Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት ሚኒስቴር

የቴሌግራም ቻናል አርማ timihert_minister — ትምህርት ሚኒስቴር
የቴሌግራም ቻናል አርማ timihert_minister — ትምህርት ሚኒስቴር
የሰርጥ አድራሻ: @timihert_minister
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.06K
የሰርጥ መግለጫ

ተጨማሪ መረጃዎችን
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም-https://t.me/timihert_minister
ይከታተሉ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-13 19:41:01
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉትን ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን አስታወቀ
....................................................

ሚያዝያ 04/2015ዓ.ም.(የትምህርት ሚኒስቴር) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉትን ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን አስታውቋል ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና የዩኒቨርሲቲው ራስ-ገዝ መሆን የአካዳሚ፣ የአስተዳደር፣ የፋይናንስ እና የሰው ሀብት አስተዳደራ ላይ የመወሰን ነጻነት የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ደግሞ ለቀጣይ የዩኒቨርሲቲው ሁለተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር ጣሰው ዩኒቨርሲቲው ሲመሰረት ከራስ-ገዝነት ሥልጣኑ ጋር መሆኑን ጠቅሰው ነገር ግን ከጊዜያት በኋላ በተለያዩ መንግሥታት ቀስ በቀስ የራስ-ገዝነት ሥልጣኑን እያጣ መጥቶ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተጠቁመዋል ።

ፕሮፌሰር ጣሰው ዩኒቨርሲቲው ከረዥም ዓመታት በኋላ ከቀጣይ አመት ጀምሮ የራስ-ገዝነት ሥልጣኑን ልያስመልሱለት የሚችሉ ውስጣዊ ቅድመ ዝግጅቶችን ላለፉት ሁለት አመታት ሲያደርግ መቆየቱንና በአሁኑ ወቅት ማጠናቀቁን ጠቅሰው ለአብነት ያክልም የዩኒቨርሲቲው የፋይናንስና የሰው ኃይል አደረጃጀት መመሪያ መዘጋጀቱን፣ በመመሪያ ላይ ከሠራተኞች ጋር ውይይት መደረጉንና በቀጣይ ለቦርድ ውሳኔ የሚቀርብ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በ14 ካምፓሶች 70 የቅድመ-ምረቃ እና 293 የድህረ-ምረቃ የትምህርት ፕሮግራሞችን እየሰጠ ይገኛል።
799 views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:41:00 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ዝግጁ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ገለጹ
....................................................
ሚያዝያ 04/2015 ዓ.ም .(የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

መውጫ ፈተናው ተማሪዎች በሰለጠኑባቸው የሙያ ዘርፎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ፡፡

የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚሰጥ ሲሆን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መውጫ ፈተናውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፡፡

የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ መውጫ ፈተና ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው የሚጠቀሙባቸውን እውቀት ክህሎትና አመለካከት በብቃት መያዛቸውን መለኪያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ብቻ ሳይሆን ዩኒቨርስቲዎች በትምህርት አሰጣጥ ላይ ያሉበትን ሁኔታ በማሳየት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሚናው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡

የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የመውጫ ፈተናውን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱንና አስፈላጊውን ግብዓት የማሟላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ጎን ለጎንም ተፈታኞችን በእውቀትና በስነልቦና የማዘጋጀት ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኝ በበኩላቸው የመውጫ ፈተና ውጤት ፍትሀዊነትን የሚመልስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የመውጫ ፈተናው የመጀመሪያው እንደመሆኑ መጠን ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች ድጋፍ የማድረግ ስራ እየተሰራ ስለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፈተናው የሚሰጥባቸውን የትኩረት መስኮች በመለየት የማጠናከሪያ ፕሮግራም እየተሰጠ ነው ያሉት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዳምጠው ደርዛ ናቸው፡፡

ጎን ለጎንም ለሴቶችና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ተኩረት ተሰጥቶ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል ፕሬዚዳንቱ፡፡

የከፍተኛ ትምህርት አገራዊ ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና በአግባቡ ለመምራትና ለማስተዳደር የተዘጋጀው የፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ባለፈው ዓመት ነሀሴ ወር ላይ መጽደቁ ይታወሳል፡፡



ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et

ይከታተሉ
---------
763 viewsedited  16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 21:28:17
በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሥራ በቅርቡ ይጀመራል-ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
................................................................................

ሚያዝያ 3/2015(የትምህርት ሚኒስቴር)፦ በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሥራ በቅርቡ የሚጀመር መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

የአዲስ ወግ “የመደመር ትውልድን መቅረጽ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ በተደረገው መድረክ የውይይት መነሻ ሃሳብ ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁሉም አካባቢዎች ምቹ የትምህርት ቤት ከባቢ መፍጠር፣ የትምህርት ቤት አመራር ሥልጠና፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ማሻሻል ከዋና ዋና ሥራዎች መካከል መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ከ47ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የተናገሩት ሚኒስትሩ ከእነዚህም መካከል አብዛኛዎቹ ተገቢውን መስፈርት ባሟላ መልኩ የተገነቡ አለመሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በአገር አቀፍ ደረጃ ሕብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ዘመቻ ለማከናወን ዕቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል ሚኒስትሩ።

ዘመቻውም በቅርቡ ይፋ ተደርጎ ወደ ተግባር እንደሚገባ ጠቅሰው የትምህርት ቤት አመራሮችን ብቁ ማድረግ የሚያስችል ሥልጠና እንደሚከናወን ገልጸዋል።
1.2K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 21:28:17
የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጅ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች እንዲያካትት ተደርጎ መዘጋጀት አለበት
፦የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ
............................................
ሚያዚያ 03/2015 ዓ.ም.(የትምህርት ሚኒስቴር)፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትናንትና ውሎው የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጁ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች እንዲያካትት ተደርጎ በጥንቃቄ መዘጋጀት እንዳለበት አሳስቧል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) እንዳሉት ረቂቅ አዋጁ የዩኒቨርሲቲዎችን አካዳሚክ ነፃነት የሚያጎናፅፍ ቢሆንም ከመንግሥትም ሆነ ከግል ዩኒቨርሲቲዎች የሚመረቁ ተማሪዎች ላይ ቅሬታ እንዳይፈጥር የዩኒቨርሲቲዎችን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የኅብረተሰቡን ፍላጎትም ያካተቱ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡
1.1K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:56:35
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችንና ትምህርት ቤቶች ትምህርት ለማስጀመር ሁሉን አቀፍ ዝግጅት እየተደረገ ነው-
.............................................

መጋቢት 29/2015ዓም.(የትምህርት ሚኒስቴር)፦ በትግራይ ክልል የሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎችን እና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር የስርዓተ ትምህርትና የመምህራን ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች፣ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶችና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች በክልሉ ትምህርት ማስጀመር የሚያስችል ውይይት አድርገዋል።

መንግስትና ህወሃት በፕሪቶሪያ የደረሱትን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ ከማቅረብ ጀምሮ የክልሉን ህዝብ በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችሉ የመልሶ ግንባታና መሰረታዊ አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው።

መንግስት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም፣ የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ ፈትተው ወደ መደበኛ ህይወት እንዲመለሱ፣ መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ፣ እንዲሁም ትምህርት እንዲጀመር የሰላም ስምምነቱን እየተገበረ ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በውይይቱ ላይ እንዳሉት፣ በግጭቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የዩኒቨርሲቲዎችና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚህም የትምህርት ተቋማት የደረሰባቸውን የጉዳት መጠን በማጥናት ትምህርት ለመጀመር የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ለይተን ቅድመ ዝግጅት ጀምረናል ብለዋል።
2.1K viewsedited  15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 18:41:41
ከመጽሀፍ ገጾች.....

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ሶሶተኛውን መፃፋቸውን : የመደመር ትውልድ ማስመረቃቸው ይታወቃል፡፡ በዚህ መጽሃፍ የትምህርት ጉዳይ አስኳላ እና አስኳል በሚለው ርዕስ ሥር ቀርቧል፡፡ አስኳላ እና አስኳል በሚለው ክፍል የተወሰዱ ገጾች እነሆ

.

"ዘመናዊው ትምህርት ከነባሩ ተፋትቶ መጀመሩ ሶስት ችግሮችን አመጣ። በትምህርትና በዕውቀት ዘርፍ ከዚያ በፊት የተሰራውን ሁሉ እንዳልተሠራ ቆጠረው። ከመሠረቱ የተነቀለ፤ ሀገሩን የማያውቅ ትውልድ ተፈጠረ። በአውሮፓ ነባራዊ ሁኔታ የተቃኘ፤ ለአውሮፓውያን የተቀረፀን ዕውቀት የሚያነበንብ ትውልድ ተፈጠረ። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ በመሆኑ፤ የኢትዮጵያን ችግር በአውሮፓ መነጽር በመመልከት፤ ለብዙ ችግሮች መፈጠር ምክንያት ሆኗል"
(ዐብይ አህመድ :- የመደመር ትውልድ 2015 ገጽ 227)
1.7K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 18:41:41
በዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ለሴቶች፣ ልዩ ፍላጎት ላላቸውና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ ነው፡፡
……………………………………………

መጋቢት 28/2015ዓም.(የትምህርት ሚኒስቴር) ፡ትምህርት ሚኒስቴር ለሴቶች፣ ልዩ ፍላጎት ላላቸውና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ወቅት ምቹ ሁኔታ መፍጠር በሚቻልበት ሂደት ላይ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከተውጣጡ የዘርፉ ኃላፊዎች ጋር ምክክር አካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ የትምህርት ሚኒስቴር የሴቶች ማህበራዊ ጉዳይና አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ የትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ያለውን የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን እየሰራ እንዳለ ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ አንደኛው የመውጫ ፈተና ነው ብለዋል፡፡

በመውጫ ፈተናው ከስርዓተ ፆታ አንፃር እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውና ልዩ ድጋፍ የሚፈልጉ ተመራቂ ተማሪዎችን እኩል እንዲሳተፉ ምቹ የፈተና አካባቢ በመፍጠር ውጤታማ እንዲሆኑ ማድረግ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚጠበቅም ገልፀዋል።

በዝግጅት ምዕራፍ፣ ከመፈተኛ ቦታዎች፣ ከመፈተኛ ቁሳቁሶች እንዲሁም በፈተና ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ የሰርዓተ ፆታ ጉዳዮች ለይቶ ከወዲሁ መፍታት እንደሚገባም ተገልጿል።

ሙሉ መረጃውን

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et

ይከታተሉ
---------
1.4K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 09:56:18
ያለፈው የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ጠንክረን እንድንሰራ አድርጎናል ሲሉ የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ገለጹ፡፡
---------------------------------------------
መጋቢት 22/2015 ዓም .(የትምህርት ሚኒስቴር) የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ጠንክረን እንድንሰራ አድርጎናል ሲሉ የጣና ሀይቅ አጠ/ከፍ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ተናገሩ።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሰጥበት አዲሱ የፈተና ስርዓት ተማሪው በሰራው ልክ የሚመዘንበት በመሆኑ ጠንክረን እንድንሰራ አድርጎናልም ብለዋል።

የጣና ሀይቅ አጠ/ከፍ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት ም/ር/መምህር አቶ ጸጋዬ ተፈራ ከዚህ ቀደም የነበረው የፈተና ስርዓት ለኩረጃ የተጋለጠ እና ተማሪዎች በቂ ዝግጅት የማያደርጉበት እንደነበረ ገልፀዋል።

አሁን ላይ ተማሪው በሰራው ልክ የሰራውን የሚያገኝበት የፈተና ስርዓት በመዘርጋቱ ለተማሪዎችም ይሁኑ ለመምህራን ጠንክረን እንድንሰራ አድርጎናል ሲሉም ተናግረዋል።
ሙሉ ዜናውን

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et

ይከታተሉ
---------
1.4K views06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 18:07:59
ጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ የቲውተር ማህበራዊ ድረ ገጹ በቲውተር ድርጅት የእውቅና ማረጋገጫ/blue badge /አግኝቷል።

የጅግጅጋን ዩኒቨርስቲ ትክክለኛ መረጃዎች ከተረጋገጠው/Verified/ የዩኒቨርስቲው ቲውተር አካውንት

https://twitter.com/jigjigauniveth

እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል ።
1.7K views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 16:48:07
የትምህርት ሚኒስቴር ለ15 ጆርናሎች ለ3 ዓመታት የሚቆይ የእውቅና ፈቃድ ሰጠ
------------------- / ----------
የትምህርት ሚኒስቴር ለአገር ውስጥ የምርምር ጆርናሎች እውቅና ሲሰጥ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ለ2014 ዓ.ም እውቅና ለማግኘት ያመለከቱ ፈቃድ ጠያቂዎች በተከለሰው መመሪያ ቁጥር 01/2012 መሰረት አሟልተው የተገኙና እውቅና የተሰጣቸው ጆርናሎች የሚከተሉት ናቸው።
1. Daagu International Journal of Basic and Applied Research

2. East African Journal of Veterinary and Animal Sciences

3. Ethiopian Journal of Behavioral Studies

4. Ethiopian Journal of Environment and Development
5. Ethiopian Journal of Health and Biomedical Science
6. Ethiopian Journal of Human Rights
7. Ethiopian Journal of Social Sciences
8. Ethiopian Journal of Water Science and Technology
9. Gadaa Journal
10. International Journal of Ethiopian Legal Studies
11. Journal of Agriculture and Environmental Sciences
12. Journal of Equity in Science and Sustainable Development
13. Journal of Science and Sustainable Development
14. Zena-Lisan Journal of Ethiopian Languages and Culture
15. Pest Management Journal of Ethiopia
642 views13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ