Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.71K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-20 15:21:08
13.2K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 15:18:30
የኢትዯጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተከሰተው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ 95% የሚሆነውን ማስመለስ ቻለ፡፡
**********
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 7፣ 2016 ዓ.ም በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801,417,747.81 ያለአግባብ ተወስዶ እንደ ነበር የተገለጸ ሲሆን ከዚህም ገንዘብ ላይ ብር 762,941,341 ማስመለስ ችሏል፡፡ ይህም መሰብሰብ ከነበረበት ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን ቀሪውን 5 በመቶ ብር 38,474,938 ገንዘቡን ተመላሽ ካላደረጉ ግለሰቦች የማስመለስ ሥራው እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡
13.0K views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 13:42:48
ሚያዝያ 12፤2016 - በአዲስ አበባ ከተማ በተገነቡ ማዕከላት ከመደበኛው ገበያ የጤፍ ዋጋ ላይ የ3 ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው ተገለፀ

በአዲስ አበባ ከተማ ተገንብተው አምራችን ከሸማቾች የሚያገናኙ ሶስት ማዕከላት ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው አሁን ላይ በዋነኛነት የገበያ ማዕከላት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን የተናገሩት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ከ3.3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው እንደተገነቡ ተናግረዋል።

ከተማ አስተዳደሩ በእነዚህ ማዕከላት አምራቾችን ሙሉ በሙሉ አስገብቶ ለሸማቾች ከማሳ የተሰበሰቡ ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ እያቀረበ ነው ብለዋል።እነዚህ ማዕከላት በሸማቹ እና በአምራቹ መሀል የነበረውን ህገ ወጥ ደላላን መስበር የቻለ ነው።

ከዋጋም አኳያ ከእሁድ ገበያ አንፃር የተሻሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።ምርቶች በበቂ ሁኔታ በገበያ ማዕከላት ቢገቡም ህብረተሰቡ ስለ ማዕከላቱ በቂ ግንዛቤ ስሌለው የሚበላሹ ምርቶች አሉ በተለይ ደግሞ የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ብልሽት እንደሚገጥማቸው ተናግረዋል።

ሸማቹ ወደ እነዚህ ማዕከላት በመምጣት ሁሉንም ምርቶች በአንድ እንዲሁም በቅናሽ ዋጋ ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል።ከመደበኛ ገበያዎች የጤፍ ዋጋ በእነዚህ ማዕከላት ውስጥ የ3ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው አንስተዋል። እንዲሁም አትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶችም ከእሁድ ገበያው ቅናሽ እንዳለውም አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል።

ማዕከላቱ በኮልፌ ፣በአቃቂ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ይገኛሉ ተብሏል።

በምህረት ታደሰ
#BisratFm
14.3K views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 07:41:47
በኮሪደር ልማት እየተሰራ የሚገኘው የአራት ኪሎ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ
16.2K views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 22:03:36
ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያሏት የሚሊየነሮች ቁጥር በአጠቃላይ 2,700 መድረሱን በዘርፉ ላይ የተደረገ አንድ ሪፖርት አመላከተ

ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ ወደ 2,700 የሚጠጉ ሚሊየነሮች እንዳሏት የገለፀዉ ይህ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ሀገሪቷ በዚህ የስነ ህዝብ እድገት ዉስጥ ጠንካራ እንድገት እንደሚኖረዉ ትንበያውን አስቀምጧል።

በ 2024 የወጣዉ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ዘጠኛ እትሙ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳዲስ ገበያዎችን የሚይዘው የአህጉሪቱ ሚሊየነር ህዝቧ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ዉስጥ በ 65% ከፍ ሊል እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል ።

አሁን ላይ በአፍሪካ ያለዉ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ሀብት 2.5 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱ የተነገረ ሲሆን ኢትዮጵያ በዚህ ኢኮኖሚ እድገት ዉስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጓ ነዉ ይህ ሀተታ የሚያመላክተዉ።

capital
14.8K views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 22:12:29 #ለመረጃ

የመጋቢት ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 26.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አሳወቀ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ፦

ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 29 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።

ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 22 በመቶ በመሆን ተመዝግቧል።

በአጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ #በየካቲት_ወር ከነበረበት 28.2 በመቶ ወደ 26.2 በመቶ በመሆን መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመላክቷል።
18.6K views19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 08:40:32
Good Morning
20.4K views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 11:29:16
17.6K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 16:45:36
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የአገሪቱን የንግድ ባንኮች ባላቸውን ካፒታልና አሴት መሰረት በሶስት የተለያዩ ምድቦች መክፈሉ ተገለፀ።
እንደ መረጃ መንጮች የአገሪቱ ባንኮች ከፍተኛ ምድብ፣ መካከለኛ ምድብ እና ዝቅተኛ ምድብ በማለት ተከፍለዋል ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአገሪቱ ጠቅላላ ባንኮች 49.5 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 48.7 በመቶ የተቀማጭ ገንዘብ በመያዝ ከፍተኛ ምድብ ላይ መቀመጥ እንዲችል የተደረገ ሲሆን ሌሎች አምስት ባንኮች በድምር ከአገሪቱ ጠቅላላ ባንኮች 28 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 29.4 በመቶ የተቀማጭ ገንዘብ በመሰብሰብ መካከለኛ ምድብ ተቀምጠዋል።
በዚህ ደረጃ የተመደቡ ባንኮች አቢሲኒያ ባንክ ፣ ዳሽን ባንክ፣ሕብረት ባንክ ፣ አዋሽ ባንክ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ሲሆኑ የካፒታል መጠናቸው በድምር ባለፈው ሰኔ 2023 በጀት መዝጊያ ላይ 31 በመቶ መሆኑ ተገልጿል ።

በዝቅተኛ ምድብ የተቀመጡት 24 ባንኮች ሲሆኑ 22.5 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 21.9 በመቶ ተቀማጭ ገንዘብ አላቸው የካፒታል መጠናቸው ከጠቅላላው የአገሪቱ ባንኮች 41.6 በመቶ መሆኑ ተገልጿል ።
13.2K views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 15:57:59
ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከዚህ ቀደም በ70/30 በማህበር ለመደራጀት ተመዝግባችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረ የ20/80 እና 40/60 ተመዝጋቢዎች  ከሚያዝያ 8/2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 የስራ ቀናት ውስጥ አዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ  6ኛ ፎቅ የጋራ መኖሪያ እና ህብረት ስራ ማህበር ዳይሬክቶሬት ዘውትር በስራ ሰአት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ ፡- ቀደም ሲል 70 ፐርሰንት በባንክ አካውንት ገንዘብ አስገብታችሁ ከሆነ የባንክ እስቴትመንት ይዛችሁ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡ 70 ፐርሰንቱን ገቢ ያላደረጉ ከሆነ ለተመዘገቡበት የቤት አይነት ከሚያዝያ 8/2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 የስራ ቀናት ውስጥ ገንዘቡን በቀድሞ የ40/60 ወይም የ20/80 ቤት ቁጠባ አካውንት ላይ ገቢ በማድረግ  እና እስቴትመንት ይዛችሁ በመቅረብ ብቁ መሆኑን በአካል ቀርበው ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
14.7K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ