Get Mystery Box with random crypto!

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የሰርጥ አድራሻ: @ibnumunewor
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 77.07K
የሰርጥ መግለጫ

كناشة ابن منور

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-05-01 10:09:57 ሰው መሳይ በሸንጎ
~
ዑለማኦች ከሰውነት አጥር ውጭ አይደሉም። የሰው ልጅ ላይ የሚታዩ ድክመቶች ይታዩባቸዋል። ከዒልምና ከተቅዋ አንፃር በአመዛኙ ከሌሎች ስለሚሻሉ የተሻለ ነገር እንጠብቃለን። ይሁን እንጂ "የኣደም ልጅ ሁሉ በጣም ተሳሳች ነው" ከሚለው እውነታ ውጭ እንዳልሆኑ መዘንጋት አይገባም። ስለሆነም፡
* አንዳንዴ ስሜታዊነት፣ ምቀኝነት፣ ጥቅመኝነት፣ ዝናን መሻት፣ አጉል ተጠራጣሪነት፣ ... የመሳሰሉ መጥፎ ባህሪዎች ሊፀናወቷቸው ይችላሉ።
* ወይም ተቆርቋሪና ታማኝ የመሰለ የቅርብ ሰው የሚያሳስታቸው ሊኖሩም ይችላሉ።
በነዚህ ወይም በሌላ ምክንያቶች አንዱ ዓሊም ሌላው ላይ ከባድ ቃል ሊናገር ይችላል። ይሄ በአየር ላይ ያለ ምናብ ሳይሆን ተጨባጭ ምሳሌዎች ሊጠቀሱበት የሚችል እውነታ ነው።

ይህንን ከተረዳን አንድ ዓሊም በሌላው ዓሊም ላይ ከባድ ትችት ቢሰነዝር ሳያጣሩ ከማራገብ በፊት ጉዳዩን ቆም ብሎ ማጤን ይገባል።
* ሌሎች ዓሊሞች ምን ይላሉ? ጉዳዩን ከማወቃቸው ጋር የተለየ ትንታኔ ሰጥተዋል? ተማሪዎች በጉዳዩ ላይ አርፈው እንዲቀመጡ አሳስበዋል? ዝምታን መርጠው ከሆነም ለነሱ የበቃ ዝምታ ለኛም ሊበቃን ይገባል።
* ጉዳዩ በልኩ ተይዞ ይሆን? ወይስ ድንበር ባለፈ መልኩ ነው የተያዘው?
* የትችቱ መነሻ ምንድነው? አሉባልታ ላይ ወይስ ተጨባጭ መረጃ ላይ የተመረኮዘ ነው?
* ተወንጃዩ አካል ምን ይላል? እንደተዋሸበት ይናገር ይሆን? ንግግሩ ተቆልምሞ ሌላ ትርጉም ተሰጥቶበት ይሆን? እየተከሰሰ ያለው ከጥፋቱ ከተመለሰ በኋላ ይሆን?
ይሄ ትችቱ በዑለማኦች የተሰነዘረ ከሆነ ነው። ካልሆነስ?
* ሲጀመር ተቺዎቹ እነማን ናቸው? አንዳንዶቹ እዚህ ግባ የማይባሉ ከንቱ ፍጥረቶች ናቸው ከተራራ የገዘፉ ዓሊሞች ላይ አንጋጠው የሚተፉት። የሆነ ጊዜ አንዱ ጎረምሳ ዐብዱልሙሕሲን አልዐባድን ሲዘረጥጥ ነበር። በአደብ ቢያርርም ምንም አልነበረም። "ሁሉም አራሚና ታራሚ ነውና።" ነገሩ ግን እንደዚያ አልነበረም ያደረገው። ሸይኽ ዐብዱልሙሕሲን የሱን ብጤ ቀርቶ እሱ የሚያጣቅሳቸውን ሸይኾች ያስተማሩ የሸይኾቹ ሸይኽ ናቸው። እሱ በገለፀበት መልኩ ሸይኾቹ እንኳ አይደፍሯቸውም። ታላላቆቹ በሚያፍሯቸው ታላቅ ሸይኽ ላይ ሲዳፈር ማየት ያሳቅቃል።
ይህን እንድፅፍ ያደረገኝ ሸይኽ ፈላሕ ሙንደካርን፣ ሸይኽ ሷሊሕ አሱሐይሚን፣ ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድርን የሚያብጠለጥሉ አካላትን አይቼ ነው። በቃ ብልግና ጀብድ ሆነ። ለሆነ ሸይኽ ቅርብ ስለሆኑ ወይም ከሆነ አካል ተዝኪያ ስላላቸው ራሳቸውን አይነኬ የሚያደርጉ አንዳንድ "ከተዘሩ ያልታረሙ" ዋልጌዎች አሉ። ለእንዲህ አይነቶቹ ሙጅሪሞች ቦታ መስጠት ራስን ማርከስ ነው። ምግባሩ ያቆሸሸውን የማንም ተዝኪያ አያፀዳውም። አላሁል ሙስተዓን!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
16.1K viewsedited  07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 07:28:31
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
12.6K viewsedited  04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 06:50:44 "ጨረቃ ዳቦ ጣይልኝ፣ ኮከቢት ተቀበይልኝ"
~
የልጅ አእምሮ ነጭ ወረቀት ማለት ነው። እኛ ዋዛ የሚመስሉንን ብዙ ነገሮች እንደ ቁምነገር ይይዛል። በልጅነቱ የሰው ጅብ ወይም ጭራቅ የሚባል አለ ብለው ስለነገሩት ካደገ በኋላም እንዲህ የሚባል ነገር አለ ብሎ የሚያምን ብዙ ሰው አለ። በርግጥ ከእድገት ጋር የሚቀየሩ ነገሮች አሉ። ቢሆንም ኋላ ተቀየረም አልተቀየረም ለህፃናት ያልሆነ ነገር እየነገርን አእምሯቸው ውስጥ የተዛባ ነገር እንዳንተክል መጠንቀቅ ይገባል። ከዚህ ጋር የተያያዙ እንደየሃገሩ እንደየባህሉ ብዙ ልማዶች አሉ። ለምሳሌ፦
* ህፃናት ሲጫወቱ "ጨረቃ ዳቦ ጣይልኝ፣ ኮከቢት ተቀበይልኝ" እያሉ መዘመር። ይሄ ሺርክ ነው።
* ጥርሳቸውን ሲጥቅሉ "አይጢቷ! የኔን ወስደሽ ያንቺን ስጪኝ" ብሎ ጣራ ላይ መጣል። ይህም ሺርክ ነው።
* ጆሮ ደግፍ ሲያዛቸው የሰው ቤት በድንጋይ እንዲመቱ መላክ። በዚህም ውስጥ ትንሹ ሺርክ አለ።
* የቀብር አፈር ቤት ላይ መበተን። ልጆች ውጭ ላይ አጥፍተው ሲመጡ ቤተሰብ እንዳይቀጣቸው ሲፈሩ የቀብር አፈር ይዘው በመምጣት ቤት ላይ ይበትናሉ። በቃ ይህን ሲያደርጉ ቤተሰብ ስለዚያ ጉዳይ አይጠይቅም ብለው ያምናሉ። በዚህም ውስጥ ሺርክ አለ።
መስጠት የፈለግኩት ጥቆማ ነው። እነዚህና መሰል ባህሎች ዛሬ ከተማ ውስጥ በብዛት አይኖሩም። ግን አንዳንዴ የማንጠብቀው ነገር ይዘው እናገኛቸዋለን። ስለዚህ ልጆቻችንን በጨዋታም ይሁን በቁም ነገር፣ በእምነትም ይሁን በልማድ መልክ የተዛባ ነገር እንዳይዙ መጠንቀቅ መልካም ነው። አንዳንዱ በጨዋታ መልክ የሚቀርብ ቢሆንም በሺርክ መቀለድ በእሳት መጫወት ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.7K viewsedited  03:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 19:22:05

12.7K views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:24:24 ከፍ በል በኢስላም!
~
አለባበሳችንን፣ አነጋገራችንን፣ የፀጉር ቁርጣችንን፣ የሜካፕ አጠቃቀም፣ የልብስ ምርጫችንን፣ ... ለመወሰን በወቅታዊ ፋሽን መሸነፍ አይገባም። ሸሪዐው ሲያዝ አሻፈረኝ ብለን የዘመኑ ፋሽን ሲሆን የምንንበረከክ ልፍስፍሶች መሆን የለብንም። እኛ በኢስላማዊ እሴቶቻችን ፈፅሞ የማንሸማቀቅ ኩሩዎች እንጂ የተሸነፈ ስነ ልቦና የያዙ ደካሞች ልንሆን አይገባም። ደግሞም ለራሳችንም ዋጋ መስጠት መልካም ነው። አላህ በኢስላም ካከበረን በኋላ፣ 0ቅልን ያክል ኒዕማ ከሰጠን በኋላ ከሰውነት ወለል ወርደን የልብስ መስቀያ፣ የፋሽን ማሳያ አሻንጉሊት ልንሆን አይገባም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
15.6K viewsedited  09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:00:22
ለአስተዋዮች ብቻ!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.6K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 22:20:24 ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:-
* የደርሹ መነሻ፦ صلاة المسافر
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.7K views19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 12:37:11 የኹጥባ አቀራረባችን ምን መምሰል አለበት.?

በኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁላህ

        t.me/Darutewhide
15.5K viewsedited  09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 21:11:05 ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:-
* የደርሹ መነሻ፦ وإذا صلى قائما فصلوا قياما
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
16.9K viewsedited  18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 20:26:17
{ أَفَلَا یَنظُرُونَ إِلَى ٱلۡإِبِلِ كَیۡفَ خُلِقَتۡ }
"ወደ ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?!" [አልጋሺያህ፡ 17]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
16.5K views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ