ኮርፖሬሽኑ ከአራት ኪሎ ቀበና የመንገድ ኮሪደር ለተነሱ 21 የልማት ተነሺዎች የእጣ ማውጣት ስነ ስርዓት አካሄደ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከየካ ክፍል ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ከአራት ኪሎ ቀበና የመንገድ ኮሪደር ለተነሱ 21 የልማት ተነሺዎች ምትክ ቤት ለመስጠት እጣ የማውጣት ስነ ስርዓት አካሄደ። ዕጣ የማውጣት መርሀግብሩ ላይ የተሳተፉት አዲስ አበባን የሚመጥን የኮሪደር ልማት ስራ የሚሰራባቸው አካባቢዎች ላይ የሚገኙ ተነሺዎች ሲሆኑ የልማት ተነሺዎቹ ተገቢው ምትክ እንደሚሰጣቸው በተገባው ቃል እና በመመሪያው መሰረት የጋራ መኖሪያ ቤት እጣ አውጥተዋል ። 18.5K views13:33