Get Mystery Box with random crypto!

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የሰርጥ አድራሻ: @ibnumunewor
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 77.25K
የሰርጥ መግለጫ

كناشة ابن منور

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 38

2023-08-30 07:41:36 ሱረቱል ዋቂዐን ስለመቅራት ከመጡ መረጃዎች ውስጥ
~
1ኛ፦ ሱረቱል ዋቂዐን መቅራት ሃብት ለማግኘት እንደሚጠቅም የሚጠቁሙ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ፦

مَن قرَأَ سُورةَ الواقعةِ في لَيلةٍ لم تُصِبْه فاقةٌ
"ሱረቱል ዋቂዐ በሌሊት ውስጥ የቀራ ሰው ድህነት አይነካውም።"
ደካማ ስለሆነ ለመረጃ አይሆንም። ኢማሙ አሕመድ፣ ኢብኑ ዐብዲል ሃዲ፣ ዘይለዒይ፣ ዒራቂይ፣ ኢብኑ ሐጀር፣ ሲዩጢይ እና አልባኒይ ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል።
سورة الواقعة سورة الغنى، فاقرأوها، وعلموها أولادكم
"ሱረቱል ዋቂዐ የሃብት ሱራ ነች። ቅሯት። ልጆቻችሁንም አስተምሯት።"

ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ ዶዒፍ (ደካማ) እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ ቁ.፡ 3880፣ 5668] [ሶሒሑል ጃሚዕ ቁ.፡ 3730]

2ኛ፦ ሱረቱል ዋቂዐን የቀራ ሰው ከዝንጉዎች አይቆጠርም የሚል ሐዲሥም አለ።
ይህንንም ኢብኑ ሐጀር "ሰነዱ በጣም ደካማ ነው" ብለውታል። [ነታኢጁል አፍካር፡ 3/264] ሸውካኒይም "ሰነዱ ውስጥ ውሸታም ሰው አለበት" ብለዋል። [አልፈዋኢዱል መጅሙዐህ፡ 311] አልባኒይም መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ ቁ.፡ 291]

Ibnu Munewor

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
12.6K viewsedited  04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-28 20:31:54 ለፋኖ እና ለደጋፊዎቹ
~
ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የአማራ ክልል ውስጥ በፋኖ እና በመከላከያ መካከል ግጭት እንዳለ ይታወቃል። በቅድሚያ እንዲታወቅልኝ የምፈልገው የምሰነዝረው ሃሳብ ከምታራምዱት ፖለቲካ ጋር የሚያያዝ አይደለም። እናንተን ጨምሮ የየትኛውም ብሄር ፖለቲካ ደጋፊ አይደለሁም። በርግጥ በሃገራችን ተጨባጭ የትኛውም የፖለቲካ ኃይል በህዝብ ስም ይምላል እንጂ ለህዝብ ከመከራና እልቂት ውጭ ያመጣለት የለም ብየ አምናለሁ። ቢሆንም አምስት ዓመት አንቀላፍተው የምርጫ ሰሞን ውር ውር የሚሉትም ይሁኑ ነፍጥ አንግተው የሚፋለሙትም የህዝብን በጎ ፈቃድና ይሁንታ ይዘው አይነሱምና በዚህ ላይ ማውራቱ ትርጉም የለውም።
የኔ ጉዳይ አንድ ነው። እባካችሁ ከሃይማኖታችን ላይ እጃችሁን ሰብስቡ። በየቦታው ሙስሊሞች ላይ የምታደርሱትን ትንኮሳ አቁሙ። በዚህ ቀውጢ ሰዓት ሃይማኖታዊ ትንኮሳዎች ብዙ ቦታዎች ላይ ደርሰዋል። የተገደሉ ሙስሊሞች፣ የተዘረፉ የሙስሊም ንብረቶች በተጨባጭ አሉ። ድብደባ የተፈፀመበት መስጂድ አለ። የተቃጠሉ መስጂዶች ዛሬም አናሰራም ተብለው እንደቀሩ ናቸው። "ሙስሊሞች አብረውን አልተሰለፉም" እያሉ መክሰስ፣ ምንም እንደሌለ እያወቃችሁ "መከላከያን ሰንጋ እያረዱ ተቀብለዋል" እያሉ ማናፈስ አሁንም እምነት ለይቶ የማጥቃት ፍላጎት እንዳለ የሚያሳይ ነው። ሙስሊሙ ምን ስላደረገ ነው "ብልፅግናን ካስወገድን በኋላ እናሳያቸዋለን" እየተባለ የሚዛትበት? "ነባሩ እስልምናና ወሃብያ" እያሉ በማያገባችሁ ውስጥ ማቡካቱንስ ምን አመጣው? አሁን ይሄ ለትግላችሁ ይጠቅማል? ጠላት ማብዛት የፖለቲካ ኪሳራ እንጂ ትርፍ ያስገኛልን? ምናልባት ከውስጣችሁ እንዲህ አይነቱን ነውረኛ ተግባር የማይቀበል ይኖር ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ካላችሁ ታዲያ ለምንድነው እንዲህ አይነቱን አዝማሚያ ባደባባይ የማትኮንኑት?
እዚህ ጋር ማንም ለማስተባበል እንዲመጣ አልፈልግም። መሬት ላይ ያለ እውነት በማህበራዊ ሚዲያ ማስተባበል አይሸፈንም። በተጨባጭ የሚታወቅ እንጂ አሉባልታ አላወራሁም። "አማራ ክልል ኮሽ ሲል ጩኸቱ ይለያል" የሚለው የግፍ ንፅፅር ከፊሉን አሸማቆ ሰሞንኛ እፎይታ ያስገኝ ይሆናል። ግን እስከመቼ? "ወለጋ ላይ ስትጨፈጨፉ ዝም ብላችሁ እኛ ስናጠቃችሁ ለምን ትጮሃላችሁ?" ይባላል እንዴ? "ሸገር ላይ መስጂዶች ሲፈርሱ ዝም ስላላችሁ እኛ ስናፈርስም ዝም በሉ!" ይባላል ወይ? ይህን ነው የምትፈልጉት? ለማንኛውም እኛ ብሽሽቅ አይደለም የምንፈልገው። "እባካችሁ አትንኩን" የሚሉ ድምፆችን ሁሉ በሙስሊሞች ደምና በደል ፖለቲካ ከሚሸቅጡት ጋር እየለጠፋችሁ አፍ ለማስያዝ አትሞክሩ። ፖለቲካችሁን ከይስሙላ ባለፈ ከሃይማኖት ፅንፈኝነት በተግባር ለዩ። አልደረስንባችሁም አትድረሱብን።

Ibnu Munewor

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
15.3K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-27 21:37:55 የአሽዐሪያ ፅንፈኝነት፣ ፈኽሩ ራዚ እንደ ናሙና
~
ፈኽሩ ራዚ (606 ሂ.)፦ የኢብኑ ኹዘይማን ኪታቡ ተውሒድ “በእውነት እርሱ የሺርክ መፅሀፍ ነው” ይላል። [ተፍሲሩ ራዚ፡ 27/582] የሚገርመው የሰለፎችን ዐቂዳ የሚያፀናውን ኪታብ በዚህ መልኩ በሺርክ የሚወነጅለው ራዚ “السر المكتوم في مخاطبة النجوم” የተሰኘ ወደ ከዋክብት አምልኮና ወደ ድግምት የሚጣራ ኪታብ የፃፈ መሆኑ ነው። በዚህ እጅግ ሰቅጣጭ ኪታብ የተደናገጡ አድራቂዎቹ “ይሄ ኪታብ የሱ ስራ አይደለም” ብለው በከንቱ ሊሟገቱ ሞክረው ነበር። ግና ራሱ ራዚ “መጧሊቡል ዓሊያ” በተሰኘው ኪታቡ ላይ የዚህን የድግምት ኪታብ ስምና የራሱ መሆኑን ጠቅሶት መገኘቱና ወደዚህ ሺርክ መጣራቱ ለመከላከል እንዳይመች አድርጎታል። [ገፅ፡ 199፣ 200፣ 210፣ 216፣ 219-222] ይሄ ግልፅ የሆነ ከኢስላም መውጣት ነው። ያለው ቀዳዳ “ምናልባት ሳይቶብት አይቀርም” የሚለው የአንዳንዶች ግምት ነው።
በሚገርም ሁኔታ ራዚ ወደ ቀብር አምልኮ ሲጣራ የአርስቶትል ባልደረቦች የሆነ ጥናት በከበዳቸው ቁጥር ወደ ቀብሩ ሄደው ሲመራመሩ ይገለጥላቸው ነበር ብሎ እንደ ማጠናከሪያ መጥቀሱ ነው። [አልመጧሊብ፡ 243] ሱብሓነላህ! በዚህ ደረጃ ያለ ሰው ነው እንግዲህ የአኢማዎች ኢማም የሆኑትን ኢብኑ ኹዘይማን የሚወርፈው።
ይሄ ብቻም አይደለም። የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ከሚያስተባብሉ አሽዐሪዮችና ማቱሪዲያዎች ውስጥ የሱና ሰዎችን ብቻ ሳይሆን አልፈው ቁርኣንና ሐዲሥን ጭምር በተሽቢህ (ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በማመሳሰል) በግልፅ እስከ መክሰስ ደርሰዋል። ከነዚህ ደፋሮች ውስጥ አንዱ ይሄው ፈኽሩ ራዚ ነው። በመረጃ ነው የማወራው። ይሄውና ንግግሩ፡-
أن الأخبار المذكورة في باب التشبيه بلغت مبلغاً كثيراً في العدد، وبلغت مبلغاً عظيماً في تقوية التشبيه، وإثبات أن إله العالم يجري مجرى إنسان كبير الجثة عظيم الأعضاء! وخرجت عن أن تكون قابلة للتأويل
“በማመሳሰል ርእስ ላይ የተጠቀሱት ዘገባዎች በቁጥር ብዙ መጠን ደርሰዋል። ማመሳሰልን በማጠንከርና የአለሙ አምላክ ግዙፍ ክፍሎች ያሉት ትልቅ አካል እንደሆነ በማፅደቅ ላይ ከባድ ደረጃ ደርሰዋል። ተእዊልን (ቁልመማን) የሚያስተናግዱ ከመሆንም አልፈዋል።” [አልመጧሊቡል ዓሊያ፡ 9/213]
ንግግሩን በጥሞና አስተውሉት። ሸሪዐዊ ማስረጃዎችን በ“ማመሳሰል” መክሰሱን ተውት። አሽዐሪያ ሰፈር የተለመደ በሽታ ነው። ሰውየውም የአላህን መገለጫዎች (ሲፋት) የሚያፀድቁ ማስረጃዎችን ነው ማመሳሰልን ይሰጣሉ፣ ማመሳሰልን ያጠናክራሉ የሚለው። ነገር ግን የአላህን ሲፋት የሚገልፁ የሸሪዐ ማስረጃዎች ከመብዛታቸው የተነሳ ለቁልመማ እንኳን እንደፈተኗቸው ማመኑን አስምሩበት። (ከመቆልመም ባይመለሱም።) በዚህ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎችን ገፍተው ከጣሉ በኋላ ነው እንግዲህ ራሳቸውን የተውሒድ ሰዎች አድርገው የሚያቀርቡት። ደግሞም እወቁ! የዛሬዎቹ አሕባሾች ዑለማዎችን ማkፈር ከቀደሙት የጥፋት አስተማሪዎቻቸው የቀዱት ልክፍት እንጂ አዲስ ነገር አይደለም።
የሆነ ሆኖ ራዚ የኋላ ኋላ በከባባድ የዐቂዳ ጉዳዮች ላይ ግራ መጋባቱን ደጋግሞ ይገልፅ ነበር። እድሜውን የፈጀበትን የዒልመል ከላም ፍልስፋና ጥሎ “የአሮጊቶችን መንገድ አጥብቆ የያዘ እርሱ ነው የሚድነው!” ሲል እንደነበር ኢብኑ ከሢር እና ሌሎች አኢማዎች ገልፀዋል። [አልቢዳያ ወኒሃያ፡ 17/12]

Ibnu Munewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.9K viewsedited  18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-27 06:20:29 ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሶላት ላይ የመጀመሪያውን ረከዐ ከሁለተኛው በላይ ያስረዝሙ ነበር። [ቡኻሪና ሙስሊም]
ይሄ አፈፃፀም በዚህ ዘመን አብዛኛው የመስጂድ ኢማም ችላ ያለው ሱና ነው ይላሉ ሸይኽ ዐብደላህ አልፈውዛን። [ሚንሓቱል ዐላም: 3/77]

Ibnu Munewor

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
12.7K views03:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-26 10:31:22
የአፋልጉኝ ማስታወቂያ

በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወንድማችን አብዱ ወራቄ ይባላል። እድሜው 18 አመት ሲሆን ይሰራበት ከነበረው ጥቁርአንበሳ አከባቢ ከሚገኝ ጁስቤት ሰኔ 10/10/2015 ላይ እደወጣ አልተመለሰም።  ወንድማችን ያየ
በ0966203725 መሃመድ ሰፈራ ብለው ቢደውልሉን ውሮታውን ከፋይ ነን ይላሉ ቤተሰቦቹ። እንተባበራቸው።

+251927841649 የወላጅ አባቱ ቁጥር ወራቄ ፍንታዬ
13.3K views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-26 07:15:16 ታሪክ በሁለት ፅንፍ መሀል
~
ውስብስቡ የኢትዮጵያ ታሪክ በማጠልሸት፣ በግሳንግስ ተረት፣ በመረጣ የታጨቀ እንደሆነ ግልፅ ነው። እጅግ በርካታ የታሪክ ስራዎች ላይ ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ ውገናዎችና ጥላቻን መሰረት ያደረጉ ስልታዊ ማግለሎች በተጨባጭ አሉ። ይህንን ያፈጠጠ ገፊና አግላይ እውነታ እጅግ አልፎ አልፎ በገጠሙ ሽርፍራፊ አዎንታዊ ክስተቶች ለመሸፈን መሞከር ፀሐይን በእጅ ለመጋረድ እንደ መሞከር ነው።
በሌላ በኩል በዘመናዊው የኢትዮጵያ ታሪክ እየቀረቡ ያሉ የብሶት ትርክቶችም መጠኑ ቢለያይም ከመረጃ የተኳረፉ ብዙ ድርሰቶች ወይም ስንጥር መረጃ ይዘው መሬት ላይ በገሃድ ያልነበረ ምስል የሚስሉ ተረኮች እየወጡበት ነው። በዚያ ላይ ብዙዎቹ ከገንቢነታቸው ይልቅ አፍራሽ ሚናቸው የጎላ ነው። ኃላፊነት የጎደላቸው የዘመናችን ፖለቲከኞችና አክቲቪስቶች ትልቁ ነዳጃቸው የብሶት ትርክት ነው። ሲጀመር ትውልዱን በታሪክ እየቆዘመ እንዲኖር ማድረግ ካለበት ተጨባጭ ጋር ተግባብቶና አዎንታዊ አመለካከት ገንብቶ ከመኖር ይልቅ ሁሌ ብሶትን እንዲያቀነቅን መክተብ ነው።
እነዚህ ሁለቱ ፅንፎች አንዳቸው የሌላውን ህመም የመጋራት፣ ወይም የሌላውን ብሶት የማድመጥ ፍላጎትም ትእግስትም የላቸውም። የነዚህ ተቃራኒ ትርክቶች አቀንቃኞች እጅግ አስፈሪ የሆነ ትውልድ እንዲመጣ አድርገዋል። የትላንት ጨቋኞችን ለመበቀል ከምኑም የሌሉ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ስለት ማንሳትን እንደ ጀብድ የሚቆጥር ትውልድ ነው የመጣው። ይሄ ውሉን የሳተ የጨቋኝ - ተጨቋኝ ትርክት ውጤት ነው። ሞልቶ የገነፈለ የህዝብ ለህዝብ ጥላቻ ቀላል የማይባል የማህበረሰባችንን ክፍል አጥቅቷል። ሰርክ "አፄዎቹ አፄዎቹ" ከማለት ባሻገር መሬት ላይ ወርዶ ህዝብ ላይ እየተፈጠረ ያለውን ጥሩ ያልሆነ ስሜት እንዲሁም እየተከሰተ ያለውን መራር እውነታ መመልከት ያሻል። በዳይ በሆነው የዘር ሚዛን እየተመዘነ ላ ኢላሀ ኢለላህ ዋጋ አጥቷል። የሸሃደተይን ዋጋ ከብሄርና ከቋንቋ በታች ሆኗል።
የሙስሊም ፀሐፍት ትኩረት መሆን ያለበት ህዝበ ሙስሊሙ አይነታቸው የበዙ የዘመኑን ፈተናዎች የሚጋፈጥባቸው ግንዛቤዎች እንዲኖሩት ማስታጠቅ ነው። የትላንቱን በደል የምንተርክበት የተዛነፈ መንገድ ዛሬ የገዛ ወገናችንን የሚበላ እሳት እየፈጠረ እንደሆነ አይቶ ባሉበት ከመቀጠል ይልቅ አካሄድን ቆም ብሎ መገምገም ያሻል። ስለ ትላንቱ ስንታመም ዛሬ ደጋግመን እየሞትን ነው።

Ibnu Munewor

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.2K viewsedited  04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-25 09:27:52 አብዛኞቹ የደዕዋ ሰዎች፣ መሻይኾች ስለ ዘረኝነት መረር ያለ ትምህርት ለመስጠት ፈቃደኛ አይደሉም። እንዲያውም በሚያሳዝን ሁኔታ የችግሩ አካል የሆኑት ብዙ ናቸው። ዘረኝነት ከመቼውም ጊዜ በባሰ አደጋው ጨምሯል። የዱር አውሬ ላይ ቢፈፀም ህሊና የማይቀበለው ዘግናኝ የሆነ ጭካኔ ላ ኢላሀ ኢለላህ በሚል ወገን ላይ እየተፈፀመ ነው። ስለ ችግሩ ለመናገር ምን እስከሚደርስ እንደምንጠብቅ አላውቅም። የሚታየው የሚሰማው ሁሉ ህሊናን የሚያዝል፣ ልብን የሚያቆስል ነው።
በነገራችን ላይ ስለ ዘረኝነት አለማስተማር ለራስ ዘር መቆርቆር ወይም ነውራቸውን መሸፈን አይደለም። ለወገን መቆርቆር ማለት አላህ ዘንድ ከሚያስጠይቃቸው ወንጀል እንዲርቁ ማሳሰብ ነው። ነውር የሚሸፈነውም በተግባር ነውርን በማስቀረት ነው። እንጂ ችግራችን ለሁሉ የሚታይ ከሆነ አይተን እንዳላየን በዝምታ በማለፍ አንሸፍነውም። አላህ ልብ ይስጠን።

Ibnu Munewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.6K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-20 19:55:14 አንገብጋቢ ነጥብ ኪታብ ለሚማሩ ተማሪዎች
~
የምንማረውን ኪታብ ለመገንዘብና ይዞ ለማቆየት ሁለት ነገሮችን ማጤን ይገባል።
1ኛ፦ ስንማር ጊዜ ከልብ ሆኖ መከታተል። ማስታወሻ መያዝ የሚፈልግ ነጥብ ካለ መፃፍ።
2ኛ፦ ከደርስ በኋላ ሙራጀዐ ማድረግ። የተማርነውን ኪታብ ከደርስ በኋላ ቢያንስ አንድ ጊዜ ክለሳ ማድረግ ይገባል። ከተቻለ ወደ ቀጣዩ ደርስ ከመግባታችን በፊት አንዴ ብንደግመው መልካም ነው። ከዚያ ያልገባን ወይም የዘነጋነው ካለ እንጠይቃለን። ክለሳ ከሌለ የያዝነውንና ያልያዝነውን አንለየውም። የያዝነውም በቀላሉ ሊዘነጋ ይችላል። ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ለሚፈልግ ክለሳ እየተዘናጋን ልፋታችንን ዋጋ ልናሳጣው አይገባም።

Ibnu Munewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
14.3K viewsedited  16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-18 20:55:36 ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:-
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 190፣ باب الرجاء
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
13.6K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-17 20:51:30 ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:-
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 186፣ ሐዲሥ ቁ. 402
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
14.8K views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ