Get Mystery Box with random crypto!

Injibara University

የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University I
የቴሌግራም ቻናል አርማ injiuniversity — Injibara University
የሰርጥ አድራሻ: @injiuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.73K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-12-20 06:26:30

1.1K views03:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 06:26:00

1.1K views03:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 06:30:04
1.8K views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 06:30:04
‘‘የትምህርት ዘርፍ ተግዳሮቶች እና መውጫ መንገዶች'‘ በሚል መሪ ሀሳብ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የውይይት መድረክ ተካሄደ።
የውይይት መድረኩን በእንኳን ደህና መጣችሁ ያስጀመሩት የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ሲሆኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንግዳ ዳኛው ደግሞ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡ የመድረኩ ዓላማ በትምህርት ስርዓታችን የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች እና መውጫ መንገዶችን ለማመመላክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በባህርዳር ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ፕ/ር አቢይ ይግዛው ቁልፍ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ዓለምን ለመለወጥ ብቸኛው መንገድ ዕውቀት መሆኑን ጠቅሰው ሀገርን በሁሉም ዘርፍ ለማሳደግ የትምህርት ስርዓታችንን ማሻሻል ይገባል ብለዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በሚቀጥሉት አምስት እና አስር ዓመታት ስትራቴጅክ ዕቅድ አዘጋጅቶ እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው ከለያቸው የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ የትምህርት ጥራት፣ ፍትሃዊነት እና አግባብነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው የትምህርትና እና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ የቀጣይ ስምንት ዓመት የምርምር እና የማህበረሰብ አግልግሎት እቅድ በኮሌጁ ዲን በዶ/ር ዓለም አምሳሉ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል እቅዱም በትምህርት ዘርፍ የሚታዩ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት በቁርጠኝነት መዘጋጅቱን በግልጽ አሳይቷል።
በውይይት መድረኩ የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ አመራሮች እና የትምህርት እና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ መምህራን፣ የብሄረሰብ አስተዳደሩ የወረዳ አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የትምህርት ዘርፍ አመራሮች እና የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት እና ስነ-ህሪ ኮሌጅ ዲኖች ተገኝተዋል።
ህዳር 6/2015 ዓ.ም
1.8K views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 19:03:42

1.6K views16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 09:09:56
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
2.0K views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 20:51:47
2.3K views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 20:10:11
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዋሸራ (ዳንግሌ) በግ ዝርያ ማሻሻል ላይ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በዛሬው እለት የመስክ ጉብኝት እና በአመት ሁለቴ ከዝናብ መውጫና መግቢያ ጋር ተያይዞ የሚሰጠውን የውስጥ ጥገኛ በሽታን የማከም አገልግሎትም ተሰጥቷል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዝርያው እየጠፋ የነበረውን የዋሸራ (ዳንግሌ) በግ ለመታደግ ICARDA ከሰተኘ ድርጅት ጋር በመሆን በፋግታ ለኮማ ወረዳ በዝምብሪ መስክ ዙሪያ ባሉ 4 መንደሮች 622 አባውራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማህበረሰብ ዓቀፍ ዝርያ ማሻሻል ፕሮጀክት ቀርጾ በመስራቱ አበረታች ለውጦች መታየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በማህበር ለተደራጁ የአካባቢው ማህበረሰቦች 114 አውራ በጎች መሠራጨታቸውንም ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር እና የእንስሳት ህክምና መምህር የሆኑት ዶ/ር መልካም ፕሮጀክቱ ሥራ ከጀመረበት ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ነጻ የበጎች የውስጥ ጥገኛ ህክምና እንደሚሰጥ ተናግረዋል። አርሶ አደሮቹ የእንስሳት መኖ እንዲያለሙ ሰርቶ ማሳያዎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ ይህንን ፕሮጀክት በሌሎች ወረዳዎችም ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የዋሸራ (ዳንግሌ) በግ የማህበረሰብ አቀፍ ዝርያ ማሻሻል ፕሮጀከት አስተባበሪ የሆኑት መምህር መልካም ጸጋ የዋሸራ በግ ዝርያ ከሌሎች የበግ ዝርያዎች የሚለዩት በሶስት ወር ለገበያ የሚደርሱ እና ከአንድ አስከ አራት በጎችን በአንዴ የሚወልዱ መሆናቸው ተናግረዋል፡፡
መርጌታ ስለሺ መንበሩ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሚሰጠው ህክምና እና የአውራ በጎች ስርጭት ጥሩ ዝርያ ያላቸውንማርባት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው ዩኒቨርሲቲውን አመስግነዋል፡፡
ታህሳስ 2/2015 ዓ.ም
1.1K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 14:43:52
ማስታወቂያ
//////////////////
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በሙሉ፦
2.3K views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 20:19:48
መሰረታዊ የአመራርነት ጥበብ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ፡፡
///////////////
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መካከለኛና መሠረታዊ አመራሮች የተሰጠው ስልጠና በዋናነት ስራ አመራር ላይ ያተኮረና የመካከለኛ አመራሩን የመምራት አቅም ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) የሥልጠናውን መርሐ ግብር በይፋ ሲያስጀምሩ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች የተሻለ ግንዛቤና ልምድ እንዲወስዱ በማሰብ የካበተ ልምድ ያላቸውን አሠልጣኞች በመጋበዝ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቅሰው ከስልጠናው በኋላ የአመራርነት ክህሎቱን በማሻሻል የሚሠራበትን ኃላፊነት ውጤታማ የሚያደርግ ግብዓት እንደሚገኝ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ሰው ኃብት ስራ አመራርና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሀብታሙ ጥላሁን ስልጠናው መከካለኛ እና መሠረታዊ አመራሮች የመምራት አቅማቸውን ለማሳደግ እና ለማሻሻል ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰው ለ120 የዩኒቨርሲቲው አመራሮች መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡

ስትራቴጂያዊ አስተሳሰብ፣ የውሳኔ አሳጣጥና የችግር አፈታት፣ የአስተሳሰብ ውቅር፣ የተቋማዊ ስነ ምግባር ሥራ አመራር፣ የጊዜ አጠቃቀም ጥበብ፣ የለውጥ አመራር፣ የሥራ አመራር ተግባቦት፣ ሁለንተናዊ ለውጥ እና የቡድን ሥራ የሚሉ ጉዳዮች በስልጠናው ተዳሰዋል።

ስልጠናውን የሰጡት የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና በሥራ አመራር ሥልጠና የካበተ ልምድ ያላቸው ዶ/ር ተመስገን ዳኘ እና ኢትዮጵያ ሲቪል ስርቪስ እና የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ መምህር የነበሩት የማኔጅመንት አማካሪ ዶ/ር ዮሴፍ ውባለም ናቸው።

ስልጠናው ለተከታታይ ሦስት ቀን የተሰጠ ሲሆን በዛሬው እለት ተጠናቋል።

ህዳር 25/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
1.2K views17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ