Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Today

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio2today — Ethio Today E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio2today — Ethio Today
የሰርጥ አድራሻ: @ethio2today
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.44K
የሰርጥ መግለጫ

ፈጣን አዳዲስ እና የተረጋገጠ መረጃ በእየለቱ ያግኙ።
YouTube :- https://www.youtube.com/channel/UCM0oGovoseqStaFWh2wIi4g

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 10:37:32
እኛ እንደ ወያኔ ጸረ-ህዝብና የወንበዴ ስብስብ አይደለንም። የተከበረ ሀገርና ፣ የተከበረ ህዝብ ጠባቂዎች ነን። ሲጮሁ አንጮህም ሲዘሉም አንዘልም በስሜት ሳይሆን በጥበብ ነው የምንመራው፣ ስሜት አይገዛንም እኛን የሚገዛን የሀገር ፍቅር ና ወታደራዊ ሙያችን ብቻ ነው

ጄነራል አበባው ታደሰ
97 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 10:34:58
ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም

"ምሽግ መቆፈሩን አልረሡትም አሳምረው ሠርተውታል። የዘነጉት ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን የተከፈተብንን ጦርነት መቀልበስ መቻሉን ነው።"

፦ በግዳጅ ቀጠናው የሚገኙ የክፍለ ጦር አዛዥ
100 views07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 07:57:07
በደባርቅ ከተማ 16 ሰርጎ ገቦች ተያዙ።

የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር በምሽት የኬላ ጥበቃ 16 የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት የኾኑ ሰርጎ ገቦችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እኩይ ዓላማ ለማስፈፀም በተለያየ ምክንያት ወደ ከተማዋ ገብተው እየተንቀሳቀሱ የመረጃ ማቀበል ሥራ የሚሠሩ 16 ተጠርጣሪ ሰርጎ ገቦች እና ሶስት ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደባርቅ ከተማ ከንቲባ ብርሃን ፀጋየ ገልፀዋል።

የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ዳግም ወረራ ለመከላከል በሚደረግ ዘመቻ የመጀመሪያው ተግባር የከተማችን ከሰርጎ_ገብ መጠበቅ እና የደጀንነት ሚና መወጣት ዋነኛና ቁልፍ ተግባር መሆኑ ታውቆ በአደረጃጀት ስምሪት ተሰጥቶ ወደ እየተሠራ መኾኑን ከንቲባው ተናግረዋል።

ደባርቅ ከተማ ውስጥ በጠንካራ የመረጃ መዋቅር፣ የኬላ ጥበቃ እና በሌሎች ስምሪቶች የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድን ተላላኪ ሰርጎ ገብ ዓላማውን እንዳያሳካ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ የከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

የደባርቅ ከተማ ባለገጀራ ወጣቶች ፣ የሰሜን ጎንደር ጥቁር አንበሳ የቀድሞ ሰራዊት የበጎ አድራጎትና ልማት ማህበር አባላት ፣ አጠቃላይ የፀጥታ መዋቅሩ ፣ ወጣቶችና ማኅበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም እያስጠበቀና የደጀንነት ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።
239 views04:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 22:59:57
በአበርገሌ ምሽግ የተደመሰሱ የወራሪው ህወሓት ወታደሮች /ህፃናት
305 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 22:54:29
ሸዋሮቢት
በሰሜን ሸዋ ዞን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ውብሸት አያሌው  አሁን ከመሸ 3:00 ሰዓት አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቀ የታጠቁ ሀይሎች ጥቃት ተፈፅሞበት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። የተኩስ ድምፅ እንደለም ነግረውኛል።
305 views19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 22:53:36
የህወሃት ታጣቂዎች በዋግህምራ አበርገሌ ግንባር በልታርፍ/የበረሃዋ ገነት/ በሚባል አካባቢ በካምፓቸው ውስጥ ጥለውት የሸሹት ነው።
296 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 22:51:52
የፖሊስ መልዕክት !

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ፦

" ምንም በማያውቁት ጉዳይ በህጻናቱ ላይ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ወንጀል ሁሉንም በእጅጉ አሳዝኗል።

ወላጆች የሚቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችን ማንነት ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል።

እንደ ቤተሰብ ሆነው የሚኖሩ የቤት ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ወንጀል የሚፈጽሙም ስላሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። "

#ተጨማሪ_መረጃ ፦

• በአንድ ቀን በአሰቃቂ ሁኔታ ሁለት ታዳጊ ልጆቻቸውን ያጡት ወላጆች በከባድ ሐዘን ውስጥ ይገኛሉ።

• ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም በእጅጉ ተረብሸው ነው የሚገኙት።

• ፖሊስ በወንጀሉ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ነው።

- ተጠርጣሪዋ ህጻናቱን አንቃ እና ስለት ተጠቅማ በአስቃቂ ሁኔታ መግድሏ የሚያመላክቱ መላምቶች አሉ።

- ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ወይም የአእምሮ ጤና ችግር እንዳለባት ለማወቅ ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው።

- በወንጀሉ የተጠርጠረችው ግለሰብ በቤት ሠራተኛነት ግድያው ለተፈጸመበት ቤተሰብ ስታገለግል ቆይታለች።

• ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው ወላጆች የሌሉበትን ሰዓት ጠብቃ ነው።

መረጃው ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የአማርኛ አገልግሎት ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነው።

#AddisAbabaPolice
308 views19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 16:00:56 ሌላ ሰበር

ከተመታችው አንቶኖቭ አውሮፕላን ውስጥ ከነበሩ አመራሮች መካከል ሱዳን ላይ ሆኖ ቡድኑን ከግብጽ ሲያስተሳሰር የቆየው ጀ/ል ፍሰሃ ተክሌ(ማንጁስ)፣ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስቴር ስዬ አብረሃ፣ የትግራይ ክልል ሰላምና ደህንነት ምክትል ቢሮ ሀላፊ የነበረው ቴኪኡ ምትኩ እና የምእራብ ትግራይ ዞን አስተዳዳሪ የነበረው ሪስቁ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው ወደ ትግራይ የበረሩ ቢሆንም በዛው ደብዛቸው መጥፋቱን የሚገልጹ መረጃዎች ተገኝተዋል።
Brook Abegaz
467 views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:35:14
#Breaking_News

የአውሮፓ ህብረት ከሩሲያ ጋር የነበረውን “የቪዛ ማመቻቸት ስምምነት” ሙሉ በሙሉ ለማቆም ወሰነ!!

ውሳኔው የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ በህብረቱና እና በሩሲያ መካከል የነበረው “የቪዛ ማመቻቸት ስምምነት” ለማቆም ሚያስችላቸውን እርምጃ ለመውሰድ ላለፉት ሁለት ቀናት በቼክ ሪፐብሊክ ከመከሩ በኋላ የተደረሰ ስምምነት ነው ተብሏል፡፡

ሚኒስተሮቹ በውይይታቸው ከሩሲያ ወደ አጎራባች ግዛቶች የሚደረጉ የድንበር ማቋረጦች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ትኩረት ሰጥተው የተመለከቱት አንኳር ነጥብ እንደነበር የአውሮፓ ህብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል አስታውቋል፡፡ሚኒስትሮቹ የድንበር ማቋረቱ ሁኔታ በአውሮፓ ከፍተኛ የሆነ ደህንነት ስጋት መደቀኑን በተመለከተ መወያየታቸውም ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት የአውሮፓ ህብረት ከሩሲያ ጋር የነበረውን “የቪዛ ማመቻቸት ስምምነት” ሙሉ በሙሉ ለማቆም መወሰኑ ጆሴፕ ቦሬል ከደቂቃዎች በፊት በትዊተር ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ ይፋ አድርገዋል፡፡

ውድ የቻናላችን ተከታዮች #Ethio_Today Facebook page ላይ መረጃዎችን ማጋራት ስላልቻልን ቴሌግራም ቻናላችንን #ሼር በማድረግ ተባበሩን

#Share

https://t.me/ethio2today
308 viewsedited  20:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:46:45 የቆቦ  ዳግማዊ   ጭፍጨፋ

ከጦርነት ውጪ መኖር የማይችለው አሸባሪው ህወሓት የቆቦ ከተማንና አካባቢውን በሕዝብ ማዕበል ከወረረ በኋላ  ቤት ለቤት አሰሳ ያደረገ ሲሆን፤ አዛውንቶችን ‹‹እናንትን አንነካም፤ ከእናንተ  ጋር ምንም  ጉዳይ  የለንም›› በማለት    ወጣት ልጆቻቸውን ግን  ፋኖ ፣ብልጽግና  የአካባቢ ሚሊሺያ ናቹህ በማለት   እያደነ  መግደሉንና  እስካሁን  ድረስም አስከሬን  በየቦታው አለመነሳቱን  የአይን እማኞች  ገልጸዋል።

በዘር ጭፍጨፋ  የተካነው  ህወሓት  ከአሥር ወራት  በፊት   ቆቦንና አከባቢዋን  በተቆጣጠረበት  ወቅት  ጳጉሜ 4 እና 5 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ 600 መቶ የሚደርሱ ንጽሃን ዜጎችን   በግፍ   መግደሉን የኢትዮጵያ  ሰብዓዊ  መብት ኮሚሽን  ያቀረበው ሪፖርትና ሌሎች ዓለም አቀፍ  መገናኛ ብዙኃን ጭምር  በሳተላይት የተደገፈ ምስል  በማውጣት  ጭምር  ዘገባ አውጥተው እንደነበር ይታወሳል።
በስሕተት ላይ ስሕተትን በመፈጸም የሚታወቁት የአሸባሪው ቡድን ታጣቂዎቹ  በጥላቻና ቂም በቀል በመነሣት በቆቦ አካባቢ ዳግመኛ   የዘር  ጭፍጨፋ  በመፈጸም  ዘመን የማይሽረው ጠባሳ ለትውልድ እያኖሩ ይገኛሉ።
 
375 views18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ