethiopian Midwives association) ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ድጋፍ አደረገ፡፡
የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር (Ethiopian Midwives association) ሁለት መቶ ሺ ብር ግምት ያላቸው ለሚድዋይፍ ሀኪሞች የተግባር ልምምድ ማስተማሪያነት የሚያገለግሉ እንደ pelvic anatomy, Delivers set, States cope, Birth simulation እና መሰል ቁሳቁሶች ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ድጋፍ አድርጓል፡፡

መስከረም 9/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የድጋፍ ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር የክትትልና ምዘና ክፍል ኃላፊ አቶ በለጠ በልጉ ኮሌጁ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ሊገጥመው የሚችለውን የተግባር ልምምድ መሳሪያዎች እጥረት ለመቅረፍ ታስቦ የተደረገ ድጋፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አብርሃም አማረ እና የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ዳንኤል አዳነ አንድ በሚያደርግ የጋራ ንግግራቸው የተደረገላቸው ድጋፍ ተማሪዎች የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር በዘርፉ ብቁ ምሩቃን ሆነው እንዲወጡ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በጤና ተቋማት በወሊድ ወቅት በእናቶችና ህፃናት ላይ ሊደርስ የሚችለውን የከፋ ጉዳት ለመቀነስ የሚያችል ዜጋን የማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው በመግለፅ ለተደረገላቸው መልካም ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ለማህበሩ ምስጋናቸውን ከማቅረብ በተጨማሪ በተለይ በጤናው ዘርፍ የተግባር ተኮር ትምህርትን ለማስፋፋት የእንደዚህ ዓይነት የተግባር መሳሪያዎች ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
3.1K views14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 16:10:06
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መቀመጫውን በአሜሪካ ካደረገው "Mihert Medical Supply Group" ከተሰኘ ድርጅት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ።

የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቱ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በማስፋፋት ላይ ለሚገኘው የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ዩኒቨርሲቲው ለማስተማሪያነት ለሚጠቀማቸው የጤና ተቋማት ግብዓቶችን ለማሟላት ያለመ ነው።

ስምምነንቱን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) እና "ምሕረት ሚዲካል ሳፕላይ ግሩፕ" የኢትዮጵያ ዳይሬክተር በሆኑት ህይወት ወልዴ ተፈራርመዋል።

ከዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመስራት እና በአካባቢው ያሉትን የጤና ተቋማት ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን ለማጠናከር ስምምነት ላይ በመድረሳቸው በጣም ደስተኛ መሆናቸውን ዳይሬክተሯ ገልፀዋል።

ነሐሴ 27/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.2K views13:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:31:16
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ሲሰጥ የነበረው አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
-----
ነሐሴ 26/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በዳልሀወስ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ፋካልቲ የስታስቲክስ ፕሮፌሰር በሆኑት በፕሮፌሰር ተሰማ አስታጥቄ አማካኝነት የምርምር ህትመት ዝግጅት እና ታዋቂ ጆርናሎች ላይ እንዴት ማሳተም እንደሚቻል አተኩሮ ለተከታታይ አራት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡

ስልጠናውን ተከታተሉት መምህራም የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ሲሆን ለፕሮፌሰር ተሰማ ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) አማካኝነት የአካባቢው ባህል የሆነው የጋቢና ጭራ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
1.7K views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ