Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች H
የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.64K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-04-20 07:41:47
በኮሪደር ልማት እየተሰራ የሚገኘው የአራት ኪሎ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ
16.2K views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 22:03:36
ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያሏት የሚሊየነሮች ቁጥር በአጠቃላይ 2,700 መድረሱን በዘርፉ ላይ የተደረገ አንድ ሪፖርት አመላከተ

ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ ወደ 2,700 የሚጠጉ ሚሊየነሮች እንዳሏት የገለፀዉ ይህ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ሀገሪቷ በዚህ የስነ ህዝብ እድገት ዉስጥ ጠንካራ እንድገት እንደሚኖረዉ ትንበያውን አስቀምጧል።

በ 2024 የወጣዉ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ዘጠኛ እትሙ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳዲስ ገበያዎችን የሚይዘው የአህጉሪቱ ሚሊየነር ህዝቧ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ዉስጥ በ 65% ከፍ ሊል እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል ።

አሁን ላይ በአፍሪካ ያለዉ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ሀብት 2.5 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱ የተነገረ ሲሆን ኢትዮጵያ በዚህ ኢኮኖሚ እድገት ዉስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጓ ነዉ ይህ ሀተታ የሚያመላክተዉ።

capital
14.8K views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 22:12:29 #ለመረጃ

የመጋቢት ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 26.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አሳወቀ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ፦

ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 29 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።

ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 22 በመቶ በመሆን ተመዝግቧል።

በአጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ #በየካቲት_ወር ከነበረበት 28.2 በመቶ ወደ 26.2 በመቶ በመሆን መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመላክቷል።
18.6K views19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 08:40:32
Good Morning
20.4K views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 11:29:16
17.6K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 16:45:36
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የአገሪቱን የንግድ ባንኮች ባላቸውን ካፒታልና አሴት መሰረት በሶስት የተለያዩ ምድቦች መክፈሉ ተገለፀ።
እንደ መረጃ መንጮች የአገሪቱ ባንኮች ከፍተኛ ምድብ፣ መካከለኛ ምድብ እና ዝቅተኛ ምድብ በማለት ተከፍለዋል ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአገሪቱ ጠቅላላ ባንኮች 49.5 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 48.7 በመቶ የተቀማጭ ገንዘብ በመያዝ ከፍተኛ ምድብ ላይ መቀመጥ እንዲችል የተደረገ ሲሆን ሌሎች አምስት ባንኮች በድምር ከአገሪቱ ጠቅላላ ባንኮች 28 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 29.4 በመቶ የተቀማጭ ገንዘብ በመሰብሰብ መካከለኛ ምድብ ተቀምጠዋል።
በዚህ ደረጃ የተመደቡ ባንኮች አቢሲኒያ ባንክ ፣ ዳሽን ባንክ፣ሕብረት ባንክ ፣ አዋሽ ባንክ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ሲሆኑ የካፒታል መጠናቸው በድምር ባለፈው ሰኔ 2023 በጀት መዝጊያ ላይ 31 በመቶ መሆኑ ተገልጿል ።

በዝቅተኛ ምድብ የተቀመጡት 24 ባንኮች ሲሆኑ 22.5 በመቶ የሃብት መጠን እንዲሁም 21.9 በመቶ ተቀማጭ ገንዘብ አላቸው የካፒታል መጠናቸው ከጠቅላላው የአገሪቱ ባንኮች 41.6 በመቶ መሆኑ ተገልጿል ።
13.2K views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 15:57:59
ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከዚህ ቀደም በ70/30 በማህበር ለመደራጀት ተመዝግባችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረ የ20/80 እና 40/60 ተመዝጋቢዎች  ከሚያዝያ 8/2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 የስራ ቀናት ውስጥ አዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ  6ኛ ፎቅ የጋራ መኖሪያ እና ህብረት ስራ ማህበር ዳይሬክቶሬት ዘውትር በስራ ሰአት በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ ፡- ቀደም ሲል 70 ፐርሰንት በባንክ አካውንት ገንዘብ አስገብታችሁ ከሆነ የባንክ እስቴትመንት ይዛችሁ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡ 70 ፐርሰንቱን ገቢ ያላደረጉ ከሆነ ለተመዘገቡበት የቤት አይነት ከሚያዝያ 8/2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 የስራ ቀናት ውስጥ ገንዘቡን በቀድሞ የ40/60 ወይም የ20/80 ቤት ቁጠባ አካውንት ላይ ገቢ በማድረግ  እና እስቴትመንት ይዛችሁ በመቅረብ ብቁ መሆኑን በአካል ቀርበው ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
14.7K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 15:55:25
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ

ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረዉን ደንብ በመሻር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ለሚሰጣቸው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታዉቋል ።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አዲሱ ደንብ ከመዉጣቱ በፊት ሲሰራበት የነበረዉን የሰነዶች ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያን በመሻር ማሻሻያዉ ከሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለሚሰጣቸው የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያ ለመወሰን ባወጣዉ በዚህ ደንብ በተቀመጠው አዲሱ የክፍያ መጠን የሰነድ አይነቶቹ ቢለያይም ለሁሉም አገልግሎቶች ከ 200 ብር ጀምሮ እስከ 500 ብር ድረስ ክፍያን ይጠይቃል ።

ካፒታል በተመለከተዉ በዚህ ደንብ ላይ ለሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዉል ሰነድ ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ሽያጭ ፣ ለመመስረቻ ፅሁፍ ሰነድ እና በስጦታ መልክ ለሚሰጡ ንብረቶች ዉል ሰነድ የክፍያ አገልግሎት ተመን ከወጣላቸው መካከል ዉስጥ ተካተዋል።
13.3K views12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 10:16:09
ላለፉት 23 ዓመታት የይገባኛል ክርክር የነበረበት ቤት ክርክሩ ሳይቋጭ በኮሪደር ልማት ምክንያት ፈረሰ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም ባረጋገጠው መረጃ መሰረት ይህ ቤት ይገኝ የነበረው ቦሌ ወሎ ሰፈር ወደ ቄራ መታጠፊያው መንገድ አካባቢ ላይ ነበር፡፡

ይህን ቤት ሁለት ግለሰቦች የይገባኛል ጥያቄ አንስተው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤትም ወስደውት ላለፉት 23 ዓመታትም ክርክሩ በሂደት ላይ ነበር ተብሏል፡፡

ክርክሩ እንዴት ይህን ያህል ጊዜ ሊወስድ ቻለ በሚል ኢትዮ ኤፍ ኤም ላነሳው ጥያቄ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የህግ ባለሙያ ጉዳዩ በእርግጥም ውስብስብ ችግሮች እንደነበሩበት ነግረውናል፡፡

የክስ ሂደቱ መቋጫ ሳያገኝ የተንዛዛው ይህ ክርክር አሁን ላይ በኮሪደር ልማት ምክንያት ቤቱ መፍረሱን ከህግ ባለሙያዎች ማረጋገጥ ችለናል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
17.5K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 17:41:21 አዲሱ የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን አሰራር እና ታክስ አገልግሎት ክፍያ ማንዋል ቁጥር 01/2016

በአዲስ አበባ ከተማ ለአፓርትመንት ቤቶች እና ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ወይም ኮንዶሚኒየም ቤቶች አማካኝ የሽያጭ ዋጋ ተመን በ34 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።

በተሻሻለው  የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሰረት ከኮንደሚንየም እና አፓርትመንት ውጪ ለሆኑ ግንባታዎች፦

የግንባታ ነጠላ ዋጋ በጭቃ የተሰራ ቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 15,000 ብር፣

በብሎኬት የተሰራ የቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 20,000 ብር፣

የህንጻ ወለላቸው ከG+1 እስከ G+5 25,000 ብር እና፣

G+6 እና በላይ የሆኑ ቤት ወይም ህንጻ ነጠላ ዋጋ በካሬ 30,000 ተደርጓል፡፡

የቦታው መገኛ ዋጋ ('location value') ለከተማው የቦታ ደረጃ የጸደቀው ወቅታዊ አማካይ የሊዝ ጨረታ ዋጋ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል።

የቤት ስም ንብረት ዝውውር ክፍያ ማለትም አሹራ 4 በመቶ እና የቴምብር ቀረጥ 2 በመቶ ከጠቅላላ የቤቱ ሽያጭ ዋጋ ተሰልቶ ከ ከመጋቢት17 ቀን 2016 ዓ/ም  ጀምሮ እንዲከፈልም ታዟል።

ይህ ማሻሻያ መምሪያ ከመውጣቱ በፊት የስም ንብረት ዝውውር አገልግሎት ጠይቀው በሂደት ላይ ሆኖ ክፍያ የፈጸሙ ተጋልጋዮች በቀድሞ አሰራር በከፈሉት ክፍያ መሰረት ይስተናገዳሉ ተብሏል።

ግንባታቸው ያልተጠናቀቁ ህንፃዎች የትመና ስራ የሚሰራላቸው ግንባታው በደረሰበት ወይም አሁን ላይ ባለበት ግንባታ ደረጃ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ያሳወቃል።
@SamuelGirma

              
20.3K viewsedited  14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ