Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-09-01 17:29:49

1.6K views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:41:50
በምርምር ሂደትና ታዋቂ ጆርናሎች ላይ ለማሳተም የሚረዳ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡
በምርምርና ህትመት ዳሬክቶሬት አዘጋጅነት በሀገረ ካናዳ ዳልሀወስ ዩኒቨርሲቲ በግብርና ፋካሊቲ የስታትስቲክስ ፕሮፌሰር በሆኑት ፕሮፌሰር ተሰማ አስታጥቄ ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በምርምርና በታዋቂ ጆርናሎች ላይ እንዴት ማሳታም እንደሚቻል የሚረዳ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡
ነሐሴ 23/2024 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዘርፍ ትኩረት በመስጠት በተለያዩ ጊዜያት የተመራማሪዎችን አቅም ለማጎልበት የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው የዛሬው ስልጠናም የዚህ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምርምር ዘርፍ የካበተ ልምድ ያለቸው ፕሮፌሰር ተሰማ አስታጥቄ በተለያዩ ሀገራት እንዲሁም ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጋር በጋራ የተለያዩ የምርምር ስራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረው ተሳታፊዎቹ ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የምርምርና ህትመት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ታምር በበኩላቸው የስልጠናው ዓላማ የተመራማሪዎችን አቅም በማሳደግ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የሚሰሩ የምርምር ሥራዎችን በታዋቂ ጆርናሎች በማሳተም ዩኒቨርሲቲውን በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስተዋወቅ ነው ብለዋል፡፡ ስልጠናው “Academic Without Border” ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት በተገኘ ድጋፍ እየተሰጠ ሲሆን ለሦስተኛ ዙር መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው “Preparation of manuscripts and the process of publication in reputable journals” በሚል አርዕስት ላይ አተኩሮ ለተከታታይ 4 ቀናት የሚቀጥል እና 125 መምህራንም እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡
1.5K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 16:17:48
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጁና የተሰራጩ የችግኝ ዝርያዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድጋቸው ተገለጸ፡፡
------------------------------------
ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ለልማት ተነሽ አርሶ አደሮች ያሰራጫቸው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ገቢ ማስገኘት መጀመራቸውን ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና፣ ምግብና ዓየር ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የተለያየ ዝርያ ያላቸውን ችግኞችን በማፍላት ለግል እና ለመንግስት ተቋማት፣ ለልማት ተነሺ አርሶ አደሮች እንዲሁም ዙሪያ ወረዳዎች ማከፋፈሉን ተናግረዋል፡፡ በግብርናው ዘርፍ የማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው በእንጅባራ ከተማ ለልማት ተነሽ ለሆኑ አርሶ አደሮች የተሰጡ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች(ጌሾ) ጥቅም መስጠት መጀመራቸውንም ገልፀዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የግቢ አረንጓዴ ልማት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፈቃዱ ጥሩነህ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ለልማት ተነሺ አርሶ አደሮች እና እንጅባራ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ 89 አርሶ አደሮች ከ2ሺ በላይ የጌሾ ችግኞችን በማሰራጨት ተጠቃሚ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡
የልማት ተነሽ አርሶ አደር ከሆኑት መካከል ወ/ሮ አለሚቱ መለሰ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከ2 ዓመት በፊት የሰጣቸው የጌሾ ተክል ሙሉ ሙሉ መፅደቁን እና አሁን ለጥቅም መድረሱን ገልጸው ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ የተለያየ ዝርያ ያላቸውን ተክሎች ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል፡፡
ነሐሴ 19/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
3.2K views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 13:30:24
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና (Medicine) እና በሌሎች ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተገለፀ፡፡
----------------------------
በ2014 ዓ.ም መግቢያ ላይ ሥራ የጀመረው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የህክምና ትምህርትን ለመጀመር ሙሉ ዝግጅት መጠናቀቁን የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አብርሐም አማረ ገልፀዋል፡፡
ኮሌጁ በ2014 ዓ.ም በስምንት የትምህርት ክፍሎች ትምህርት መጀመሩን የጠቀሱት ዶ/ር አብርሐም በ2015 ዓ.ም የህክምና (Medicine) እና ፋርማሲ (Pharmacy) ትምህርትን ጨምሮ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞችን 10 በማድረስ ማለትም (Medicine, Anesthesia, Medical laboratory science, Public health, Nursing, Midwifery, Pediatric Nursing, Psychiatry, and Environmental health science.) እና 6 የድህረምረቃ ፕሮግራሞችን በመጨመር (MPH in General Public Health፣ MPH in Human nutrition፣ MPH in Epidemiology፣ MPH in Reproductive Health፣ MSc in Clinical Midwifery, and MSc in Adult Health Nursing) ለ2015 ዓ.ም ሙሉ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ በህክምና 34 እና በፋርማሲ 30 ተማሪዎች ተለይተው ትምህርት ለማስጀመር በእንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ተፈታኝ ተማሪዎች ምርጫቸውን እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እንዲያደርጉም ዶ/ር አብርሐም አሳስበዋል፡፡
ነሐሴ 18/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.2K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 10:35:10

1.3K views07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 10:26:51

1.8K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:07:20
2.4K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:07:14
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ
*****
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከታች በተገለፁት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
መስፈርቱን የምታሟሉ ከዛሬ ጀምሮ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
2.2K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 19:50:12
ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የአንስቴዥያ ማሽን ድጋፍ ተደረገ፡፡
ሐምሌ 29/2014ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት 1ሚሊዬን ሁለት መቶ ሽህ ብር ግምት ያለው የህክምና/አንስቴዥያ ማሽን ለእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ድጋፍ አድርጓል፡፡
በድጋፍ ርክክቡ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ለውጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀው ዛሬም ለእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ለአንስቴዥያ ህክምና የሚያስፈልገውን የአንድ ሚሊየን ሁለት መቶ ሽህ ብር ማሽን ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ሆስፒታሉን ዘመናዊ እና ሁሉን አቀፍ ህክምና እንዲሰጥ ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታሉን ለማሻሻል በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ለሆስፒታሉ የሚደረገው ድጋፍ ተማሪዎቻችን በጥራት እንዲማሩ እና ሆስፒታሉም ለህብረተሰቡ መልካም አገልግሎት እንዲሰጥ በማሰብ ነው ብለዋል፡፡
የእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ዜናው አማረ ዩኒቨርሲቲው እና ሆስፒታሉ በተፈራረሙት መግባቢያ ሰነድ ወደ ተግባር መግባቱ ሆስፒታሉ በ2015 ዓ.ም ለሚሰራቸው ሥራዎች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተናግረው ዩኒቨርሲቲው ለህክምና አገልግሎት የሚሆን የአኔስቴዥያ ማሽን ድጋፍ ስላደረገላቸው አመሰግነዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አብርሃም አማረ አሁን ላይ የሆስፒታሉን ዕቃዎች የምንጠቀማቸው በጋራ ስለሆነ ሆስፒታሉን ምቹ የማስተማሪያና ለህብረተሰቡ የዘመነ አገልግሎት የሚሰጥ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
1.6K views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 19:10:44
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአዋሽ ባንክ እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር የመግባቢያ ስምምነት አደረገ፡፡
--------------------
ሐምሌ 28/2014 ዓ.ም፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት ሰራተኞችን የብድር ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ከአዋሽ ባንክ ጋር ተፈራርሟል፡፡
ከአዋሽ ባንክ ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት ሠራተኞች የቤት መስሪያ እና መግዣ፣ የቤት መኪና መግዣ እና የፍጆታ ብድር ለማመቻቸት የሚያስችል መሆኑን የአዋሽ ባንክ የባህርዳር ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ መሰረት አምበሉ ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከአዋሽ ባንክ ጋር የተደረገው ስምምነት የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች የብድር ተጠቃሚ በማድረግ ኑሯቸውን የሚያሻሽሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት ምቹ የሥራ ከባቢን መፍጠር መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ስምምነቱ ሰራተኞችን ለማቆየት እና ለመሳብ ትርጉም እንደሚኖረው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
በተጨማሪም በዛሬው ዕለት በግብርና ምርት እና ምርታማነት፣ በደን እና አካባቢ ጥበቃ፣ በትምህርት ዘርፍ ልማት፣ ምርምር እና ስልጠና ላይ ያተኮሩ አገር በቀል እና ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር የተደረጉ ስምምነቶች ይፋ ተደርገዋል
1) በቻይና ሀገር Changsha Jiarong) Agricultural science and Technology ተቋም 2) መሰረታቸውን በካናዳ እና በአሜሪካ ያደረጉ WE Forest the Hunger Project የተሰኙ ድርጅቶች
3) መሰረቱን ካናዳ ያደረገ Partners in Education Ethiopia “Partners” የተሰኘ ድርጅት
4) Ethiopian Commodity Exchange እና
5) ሳንኪታ ልደታ ተፋሰስን ለማልማት ያለመ ከአዊ ብ/ዞን ግብርና መምሪያ ጋር ስምምነት ተደርጓል
821 views16:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ