Get Mystery Box with random crypto!

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የሰርጥ አድራሻ: @ibnumunewor
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 76.49K
የሰርጥ መግለጫ

كناشة ابن منور

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-25 09:25:52 ሶላት የተወ ሰው የሚኖረውን ብይን (ሑክም) በተመለከተ ከጥንት ጀምሮ በዑለማእ መካከል የሃሳብ ልዩነት አለ።
1፦ ከፊሎቹ ከኢስላም ይወጣል ሲሉ
2፦ ሌሎቹ ደግሞ ወንጀለኛ ቢሆንም ከኢስላም አይወጣም ብለዋል።
በሁለቱም አቋሞች በኩል ታላላቅ ዑለማኦች አሉ። አቅሙ ያለው ሰው መረጃዎቹን ፈትሾና አበጥሮ ከሁለቱ አቋሞች ውስጥ ሚዛን የሚደፋውን መውሰድ ይጠበቅበታል። ከዚህ አልፎ ጉዳዩን በሌላኛው በኩል ያሉትን ዓሊሞች በቢድዐ ለመወንጀል ማዋል ግን ተገቢ አይደለም። ይሁን እንጂ አንዳንዶች "ሶላት የተወ ሰው ከኢስላም አይወጣም" የሚሉ ዓሊሞችን በኢርጃእ ሲወነጅሉ ይታያሉ። ይሄ የተሳሳተ አካሄድ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
12.6K viewsedited  06:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 07:01:01 በተለይ ወደ ዳዕዋ የቀረባችሁ ወንድሞች ክፉ ምሳሌ እንዳትሆኑ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁላሀ

        t.me/Darutewhide
14.1K views04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 14:42:02 “ጥንብ ነችና ተዋት!”
~
ዘረኝነት በነብዩ ﷺ አንደበት “ጥንብ” እንደሆነ ተገልጿል። ጥንብ ላይ የሚያንዣብበው ጥንብ አንሳ ነው! ሰው ሁን። ከጥንብ ራቅ። በተቅዋ ከፍ በል። “ከናተ በላጫችሁ ይበልጥ አላህን የሚፈራው ነው” ብሎናል ጌታችን። [ሑጁራት፡ 13] ሐበሻው፣ ጥቁሩ፣ ባሪያው ቢላል፤ ከዐረቡ፣ ከቁረይሺዩ፣ ከነብዩ ﷺ አጎት አቡ ለሀብ የበለጠው በተቀዋው እንጂ በምንም አልነበረም። ሞኝ አትሁን። ከእምነትህ ዘርህን አታስቀድም። አታይምንዴ አላህ ዐረቡን፣ ቁረይሺዩን፣ የነብዩን ﷺ አጎት አቡ ለሀብን ከሀበሻው ጥቁር ባሪያ በታች ሲያደርገው?! መቼም አቡ ለሀብን የሚያወግዝ አንድ የቁርኣን ምእራፍ እንደወረደ የምትዘነጋው አይመስለኝም። ቢላል ግን በኢማኑ ስንቶች የሚቋምጡበትን ማእረግ ነው የታደለው። የነብዩ ﷺ ቅርብ ሰው ነበር። የነብዩ ﷺ ሙአዚን መሆን ምንኛ መታደል ነው?! እርግጠኛ ነኝ ዛሬም ድረስ ቢላል በሙስሊሞች ልቦና ውስጥ ያለው ቦታ ታላቅ እንደሆነ እስክነግርህ አትጠብቀኝም።
የትኛውንም ቋንቋ ስለተናገርክ ከማንም በላይ አይደለህም። ከየትኛውም ብሄር ስለመጣህም ከማንም በታች አይደለህም። ከሁሉ በፊት አንተ ለራስህ ትክክለኛ ቦታህን ስጥ። ሰዎች ስለሰቀሉህ አትሰቀልም። ሰዎች ስላወረዱህም አትወርድም። ለሆሳሱ ሁሉ ስላንተ እየመሰለህ አትሳቀቅ። ለቃላት መጥፎ ትርጉም እየሰጠህ አትሸማቀቅ። በትንሽ በትልቁ ውስጥህ አይደፍርስ። ጥቂት ከጠረጠርክ ሸይጧን ብዙ ያመሳስልብሃል። በዘሩ ሊኮፈስብህም የሚሻ ካለ፣ በማንነትህ ሊንቅህ ከዳዳው በተቅዋ ብለጠው። እሱ ጥንብ ቢያነሳ አንተም ጥንብ ታነሳለህንዴ?!
ሀላፊነት ይሰማህ። ቂል የዘረኝነት እሳት ሲያቀጣጥል አንተ ጋዝ አታርከፍክፍ። ቂል ትከተላለህንዴ? የአረሕማን ባሪያዎች ማለት ቂሎች በቂልኛ ሲያናግሯቸው በነገር ሲተነኩሷቸው ነገር እንዲበርድ የሚያደርጉ፣ ሠላም እንዲሰፍን የሚጥሩ ናቸው። ታዲያ አንተ የማን ባሪያ ነህና?! እርግጠኛ ነኝ “የሸይጧን ነኝ” አትለኝም! የዘረኛ ዘረኝነት ዘረኛ አያድርግህ። የጥንብ አንሳው ጥንብ ማንሳት ጥንብ እንደማያስነሳህ ሁሉ። ሞኝ አትሁን! የሱ ዘረኝነት ላንተ ይቅርታ አይሆንም፡፡ እሱን ሸይጧን ቢጋልበው አንተም ጀርባህን ትሰጣለህ እንዴ? ግን የሸይጧን ፈረስ የሆነ ሰው ምንኛ አስቀያሚ ነው?!
እናም እልሃለሁ ዘረኛው በቆሻሻ ዘረኝነት ውስጥ ሲዋኝ ብታየው ከቻልክ “አላህን ፍራ” በለው። በጥንብ እየተጨማለቀ እንደሆነም አስረዳው። ካልሆነልህ እሱ የያዘውን ጥንብ ለመንጠቅ እንዳትሞክር፤ ወይም ጥንብ ላይ እንዳትሻማ። ዘረኝነትን በዘረኝነት እንዳትመልስ ማለቴ ነው። ሸይጧን ከፊት ሲስብህ፣ ከኋላም ሲገፋህ ዝም ብለህ አትነዳ። “አላህን ፍራ” ማለት ካቃተህ አላህን መፍራት ግን አያቅትህ። ሂሳብ ስራ። ፈሪ ሁን! አዎ! አንድየውን፣ ሁሉን አዋቂ፣ ሁሉን ተመልካች፣ የፍርዱ ቀን ዳኛ… የሆነውን ጌታ የምትፈራ ሁን። አስተውል! “ፈሪ” እባላለሁ ብለህ አትጨነቅ። የፈራሀው አላህን እንጂ ሰው አይደለም! ቀድሞ ነገር አላህን እንደሚፈራ ሰው ጀግና አለና ወይ? በጭራሽ! ነብዩስ ﷺ “ጀግና ማለት በንዴት ጊዜ ቁጣውን የሚቆጣጠር ነው” አላሉምንዴ? ታዲያ ትእዛዛቸውን እናክብራ! ወዳጅ ያምፃልንዴ?!
የሌላውን ብሄር፣ ቋንቋ፣… ከማንቋሸሽ ራቅ። በሌላው ብሄር ላይ ከመሳለቅ ከመቀለድ ተጠንቀቅ። በሌላው ላይ ሲቀለድም አትሳቅ። ለራስህ የማትወደውን ነገር በሌላው ላይ አታድርግ። ይሄ ብዙዎቻችን የተለከፍንበት ገዳይ በሽታ ነው አላህ የጠበቀው ሲቀር። ምናልባት አንተ ስለራስህ ደንታ ቢስ ሆነህ ሊሆን ይችላል። ግን ሁሉ እንዳንተ እንዳልሆነ አትርሳ።
አትጠራጠር! ዘረኝነት የጃሂሊያ ስራ የመሀይሞች መታወቂያ እንደሆነ ታማኙ የአላህ መልእተኛ ነግረውሃል። ልብ በል! በምትናገረው ቋንቋ ከማንም በታች እንዳልሆንክ ሁሉ ከማንም በላይም አይደለህም! ከፍም ዝቅም የሚያደርግህ ስራህ እንጂ ዘርህ አይደለም። “ስራው ያስቀረውን ዘሩ አያስቀድመውም!” አይደል ያሉን ነብያችን ﷺ? ነብዩኮ ልጃቸው እንኳ “የነብይ ልጅ ነኝ” ብላ እንዳትሸወድ ይልቁንም በርትታ ሰርታ እራሷን እንድታተርፍ ነው አደራ ያሏት። ከፍ ማለት ከፈለግክ በኢስላም ከፍ በል፣ በተውሒድ ከፍ በል፣ በሱና ከፍ በል። ከዚህ በራቅክ ቁጥር እየወረደክ፣ እየዘቀጥክ፣ ቁልቁል እየተምዘገዝግክ እንደሆነ ነጋሪ እስኪነግርህ አትጠብቅ።
ጥሪየ ማንነትህን እንድትጥል፣ ማንም በመታወቂያህ ሲረማመድ ዝም እንድትል አይደለም። ይልቁንም ጥሪየ አላህን እንድትፈራ ሚዛንህ እንድትጠብቅ ብቻ ነው። እናም የራስህን አስጠብቅ፣ ከሌሎች አትድረስ። ዘርህን ከእምነትህ ያስቀደምክ እለት ግን አትጠራጠር ታመሃል፡፡ እንዲህ እየገዘገዘህ ህመሙ ካልተሰማህማ ጭራሽ ቫይረሱ አናትህ ላይ ወጥቷል፡፡ ጓደኛህ ይህን ህመምህን እያየ፣ ጥምብ ስታጨማልቅ እየተመለከተህ ዝም ካለህ፤ ወይ እንደ ተናካሽ ውሻ ያገኘኸውን ስለምትነክስ ፈርቶሃል፣ ወይ ደግሞ እሱም እንዳንተው ጥንብ አንሳ ነው ማለት ነው!
አደራ ግን እኔ ይሄን ሁሉ ስለቀልቅ ከችግሩ ነፃ ነኝ እያልኩ አይደለም፡፡ እኔ ቀርቶ ስንት ታላላቆች የሚወድቁበት ችግር እኮ ነው፡፡ ቀድሞ ነገር ታላቅ ሰው ማለት ፍፁም የማይሳሳት ነውንዴ? ከስህተቱ የሚመለስ ነው እንጂ!!! እናም ቫይረሱ ጋር ላለመድረስ ስንሳሳትም ለመመለስ እንጣር፡፡ እንዲህም እንበል፡ “አላሁመ ኣቲ ነፍሲ ተቅዋሃ፣ ወዘኪሃ አንተ ኸይሩ መን ዘካሃ፣ አንተ ወሊዩሃ ወመውላሃ!” “ጌታዬ ሆይ አንተ ለነፍሴ ተቅዋዋን ስጣት፡፡ አጥራትም፤ አንተ ከሚያጠራት ሁሉ በላጭ ነህና፡፡ አንተ ረዳቷም ተንከባካቢዋም ነህ”
=
ኢብኑ ሙነወር
(ሚያዚያ 15/2009)
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
18.5K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 12:57:33 “ከፈተናዎች መውጫ”
ክፍል - 1
ሚያዚያ 14/2016 ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀረበ
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
12.6K views09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 10:28:43 “ከፈተናዎች መውጫ”
ክፍል - 2
ሚያዚያ 14/2016 ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀረበ
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
12.9K viewsedited  07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 09:56:07 የወለጋ ካርድ
~
የወለጋ ካርድ ያልኩት በአማራ ፖለቲከኞችና አጋፋሪዎቻቸው ክልሉ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችን የሚያጋልጡ ድምፆችን ለማፈን የሚጠቀሙበትን አፍ ማስያዣ ስልት ነው። እያንዳንዱ ሙስሊሞች ላይ የሚደርስ ጥቃት በተዘገበ ቁጥር "ወለጋ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ሲፈፀም የት ነበራችሁ?" ይላሉ።
* በጎንደር ሙስሊሞች ላይ የደረሰ ጥቃት ሲዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* በባህርዳር ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመ ግድያ ሲወራ ይህንኑ የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
* የሞጣ ግድያ ቢዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* የእንፍራንዝ ደረሶች ግድያ ቢዘገብ የተለመደውን የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ግድያዎች፣ ዝርፊያዎች፣ እገታዎች፣ ማሳደዶች፣ መስጂዶችን ማቃጠል በተዘገቡ ቁጥር ያለ መታከት ይህንኑ ካርድ ይመዛሉ። ሂሳባቸው አጭር ነው። ወለጋ ላይ የደረሰው ጥቃት በቂ ሽፋን ስላልተሰጠው እኛ ስንገድልም፣ ስናፈናቅልም፣ ስናግትም፣ ስንዘርፍም ተቃውሞ ቀርቶ ኮሽታ ሊሰማ አይገባም ነው። እንዲያውም እንደ ተበዳይ ነው የሚተውኑት። "የኛ ማጥቃት ለምንድን ነው የሚራገበው? ደመ መራራ ነን። ነገር ይገንብናል" አይነት ነው ጨዋታው። "አማራ ክልል ኮሽ ሲል ይራገባል" ይላሉ። ያ ሁሉ በጎንደር፣ በደባርቅ፣ በእንፍራንዝ፣ በእስቴ ፣ በቢቸና፣ በሞጣ፣ በባህር ዳር፣ ... የደረሰው መስጂዶችን ማቃጠል፣ የበርካታ ሙስሊም ግድያ፣ እገታ፣ ... ሁሉ ጢኒኒጥ ኮሽታ ብቻ ናት። መስጂድ እንደ ደመራ አንድደው መጨፈራቸው ራሱ እዚህ ግባ የማይባል ተራ ነገር ነው ፣ እንዲሁ ኮሽታ ብቻ። የትኛውም ነገር ይድረስ "አማራ ክልል ውስጥ ኮሽ ሲል... " እያሉ ጥቃቱን ተራ ኮሽታ አድርገው ነው የሚገልፁት። አላህ አናታቸው ኮሽ ያድርገውና።
ከዚያ እኛ ብንበድልም የወለጋው ከኛ ስለሚበልጥ የኛን ብዙም አታስጩሁት ነው የሚሉት። በክልሉ ሙስሊሞች ያነጣጠሩ ጥቃቶች በተዘገቡ ቁጥር ይህንን ካርድ መምዘዝን በቃ ንቃት አድርገውታል። አላማው የተቃውሞ ድምፆችን ማፈን ነው። ሳይወራ፣ ሳይዘገብ መጨረስ። በዚህ አይነት የማንሰማቸው ስንት በደሎች እንደሚኖሩ ማሰብ ይቻላል።
በነዚህ መሰሪዎች ለተሸወዳችሁ ሙስሊሞች ሁሉ! ለመሆኑ በደሉ ምን ሲደርስ ነው "አሁንስ በዛ!" የምትሉት? ነው ወይስ እንዲሁ እያሉ ሁሉንም በየተራ ቢጨርሱም አትነቁም? ለይቶ ማራገብ አለ ካላችሁ የጎደለውን በመሙላት ላይ ስሩ እንጂ በሙስሊም ደም ቁማር ለሚሰራ እባብ ለምን ትወግናላችሁ? የኦሮሚያው ችግር ሽፋን ካላገኘ እናንተ ዘግቡት። "ለምን የኦሮሚያ ሲሆን ...?" የሚላችሁ ሲኖር ነው "ምነው የአማራ ብቻ..." የሚባለው። እንጂ እንዴት በዘር መሰላል ተንጠላጥላችሁ እምነታችሁን ለሚያረክስ፣ ወገኖቻችሁን ለይቶ ለሚያጠቃ አካል ጠበቃ ትሆናላችሁ?! ወላሂ ይሄ የሞኝነት ጥግ ነው።

=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
14.5K views06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 16:17:38 አስተማሪና መሳጭ ታሪክ!
~
በሰዑዲ የሚኖር የመኒ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ያጋጠመውን ታሪክ እንዲህ ይተርከዋል፡፡
ከፊሌ የዘካ ገንዘብ ሊያከፋፍል ፈልጎ ከሱ ጋር ወጣሁ፡፡ የድሃ መንደሮች ወዳሉባቸው ጠረፍ አካባቢ ሄድን፡፡ የዘካው ገንዘቦች በፖስታ የታሸጉ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ፖስታ በውስጡ 5ሺ ሪያል ይዟል፡፡ ከአንዱ መንደር ወጥተን የጂዳ-ጂዛን መስመር ስንይዝ አንድ የ70 አመት አካባቢ ሽማግሌ አገኘን፡፡ ሽማግሌው ብርቱና ጤናማ ነው፡፡ ጎዳናውን ይዞ ይጓዛል፡፡
ወዳጄ፡ “ይሄ ደግሞ በዚህ ሰዓት በዚህ በረሃ ምን ይሰራል?” አለኝ፡፡
ሹፌሩ፡ “ህገ ወጥ የመኒ ነው” አለ፡፡
ካጠገቡ ደርሰን ቆምንና ሰላም አልነው፡፡
* “ከየት ነው ወንድም?”
- “ከየመን”
* “የት ነው የምትሄደው?”
- “የአላህን ቤት ናፍቄያለሁ።”
* “ህጋዊ ነህ?”
- “አይደለሁም”
* “ለምን ህጋዊ አልሆንክም?”
- “ለዋስትና 2ሺ ሪያል ማስያዝ ይጠበቅብኛል፡፡ እኔ ያለኝ 200 ብቻ ነው፡፡ በመቶዋ ተሳፈርኩባት፡፡ የቀረኝ መቶ ብቻ ነው” አለ፡፡
* “እሺ አጎቴ! በጉዞ ላይ ምን ያክል ሆነህ?” አለው ጓደኛየ፡፡
- “ስድስት ቀን!”
* “እየፆምክ አይደለም ኣ?”
- “አይ ፆመኛ ነኝ፡፡”
* “ጥሩ፡፡ አንተ ከ 5 በላይ የፍተሸ ኬላዎችን አልፈሃል፡፡ እንዴት ነበር የምታልፋቸው?”
- “ከሱ በስተቀር እውነተኛ አምላክ በሌለው አላህ እምላለሁ! የማልፈው በነሱው ዘንድ ነው፡፡ ግን አንድም ያናገረኝ የለም!”
* “ለስራ ነው አመጣጥህ?”
- “በጭራሽ ወላሂ! እኔ የአላህን ቤት ናፍቄ ነው የመጣሁት፡፡ ዑምራ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡ ወደ መካ ነው የምጓዘው፡፡”
* “በአስፋልት ላይ ስትጓዝ ተዘዋዋሪ ዘቦች /ፓትሮል/ አልያዙህም?”
- “ከግማሽ ሰዓት በፊት በ 50 ኪ. ሜ. ርቀት ላይ ይዘውኝ ነበር፡፡ እዚህ ከመድረሴ አንድ ኪ. ሜ. ቀደም ብሎ ድረስ እነሱ ናቸው ያመጡኝ፡፡ የት እንደምሄድ ሲጠይቁኝ በአላህ ምየ የአላህን ቤት እንደምፈልግ ስነግራቸው ለቀቁኝ።”
* “ሱብሓነላህ! ጭራሽ እስከዚህ ቦታ በፍጥነት እንዲያደርሱህ አላህ ፓትሮሎችን አመቻቸልህ” አልኩኝ በውስጤ፡፡
- ወዳጄ ሁለት ፖስታዎችን እየሰጠው “እነዚህን ያዝ፡፡ ዘካ ነው” አለው፡፡
* እየተቀበለ “ጀዛኩሙላህ ኸይር” አለ፡፡
በፖስታዎቹ ያለው ገንዘብ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ አያውቅም፡፡
* “የሰዑዲን ብር ታውቃለህ?” አልኩት፡፡
- “አዎ!” አለ፡፡
* “ጥሩ፡፡ ፖስታውን ክፈትና እንዳይጠፋብህ ገንዘቡን በቀበቶህ (በሒዛምህ) ውስጥ ደብቅ” አልኩት፡፡
ሲከፍተው 10 ሺህ ሪያል!!
- “ይህ ሁሉ ለኔ ነው?” አለ፡፡
* “አዎ ላንተ ነው” አልነው፡፡
ከመኪናው ላይ ወደቀ፡፡ ራሱን ሳተ፡፡ ከመኪናው ወርደን በላዩ ላይ ውሃ መርጨት ያዝን፡፡
- “ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው? ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው?” እያለ መጮህ ያዘ፡፡ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ቀጠለ፡፡
* ባልደረባዬ፡ “ከኛ ጋር ትንሽ ወደ ፊት እንውሰደው” አለ፡፡
ከኛ ጋር መኪና ላይ ወጣ፡፡ ትንሽ ሲረጋጋ ጠየቅኩት፡
* “ምንድን ነው ይህ ሁሉ ለቅሶ?” አልኩት፡፡
- “እኔ የመን ውስጥ ከቤቴ ጎን ቦታ አለችኝ፡፡ ለአላህ ሰጥቻታለሁ፡፡ እኔና ቤተሰቦቼ በሷ ላይ በጭቃና በድንጋይ አድርገን መስጅድ ገንብተንባታል፡፡ ግንባታው ቢጠናቀቅም ምንጣፍና ጥቂት ነገሮች ቀርተውት ነበር፡፡ ለዚህ መስጂድ እንዴት ምንጣፍ እንደማገኝ ተቀምጬ አስብ ነበር” አለ፡፡
ይህን ሲል የእውነት ሁላችንም አለቀስን፡፡ “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው ዱንያ እንዳለች ትመጣለታለች” የሚለውና “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው አላህ መብቃቃቱን ከልቡ ውስጥ ያደርግለታል፡፡ ነገሩንም ይሰበስብለታል፡፡ ዱንያ በግዷ ወደሱ ትመጣለች፡፡ አሳቡ ዱንያ የሆነ ደግሞ አላህ ድህነቱን በአይኖቹ መሀል ያደርግበታል፡፡ ነገሩንም ይበትንበታል፡፡ ከዱንያም የተወሰነለት ብቻ እንጂ አይመጣለትም” የሚለው የነብዩ ﷺ ንግግር ትዝ አለኝ፡፡
በዚህን ጊዜ ወዳጄን ለሰውየው እንዲጨምረው ጠየቅኩት፡፡ ተጨማሪ 2 እሽግ ፖስታ ሰጠው፡፡ በድምሩ 20 ሺ ሪያል አገኘ ሰውየው፡፡ ሰውየው ከመኪናው ከመውረዱ በፊት እያለቀሰ ያጉተመትምና ዱዓ ያደርግ ነበር፡፡
* “በአላህ ላይ እውነተኛ የሆነውን መመካት ብትመኩ ኖሮ ልክ ወፍን እንደሚረዝቀው ይረዝቃችሁ ነበር፡፡ ተርባ ወጥታ ጠግባ ትመለሳለች” የሚለው የነብዩ ﷺ ሐዲሥ መጣብኝ፡፡
የተተረጎመ
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 25/2010)

የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
16.3K viewsedited  13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 09:20:14 እራሳችንን እንዴት ነው የምናየው?
~
ኢብኑ ዑመር ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፦
"ተቅዋ ማለት እራስህን ከማንም በላይ እንደሆንክ አድርገህ ላታይ ነው።"
ተፍሲሩል በገዊ: 1/60
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
14.2K views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 20:33:48 ለመርከዘ ተውሒድ ተማሪዎች!
~
የመጨረሻ መግቢያ ጊዜ ነገ ሸዋል 9 ነው። ከሸዋል 12 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን የምንቀበል ይሆናል፤ ኢንሻአላህ።
14.5K views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 13:41:27
የ አፋልጉን ማስታወቂያ

በምስሉ ምትመለከቱት ልጅ አብድልከሪም መሀመድ ሁሴን ይባላል የትውልድ ቦታ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ልዩ ስሙ ትልሞን ይባላል
እድሜው 16አመት ነው ከቤት ከወጣ 1አመት ሆኖታል ይገኝበታል ባልነው ቦታ ሁሉ ፈልገናል ነገ ዛሬ ይመጣል እያልን ስንጠብቅ እስካሁን ግን ምንም ፍንጭ አላገኝንም እባካችሁ እናንተ ኢትዮጵያዊያን ሆይ ተባበሩን እኛ ቤተሰቦቹ በጭቀት ላይነን በተለይ እናቱ በከባድ ሁኔታ ላይ ናት ... ተባበሩን

አብድልከሪም ያለበት ለጠቆመን ወይም ላገናኝን ወረታውን እንከፋላለን ማንኛውም ጥቆማ ያላችሁ ወይም ያለበትን የምታወቁ

በስልክ ቁጥር 09 0452 57 52 ሙባረክ መሀመድ

09 13 54 96 65 ህያር ሰማን

በነዚህ ስልኮች ጠቁሙን
13.6K views10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ