Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች H
የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.64K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-03-15 07:20:52
የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና በእነ አብዲ ሞሃመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) መዝገቦች ቀርበው የነበሩ ክሶች እንዲቋረጡ መወሰኑን አሳውቋል።

በእነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው መዝገብ ስር ያሉ ተከሳሾች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሙስና ወንጀል ክስ ክርክር ሲካሄድ ነበር።

በሌላ በኩል የእነ አብዲ ሞሃመድ ኡመር የክስ መዝገብ በ1ኛ የህገመንግስትና የሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት የክርክር ሂደት ላይ ቆይቷል።

የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር እነዚህ የክስ ሂደቶች "ለዘላቂ የህዝብ ጥቅም " ሲባል እንዲቋረጡ ተወስኗል ብሏል።
20.1K views04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-12 00:53:49
ይህ የምትመለከቱት በቻይና Hangzhou ግዛት የሚገኝ በአለማችን ትልቁ የጋራ መኖሪያ አፓርታማ ሲሆን 30,000 ቤቶች በጋራ ይኖርበታል።
12.9K views21:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 22:16:06 የቤቶቹ ጨረታ ላይ የተነሳው ጥያቄ ምንድነው ?

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የ1997 ዓ.ም. የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ዕጣ ያልወጣላቸው ቆጣቢዎች ያቀረቡለትን አቤቱታ መሠረት በማድረግ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከ3 ሺህ ቤቶች በላይ በሽያጭ ለማስተላለፍ ያወጣው ጨረታ ላይ የሕጋዊነትና የፍትሐዊነት ጥያቄ አንስቷል።

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አጋጠመኝ ያለውን የፋይናንስ አቅም ችግር ለመፍታትና ተጨማሪ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን ለመገንባት፣ ከከተማው የዲዛይንና ግንባታ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን 3,146 የመኖሪያ ቤቶችንና 306 የንግድ ሱቆችን በጨረታ ለመሸጥ ማቀዱን መግለጹ ይታወሳል።

በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበው ከስቱዲዮ እስከ ባለ3 መኝታ ቤት ድረስ ቤቶች ለማግኘት እየቆጠቡ ያሉ 959 ነዋሪዎች፣ እያንዳንዳቸው ምን ያህል እንደቆጠቡ የሚገልጽ ሙሉ ስማቸው ከፊርማቸው ጋር ያረፈበትና በድምሩ 144,820,085.43 ብር መቆጠባቸውን ከሚያሳይ ሰነድ በማያያዝ፣ ኮርፖሬሽኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶቹን ለመሸጥ የጀመረውን ሒደት #እንዲያሳግድላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ ለዕንባ ጠባቂ ተቋም ጨረታው ይፋ በተደረገበት ዕለት አስገብተው ነበር።

አቤቱታቸውን የተቀበለው ዕንባ ጠባቂ ተቋም የካቲት 22 ቀን 2016 ዓ.ም በዋና ዕንባ ጠባቂ እንዳለ ኃይሌ (ዶ/ር) ተፈርሞ በወጣ ደብዳቤ፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ7 የሥራ ቀናት ውስጥ ምላሹን እንዲያሳውቀኝ ሲል 4 ጥያቄዎችን አቅርቧል። 

1ኛ. ኮርፖሬሽኑ የመኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ በሽያጭ የማስተላለፍ ሕጋዊ መሠረት ያለው ስለመሆኑ በማስረጃ ተደግፎ እንዲቀርብ ብሏል። 

2ኛ. መኖሪያ ቤቶቹ በጨረታ ለሽያጭ ሲቀርቡ የ1997 ዓ.ም. እና የ2005 ዓ.ም. የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎችን ቅድሚያ በመስጠት፣ በልዩ ሁኔታ ተሳታፊ ያልተደረገበት ምክንያት እንዲገለጽ ጠይቋል። 

3ኛ. ኮርፖሬሽኑ የመኖሪያ ቤቶችን ከዕጣና ከምደባ ውጪ በጨረታ ሽያጭ ለማስተላለፍ ሲወስን፣ በ1997 ዓ.ም. እና 2005 ዓ.ም. ተመዝግበው ቤት እየተጠባበቁ ያሉ ነዋሪዎች ጉዳይ ላይ ግልጽና የመጨረሻ ውሳኔ ያልተሰጠበትን ምክንያት እንዲገለጽ የሚል ጥያቄ አቅርቧል። 

4ኛ. ኮርፖሬሽኑ ቤቶችን በጨረታ ለመሸጥ ሲወስን ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው የከተማው ነዋሪዎችን አቅም ባገናዘበ መንገድ የጨረታ መነሻ ዋጋና የአከፋፈል ሥርዓት ሊታይ ያልቻለበትን ምክንያት በመግለጽ፣ ኮርፖሬሽኑ ምላሹን በሰባት የሥራ ቀናት ውስጥ እንዲሰጥ ሲል በደብዳቤ ጠይቋል። 
13.3K views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 22:13:23
የቤቶች ጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ተጠናቀቀ።

የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነቧቸውና ለጨረታ ያቀረቧቸው 3,146 የመኖሪያና 306 የንግድ ባጠቃላይ 3,452 ቤቶች የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ በዛሬው ዕለት መጋቢት 02/2016 ዓም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት መጠናቀቁ ተገልጿል።

ከጥር 27/2016 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን የቆየው የሰነድ ሽያጭ በዛሬው ዕለት መጠናቀቁን ተከትሎ በነገው ዕለት መጋቢት 03/2016 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥን ይከፈታል ተብሏል።

በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ለጨረታ የቀረቡት 935 የመኖሪያና 15 የንግድ ቤቶች ላይ ተጫራቾች ያስገቧቸው ሰነዶች በታዛቢዎች ፊት የሚከፈት ይሆናል ተብሏል።
13.1K views19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 20:55:08
14.1K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-10 14:30:59
የሚሻለው የህዝብ ጥቆማዎችን መቀበል እና ማጣራት ማድረግ ወይስ ለማዳፈን መሞከር?

በቅርቡ በቦሌ ኤርፖርት ባሉ ብልሹ አሰራሮች ዙርያ አንዳንድ መረጃዎችን አጋርቼ ነበር፣ የተወሰኑ እርምጃዎችም እንደተወሰዱ መስማቴን እንዲሁ። በርካታ ሌሎች ግለሶችም 'እኛም ላይ እንዲህ ደርሷል' በማለት ማህበራዊ ሚድያ ላይ መረጃ አጋርተዋል። እኔ ያጋራሁት መረጃ ጉዳይ አየር ማረፊያውን ከሚያስተዳድሩ አካላት ጋር እንጂ ከአየር መንገዱ ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ ለማስረዳት ሞክሬያለሁ።

ይህንን በአራት ባለስልጣናት ዛሬ የተሰጠ መግለጫን ሳነብ መጨረሻ አካባቢ "በኤርፖርት ዙሪያ የወንጀል ተግባራት ላይ በሚሳተፉ ሰዎች ላይ ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተገቢው  ማጣራት ተደርጎ  ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ገልፀዋል" ይላል። መልካም።

ይሁንና ቅሬታው በቀጥታ በአየር መንገዱም ዙርያ ቢሆንም ጥቆማዎችን አመስግኖ ተቀብሎ ማጣራት ማድረግ ይገባል እንጂ ለማዳፈን መሞከር አይጠቅምም።

ይበልጥ የሚገርመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወሮ ሰላማዊት ዳዊት ለኢቢሲ "የስራ ጫና በሚኖርበት ወቅት ችግር የሚፈጥሩ ሰራተኞች እንዳሉ እንገነዘባለን" ብለው ትናንት ተናግረው ነበር።

ነገር ግን ሀላፊዋ በልጁ ላይ በቅርቡ የተፈፀመ እንግልትን መረጃ ያጋራ አቶ ነብዩ ሲራክ የተባለ ግለሰብ ጋር ስልክ በመደወል "ሚዲያ ላይ መወራቱ ማንንም አይጠቅምም፣ ምናልባት እናንተን ታዋቂ popular ሊያደርጋችሁ ይችል ይሆናል፣ ተቋሙ ያለ መረጃ መሰደብ የሌለበት ተቋም ነው" እንዳሉት መረጃ አጋርቷል።

ከህዝብ የሚደርሱ ቅሬታዎች እና ጥቆማዎች ለለውጥ ለሚሰራ አካል መሻሻሎችን ለማድረግ ከፍተኛ ግብዐቶች ናቸው፣ የስም መነሳት ብቻ ለሚያሳስበው አካል ግን ትንኮሳዎች እና የስም ማጥፋት ድርጊቶች ናቸው።

1/2
18.2K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-10 14:30:55 2/2
Note: እዚህ መግለጫ ላይ ለተገኙ አንድ ሀላፊ በኤርፖርት ስለሚሰሩ ውንብድናዎች መረጃ ከማስረጃ ጋር በቀጥታ አድርሻቸው ነበር፣ ሊንክ ላክልኝ ብለው ከላኩላቸው በኋላ እስከዚህ መግለጫ ድረስ ዝምታን መርጠው ቆይተዋል።

*ኢቢሲ ይህን ዜና ሲያጋራ የህዝብ አስተያየት ፈርተው ይሁን ሌላ ባላውቅም ከሌሎች ዜናዎች በተለየ የአስተያየት መስጫ (comments section) ቆልፈው ነው።

@EliasMeseret
16.7K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-10 04:49:49
የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ኮርፖሬሽን ጨረታ ባወጣባቸው የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ዙሪያ ከጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ላቀረቡበት ቅሬታ ባንድ ሳምንት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቋል። ኮርፖሬሽኑ ከኹለት ሳምንት በፊት ጨረታ ያወጣው፣ በ3 ሺህ 146 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና በ306 ለንግድ መደብርነት በተሠሩ ቤቶች ላይ ነበር። ኾኖም ከ950 በላይ የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች የጨረታውን መውጣት በመቃወም ለእንባ ጠባቂ ተቋም አቤቱታ አቅርበዋል። እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ለዓመታት ገንዘብ በባንክ እየቆጠቡ የጋራ መኖሪያ ቤት ያልደረሳቸው በርካታ ተመዝጋቢዎች እያሉ ኮርፖሬሽኑ ለምን በጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ላይ ጨረታ እንዳወጣ ማብራሪያ እንዲሰጥ ነው። ኮርፖሬሽኑ ቀደም ሲል የቆረጠውን የጨረታ ማውጫ ቀን ወደ መጋቢት 3 አራዝሞታል።

ዋዜማ
18.4K views01:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-09 17:59:23
ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች 5 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሊገነባ ነው
****

በ450 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ለሚገነባው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ሰራተኞች ሁለተኛ ምዕራፍ የ5 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።

የግንባታ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ የመሰረት ድንጋዩን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስቀምጠዋል።

በግንባታ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሥራ አስፈጻሚ ሳሙኤል ታፈሰ፣ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታረቀኝ ገመቹና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

በ17 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የቤቶቹ ግንባታ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሲኤምሲ ልዩ ሥሙ ሃያት-49 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ እንደሚከናወን ተገልጿል።

ግንባታው በሰንሻይን ኮንስትራክሽንና በቻይናው ኮንስትራክሽን ኮሙኒኬሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ) የሚከናወን ሲሆን በአራት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል መባሉን ኢዜአ ዘግቧል።

በፕሮጀክቱ ከ5 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚይዝ የመኪና ማቆሚያ ሥፍራ፣ የልጆች መጫወቻ፣ አረንጓዴ ሥፍራ፣ ትምህርት ቤት፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራና የገበያ ማዕከላት እንደሚይዝ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም ቤቶቹ የራሱ ጥልቅ ጉድጓድ ውኃና የፀሐይ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚኖረውም ተመላክቷል።
19.4K views14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-09 16:33:57
ኮርፖሬሽኑ ከአራት ኪሎ ቀበና የመንገድ ኮሪደር ለተነሱ 21 የልማት ተነሺዎች የእጣ ማውጣት ስነ ስርዓት አካሄደ

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከየካ ክፍል ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ከአራት ኪሎ ቀበና የመንገድ ኮሪደር ለተነሱ 21 የልማት ተነሺዎች ምትክ ቤት ለመስጠት እጣ የማውጣት ስነ ስርዓት አካሄደ።

ዕጣ የማውጣት መርሀግብሩ ላይ የተሳተፉት አዲስ አበባን የሚመጥን የኮሪደር ልማት ስራ የሚሰራባቸው አካባቢዎች ላይ የሚገኙ ተነሺዎች ሲሆኑ  የልማት ተነሺዎቹ  ተገቢው ምትክ እንደሚሰጣቸው በተገባው ቃል እና በመመሪያው መሰረት የጋራ መኖሪያ ቤት እጣ አውጥተዋል ።
18.5K views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ