Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች H
የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.64K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-03-27 12:58:06 #Update

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸውን ያለሆነ ገንዘብ በህገወጥ መንገድ ወስደው በከፊል የመለሱ ወይም ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ያላደረጉትን 5,166 ግለሰቦች ስም ዝርዝር ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ግለሰቦቹ ቀሪ የወሰዱትን ገንዘብ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ እንዲመልሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

ይህንን የማያደርጉ ከሆነ ወደ ህጋዊ እርምጃዎች እንደሚገባ ገልጿል።

ስማቸውን ከፎቷቸው ጋር በማድረግ ህገወጥ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን ለህግ አካላትና ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
16.8K viewsedited  09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-27 12:56:45
Bole
16.2K views09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-27 08:06:33
ከሚደርሱኝ ጥቆማዎች በመነሳት ማረጋገጥ የቻልኳቸው የቤት ፈረሳ መረጃዎች

- አያት ዞን አንድ ውስጥ ያሉ በርካታ 'ዘመናዊ' ሊባሉ የሚችሉ መኖርያ ቤቶች ስፍራው ለሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ግንባታ ስለሚፈለግ ተነሱ እንደተባሉ፣ ባለፈው እሁድ እለት በመንግስት አካላት ስብሰባ ተጠርተው ይህ በይፋ እንደተነገራቸው አረጋግጫለሁ። ይህ በአካባቢው ቤቶችን የማንሳት ጉዳይ ቀጣይ እንደሆነም ታውቋል።

- በቦሌ ክ/ከተማ በተለምዶ ጉርድ ሾላ ንግድ ባንክ አካባቢ አስፓልት ዳር ያሉ የግል ቤቶች ተለክተው አንዳንዱ ቤት እስከ ሳሎኑ፣ አንዳንዱ ደግሞ እስከ መኝታ ቤት ድረስ እንዲፈርስ መደረጉ ታውቋል። እስከ ሳሎን ድረስ ብቻ በልኬት የፈረሰባቸው ቀሪውን መኝታ ቤታቸውንና ኪችናቸውን ዛሬ ለመሸፈን መግቢያና መውጪያ በራቸውን ሲሰሩ በድጋሜ አፍርሰውባቸው እንደገና ፍቃድ አውጡ እንደተባሉ ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

Photo: File

Elias Meseret
17.7K views05:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-23 15:41:35
የመሬት ይዞታ ምዝገባ ጥሪ

በሸገር ከተማ፣ በኮዬ ክፍለ ከተማ ፤በወዴሳ ወረዳ ኮንዶሚኒዬም ሰፈር ባለይዞታዎች በሙሉ

በክፍለ ከተማው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ በተራቸዉ መሰረት
B451, 452 ,453 ከ16-18/07/2016

B454, 455,456 ከ19-21/07/2016

B457, 458,459 ከ24-25/07/2016

B460, 461 ከ26-27/07/2016


በዚህ መሰረት በወዴሳ ሰፈር ዉስጥ የሚትገኙት የመሬት ባለይዞታዎች ምዝገባዉ እስከ 15/06/2016 ዓ.ም ስለሆነ ሰነዳችዉን በመያዝ ለዚህዉ ለግዛያዊ በተቋቋመዉ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ጣቢያ ወይም ኮዬ ፈጬ ክ.ከተማ ወዴሳ ወረዳ ካደስተር ፅ/ቤት የማረጋገጥ ቡድን 4th FLOOR ቀርባቸዉ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

ዋነዉና 2ኮፒ ሆኖ መቅረብ ያለባችዉ ሰነዶች፤

1. ካርታ
2. ቅድመ ክፍያ ደረሰኝ
3. የታደሰ መታወቂያ
4. የቁልፍ መረካከቢያ
5. የቤት ውል
6. የባንክ ዉል
7. የእግድ ደብዳቤና ዉል
8. የዉክልና (ወደ አፋን ኦሮሞ የተተረጎመ)
9. የጋብቻ ሰሪትፊኬት እና ሌሎች

አድራሻ፡ ኮዬ ፈጬ ክ/ከተማ ወዴሳ ወረዳ 4th FLOOR ካደስተር ፅ/ቤት
15.7K viewsedited  12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 00:29:33 መንግሥት የመኖሪያ ቤቶችን እየገነባ የቤት ባለቤት ማድረግ አይችልም ተባለ!
Via #ethiopian_reporter
መንግስት ኮንዶሚኒየም መሥራት አቆመ!
**
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለውን የመኖሪያ ቤቶች ችግር ለማቃለል አስተዳደሩ በአማራጭነት ባቀረባቸው የተለያዩ አማራጮች በመጠቀም የመኖሪያ ቤቶችን መገንባት እንደሚቻልና ኅብረተሰቡም በዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አስተላለፉ፡፡

ከንቲባዋ ይህንን የገለጹት ሰሞኑን ሰንሻይን ኮንስትራክሽን የገነባቸውን አምስት ሺሕ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ባስተላለፈበት ፕሮግራም ላይ ነው፡፡ እንደ ወ/ሮ አዳነች አበቤ ገለጻ፣ መንግሥት የመኖሪያ ቤቶችን እየገነባ የቤት ባለቤት ማድረግ የማይችል በመሆኑ አስተዳደሩ አዲስ በቀረጻቸው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮግራም ላይ ተሳታፊ መሆን የሚቻልበት ዕድል ማመቻቸቱን አመልክተዋል፡፡ በከተማዋ ነዋሪዎች በዋነኛነት የሚነሳው የመኖሪያ ቤት ችግር መሆኑን ያመለከቱት ከንቲባዋ አስተዳደሩም ይህንን ጉዳይ ከሁሉም በላይ በአንገብጋቢነት እንደሚመለከተው ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የቤት ችግርን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የተለያዩ የአማራጮች እየተተገበሩ መሆኑን በማስታወስ የከተማው ነዋሪም እነዚህን አማራጮች መጠቀም እንደሚችል አስረድተዋል፡፡

እንደ ከንቲባዋ ገለጻ የተቀየሱት አማራጮችን በመጠቀም የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመፍታት በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ ቢሆንም አሁንም የመኖሪያ ቤት አቅርባትና ፍላጎቱ ግን ሊጣጣም አልቻለም፡፡ በመሆኑም ይህንን ለማጣጣምና የመኖሪያ ቤት አቅርቦቱን ለመጨመር በርካታ የቤት አቅርቦት ፕሮግራሞች በመቅረጽና አስፈላጊው የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ ወጥቶለት አብሮ የማልማት እንቅሰቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት የከተማ አስተዳደሩ አቅም ላላቸው የከተማው ነዋሪዎች፣ ለባለሀብቶች፣ ለግል አልሚዎችና ሌሎችም በዚህ ሥራ መሳተፍ የሚችሉትን ሁሉ በማበረታታት ላይ የሚገኙ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

በእነዚህ የቤት ግንባታ አማራጮች ለመሳተፍ የሚፈልጉ በሩ ክፍት ስለመሆኑ በመግለጽም አስተዳደሩ በአማራጭነት ባቀረባቸው የቤት ግንባታ አሠራሮች ኅብረተሰቡ ተሳታፊ ይሆን ዘንድም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አስተዳደሩ በአማራጭነት ካቀረባቸው የቤት ማልሚያ ፕሮግራም ውስጥ አንዱ በፓርትነርሺፕ ወይም በአጋርነት አብሮ መሥራት በቀዳሚነት ጠቅሰዋል፡፡ ሁለተኛ በሪልስቴት መሬት ሳይሸጥ ዓላማው ሳይቀር በዕለቱ አምስት ሺሕ ቤቶችን እንዳስተላለፈው ሰንሻይን ኮንስትራክሽን የተሰጠውን መሬት አልምቶ ለተፈለገው ዓላማ ማዋል መቻል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተረከቡት መሬት ዓላማው ሳይቀር ለተፈለገው ዓላማ መዋል የሚችል ከሆነ አስተዳደሩ የሚያበረታታ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል፡፡ ኅብረተሰቡ በአማራጭነት ሊጠቀምበት ይችላል ብለው ሦስተኛ አማራጭ ብለው የገለጹት በማኅበር ተደራጅቶ ቤት መሥራትን ነው፡፡ አራተኛው አማራጭ ደግሞ ከሦስቱ አማራጮች ለየት ባለ መንገድ የሚተገበር ነው፡፡ ይህም ቤት የሚፈልጉ መሬት ያላቸው ገንዘብ ግን የሌላቸው ነዋሪዎች ገንዘብ ካለው አልሚ ጋር በአጋርነት አብረው ማልማት የሚችሉበት ዕድል የተመቻቸ መሆኑ ነው፡፡ አምስተኛ አማራጭ ደግሞ መንግሥት ራሱ እንዲገነባ የሚያቀርበው እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ እነዚህ አማራጮች የከተማዋን ዲዛይን በጠበቀ መልኩ የሚገነቡ እስከሆነ ድረስ አስተዳደሩ ድጋፍ የሚያደርግባቸው አዳዲስ አሠራር ስለመሆናቸው ከገለጻቸው ለመረዳት ተችሏል፡፡

‹‹በየትም አገር የቤት አቅርባት እየጨመረ እንዲሄድ ይደረጋል እንጂ መንግሥት እየገነባ ሁሉንም ነዋሪ የቤት ባለቤት ማድረግ አይችልም፣ በየትኛውም ዓለም አልተደረገም፤›› ያሉት ከንቲባዋ ነገር ግን አዲስ አበባ የቤት አቅርባትን የሚያስችሉ አቅሞቻችንን ማቀናጀት በጋራ ማልማት የሚቻል ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡

አሁንም አስተዳዳሩ ይህንን ሥራ ለማጠናከር እየሠራ ሲሆን በዕለቱ የሰንሻይን ኮንስትራክሽን አምስት ሺሕ ቤቶች ሠርቶ በማስረከቡ በከተማችን በዚህን ያህል ቁጥር የቤት አቅርቦት መጨመር ያስቻለ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ሰንሻይን ይህንን ያህል ገንብቶ ቤቶቹን ማስተላለፍ የቻለው መሬቱ ስላልተለወጠ ለተፈለው ዓላማ ስለዋለ መሆኑና ይህም 3.8 ሔክታር መሬት በነፃ አስተዳደሩ የቀረበ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ እንዲህ በትብብር ከተሠራ ውጤታማ መሆን ይቻላልም ማለትም አሁንም ወደፊትትም ቤት ለማልማት አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸው በትክክል ማቅረብና መተግበር ለሚችሉ አስተዳደሩ በነፃ መሬት ባያቀርብም በበርካታ ማበረታቻዎችን የሚሰጡና የሚደግፉ መሆናቸውም አስታውቀዋል፡፡ ከንቲባዋ እነዚህ አማራጮች ሌላ ኩባንያዎች ለሠራተኞቻቸው ቤት መገንባት የሚችሉ ከሆነ ይህንን ለማበረታታት ቦታ የሚያቀርቡ እንደሆነም በሰሞኑ ንግግራቸው አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሠራተኞቹ አምስት ሺሕ ቤቶችን ለማስገንባት የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ፕሮግራም ላይ የተገኙት ወ/ሮ አዳነች ኩባንያዎች ለሠራተኞች ቤት መገንባት የሚፈልጉ ከሆነ ይበረታታሉ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የወሰደውን ዕርምጃ በምሳሌነት በመጥቀስ በከተማ ውስጥ በርካታ ትልልቅ ኩባንያዎች ስላሉ ለሠራተኞቻቸው ቤት በመገንባት የቤት አቅርባትን ችግር ለማቃለል ለሚያደርጉት ጥረት አስተዳደሩ መሬት የሚያቀርብ በመሆኑ ኩባንያዎች ይህንንም የቤት ማልሚያ መንገድ በመጠቀም መገንባት እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

አስተዳደሩ በአማራጭነት ካቀረባቸው አሠራሮች ውስጥ በተለይ ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ ለማልማት በተቀረጸው ፕሮግራም 70 የሚሆኑ አልሚዎች ከአስተዳደሩ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ያደረጉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በዝግጅት ላይ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንዲህ ላሉ የቤት ልማቶች አስተዳደሩ 1,500 ሔክታር መሬት መዘጋጀቱም መገለጹ ይታወሳል፡፡

አስተዳደሩ ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የተመዘገቡ ቤት ፈላጊዎች ቁጥር ከ600 ሺሕ በላይ ደርሰዋል፡፡ ባለፉት 20 ዓመታት ደግሞ በመንግሥት የተገነቡ ቤቶች 316 ሺሕ ሲሆኑ በዚህ የግንባታ ሒደት የቤት ፍላጎትን መሙላት እንደማይችልም በመታሰቡ አስተዳደሩ በአማራጭነት በቀረቡ የቤት ማልሚያ ፕሮግራሞች እየተሳተፉ ያሉ አልሚዎች የቤት ችግርን ለማቃለል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ተብሎም ታምኖበታል፡፡

ከዚሁ አንፃር በከተማዋ እየተካሄደ ያለውን የቤቶች ልማት በተመለከተ በ2016 በሙሉ በጀት ዓመቱ ግንባታቸውን ለማስጀመር ከታቀዱት 120 ሺሕ ቤቶች በግማሽ ዓመቱ ውስጥ 99113 ቤቶች ማልማት መቻሉን ከንቲባዋ በቅርቡ የስድስት ወር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት መጥቀሳቸው ይታወሳል፡፡

ከዚህም ሌላ በበጀት ዓመቱ 111 ሺሕ ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል የአጋርነት ውልና የመሬት ዝግጅት እየተከናወኑ ስለመሆናቸውም ጠቅሰዋል፡፡ እንዲህ ባሉ በአጋርነት ቤት በማልማት ሥራዎች በሪል ስቴት ኩባንያዎችና በግለሰብ አልሚዎች በግማሽ ዓመቱ ውስጥ አሥር ሺሕ ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በግለሰብና በሪል ስቴት ኩባንያዎች ከተገነቡት አሥር ሺሕ ቤቶች ሌላ በመንግሥት በጀት 4,200 በበጎ አድራጊ ግለሰቦችና ኩባንያዎች በኩል ደግሞ 5023 ቤቶች በአጠቃላይ 19,223 ቤቶች ስለመገንባታቸውም ጠቅሰዋል፡፡
#ሪልስቴት #ኮንዶሚኒየም #ኢትዮጵያ
17.1K views21:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 00:29:30
መንግሥት የመኖሪያ ቤቶችን እየገነባ የቤት ባለቤት ማድረግ አይችልም ተባለ!

መንግስት ኮንዶሚኒየም መሥራት አቆመ!

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለውን የመኖሪያ ቤቶች ችግር ለማቃለል አስተዳደሩ በአማራጭነት ባቀረባቸው የተለያዩ አማራጮች በመጠቀም የመኖሪያ ቤቶችን መገንባት እንደሚቻልና ኅብረተሰቡም በዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አስተላለፉ፡፡
16.2K viewsedited  21:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 00:24:26
ለመምህራን በእጣ የተላለፉ ቤቶችን የተመለከተ ማስታወቂያ

ለመምህራን የተላለፉ 435 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውል የመፈፀም ሂደት ነገ በ12/08/16 ዓ.ም  ይጀመራል

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ እና ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ6/07/2016 ዓ.ም በተለያየ ምክንያት ሳይተላለፋ የቀሩ 435 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ለመምህራን በእጣ መተላለፋቸው ይታወሳል።

በመሆኑም የቤት እድለኛ የሆናችሁ መምህራን ከሀሙስ ማለትም ከ12/08/16 ዓ.ም ጀምራችሁ  በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ውል መፈፀም የሚያስችል ሂደት እንድትጀምሩ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ይገልፃል።

ተዋዋዮችም በአለቱ  የታደሰ መታወቂያ ፣ በተጨማሪም መምህር/ት መሆናችሁን የሚያሳይ ማስረጃ የት/ቤት መታወቂያና  ከትምህርት ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ ይዛችሁ  መገኘት አለባችሁ በማለት ኮርፖሬሽኑ እያሳሰበ በዉክልና ለመስተናገድ የምትመጡ አካላት  በቂ ማስረጃ መያዛችሁን አትዘንጉ።

ማሳሰቢያ

- በ60 ቀናት ዉስጥ ቀርቦ ዉል ያልፈጸመ እድሉን እንደተወ ተቆጥሮ ተጠባባቂዎች በቅድመ ተከተል እንደሚስተናገዱ እናሳስባለን!

- ተዋዋዮች ለመዋዋል ስትመጡ ከታች የተቀመጠውን መስፈርት ታሳቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን!

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
15.6K views21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-19 23:09:45
እስቲ ስም አውጡለት
19.9K viewsedited  20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-19 14:42:45
መካኒሳ ፒስ ህንፃ
13.8K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-19 12:49:53 “ሕዝቡ የፓርክ ሳር እና አበቦች የሚያገኙትን ያህል ውሃ እንኳን እያገኘ አይደለም”- የአዲስ አበባ ነዋሪዎች

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ የከተማዋ ነዋሪች ለአዲስ ማለዳ ቅሬታቸውን ተናግረዋል። 

“መንግስት መጀመሪያ የሕዝቡን የውሃ አቅርቦት ችግር ሳይፈታ የመንገድ ላይ እና የፓርኮችን አትክልቶች በቀን ሶስት ጊዜ ሲያጠጡ መዋል አግባብነት የሌለው ነው” ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች ተመሳሳይ የሆነ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ እና ችግሩን ለማስተካከል እየተሰራ ያለ የሚታይ ጥረት አለመኖሩን አዲስ ማለዳ ካነጋገረቻቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተረድታለች። 

በጉለሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 4፣5 እና 7 አካባቢዎች ከፍተኛ የውሃ ችግር እንዳለ እና በሳምንት አንድ ጊዜ የሚመጣው ውሃ በበቂ ሁኔታ ሳይዳረስ እና የሚመጣበትም ሰአት ለሊት በመሆኑ ለመቅዳት አስቸጋሪ በመሆኑ ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የነዋሪዎቹን ቅሬታ በመያዝ አዲስ ማለዳ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣንን ለማነጋገር ባደረገችው ጥረት ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ነገር ግን በተለያዩ አካባቢዎች ውሃ በሳምንት አንድ ቀን እንደሚመጣና ኃይል የሌለው በመሆኑ አንድ ጀሪካን ለመሙላት ከ30 እስከ 40 ደቂቃ ይፈጃል ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ። 

“እሱን ሌሊት ስንቀዳ አድረን ጠዋት ተነስተን ስራ መግባት አልቻልንም። ከሳምንት ሳምንት መድረስም ከብዶናል” ሲሉም ጠቁመዋል። 

በተወሰኑ አካባቢዎች ደግሞ የአካባቢው ሰው ገንዘብ በማዋጣት የታንከር ውሃ በመኪና እያስመጡ እየተጠቀሙ እንደሆነ እና ለተጨማሪ ወጪ መዳረጋቸውን እንዲሁም በመኪናው ለሚመጣው ውሃ የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች በእጅጉ እየተጎዱ መሆኑን ቅሬታቸውን አመላክተዋል። 

እንዲሁም በልደታ ክፍለ ከተማ ልደታ መናፈሻ አካባቢ “ውሃ ከጠፋ አንድ ወር ሆኖታል” የሚሉት ነዋሪዎች የመጠጥ ውሃ እየገዙ እንደሚጠቀሙ፤ ነገር ግን ልብስም ሆነ እቃዎችን ለማጽዳት እየተቸገሩ መሆኑን ለአዲስ ማላዳ ተናግረዋል። 

በተመሳሳይ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ቤተል ሮም ሰፈር ባጃጅ መጨረሻ “ንጹህ ውሃ ካየን አመት አለፈን በሳምንት ሁለት ቀን የሚለቀቅልን በጣም የቆሸሸ እና የተበከለ ነው። በመሆኑም ንጹህን ውሃ በሮቶ እያመጡ ይሸጣሉ ይህ ደግሞ ወንጀል ነው” ሲሉ ያሉበትን ችግር አስረድተዋል። 
15.5K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ