Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች H
የቴሌግራም ቻናል አርማ housinginaddisababa — Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች
የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.64K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-04-09 17:41:11
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደርን በተመለከተ
17.3K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 17:00:19
በእግረኞች የሚፈጸሙ የትራፊክ ደንብ ጥሰቶች እና የቅጣት መጠን

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከመጋቢት 13 ቀን 2016 ጀምሮ እግረኞችን ለመቆጣጠና አደጋ ለመቀነስ ደንብ ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል።

እስካሁን ባለው ሂደት ባለፉት 15 ቀናት ከ700 በላይ እግረኞች በዚህ ደንብ መሰረት መቀጣታቸውን አዲስ ማለዳ ሰምታለች።

አዲስ ማለዳ ከባለስልጣኑ ባገኘችው መረጃ በመንገድ ትራስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 መሰረት የጥፋት ዓይነት እና የቅጣት መጠን የሚከተሉት ናቸው

ተገቢውን ጥንቃቄ ሳያደርግ መንገድ ማቋረጥ - 40 ብር
ለተሽከርካሪ በተፈቀደ መንገድ ላይ ያለበቂ ምክንያት የተጓዘ ወይም የቆመ - 40 ብር
እግረኛ መንገድ በሌለበት ቀኝ ጠርዝ ይዞ መጓዝ - 40 ብር
ከእግረኛ መንገድ ውጭ መጓዝ - 40 ብር
የእግረኛ መንገድ ላይ ንግድ ማካሄድ፣ ቁሳቁስ ማስቀመጥና ለእግረኞች ጉዞ እንቅፋት መሆን - 80 ብር
በብረትም ሆነ በግንብ የተለየ መንገድ ዘሎ ማቋረጥ - 80 ብር
በጆሮ ማዳመጫ እያዳመጡ መንገድ ማቋረጥ - 80 ብር
ለእግረኝ ክልክል በሆነ መንገድ፣ በማሳለጫ እና ቀለበት መንገድ ማቋረጥ - 80 ብር

እነዚህ ጥፋቶች ፈጽሞ በገንዘብ መቀጣት የማይችል አልያም የማይፈልግ ማንኛውም እግረኛ ማህበራዊ አገልግሎት ይሰጣል።
- ባለ 40 ብር ቅጣት የ30 ደቂቃ
- ባለ 80 ብር ቅጣት ደግሞ የ1 ሰዓት ማህበራዊ አገልግሎት ይሰጣሉ።

በአዲስ አበባ ከተማ በሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎች 80 በመቶ የሚሆነው የሞት አደጋ የሚከሰተው በእግረኞች ላይ ነው።
———
(አዲስ ማለዳ)
18.3K views14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 21:44:35 የቤት ኪራይ? የቤት ግዢ ? መሬት?
ይቀንሳሉ ይጨምራሉ?

ሰሞኑን በርካታ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች እየወጡ መሆኑን ተከትሎ ከሚዘዋወሩ ጥያቄዎች መካከል የቤት ዋጋ ይቀንሳል ወይስ ይጨምራል? የቤት መግዢያስ ? የመሬት ነገር እንዴት ይሆናል? የሚሉ ግዘፍ ነስተው ወጥተው ይታያሉ።

እኔም በዚህ ጉዳይ የግል ምልከታና ግምቴን ማስቀመጥ ወደድኩ።

በእኔ አመለካከት በአጭሩ የቤት ኪራይ ዋጋ ይጨምራል፣ የቤት መግዣ ዋጋ ይቀንሳል፣ የመሬት ዋጋም እየቀነሰ ይሄዳል የሚል ነው። ለእያንዳድንዳቸው ምክንያቶቼንም እንዲህ አስቀምጣለሁ:-

1) #የቤት_ኪራይ_ዋጋ_ይጨምራል ያልኩባቸው ምክንያቶች
፩) ብዙ ቤቶች ለኪራይ ገበያ እየወጡ ባለመሆኑ
፪) እንደሌሎች ዘርፎች ከመንግስት መመሪያዎች ትይዩ በቤት ባለቤቶች የሚያወጧቸው መሬት ላይ የሚተገበሩ ያልተጻፉ ህጎች ገዢ ስለሚሆኑ
፫) ባለፉት አመታት ዋጋ መጨመርም ሆነ ከቤት ማስወጣት ክልክል በነበረባቸው ወቅቶች የቤት አከራዮችና ተከራዮች ኑሮ ውድነቱን ያማከለ መጨማመርና ልምምድ መኖሩ
፬) ፖሊሲዎችን እንደ ክፍተት የሚጠቀሙ የተከራይ አከራዮች መበራከት (ትልቅ ቤት ተከራይተው ከፋፍለው የሚያከራዩ (House hackers ) መበራከት)
፭) በመኖሪያ ቤትነት ከማከራየት ይልቅ ጥቂት የቤት ዕቃዎችን አሟልተው በእንግዳ ማረፊያ (Guest house) ስም ማከራየት ተመራጭ (ማምለጫም) እየሆና መምጣቱ
፮) ከተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች ወደ መዲናችን በተለያዩ ምክንያቶች ለኑሮ የሚመጡ ወገኖች ቁጥር እየጨመረ መሄዱ
፯) የጊቢውና ሌሎች ወሳኝ ቦታዎች ቁልፍና የግቢው መተዳደሪያ ህግ በቤቱ ባለቤቶች እጅ መሆኑ :)

2) #የቤት_መግዣ_ዋጋ_ይቀንሳል ለማለት ምክንያቶቼ
፩) የገንዘብ (ካሽ) እጥረት መኖሩ
፪) ብዙ አልሚዎች ዘርፉን መቀላቀላቸው
፫) በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ በርካታ ቤቶችን በአንድ አካባቢ የሚገነቡ ከተማ አከል የቤት ግንባታዎች ( mass housing projects) መጀማመር
፬) በቴክኖሎጂ የተደገፉ ዋጋ ቀናሽ የቤት አማራጮች እየመጡ መሆኑ
፭) የመሬት አቅርቦት መሻሻል ( በሊዝ፣ በPPP ፣ አብሮ ማልማት...)

3) #የመሬት_ዋጋ_ይቀንሳል ስል ምክንያቶቼ
፩) በርካታ መሬት ወደ ገበያ እየወጣ መሆኑ ( በመንግስት፣ በግለሰቦች፣ በልማት ተነሺዎች፣ በልማት ሰጊዎች :) ...)
፪)የገንዘብ (ካሽ) እጥረት መኖር
፫) ከመግዛት ይልቅ አብሮ ማልማት በቦታ ገዢዎች እየተመረጠ መምጣቱ
፬) የፈረሳ ስጋት መኖር
፭) ከመንግድ ገብቶ መገንባት የሚለው መመሪያ ይየትናንሽ መሬቶችን የመልማት አቅም ስለሚፈታተን
፮) በኮሪደር ልማት ተከትሎ የተቀመጠውን የግንባታና ዲዛይን መስፈርት አሟልቶ መገንባት ለብዙዎች ከባድ መሆኑ
፯) በቂ አቅም ማሳያና ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ለሚያዘጋጁ ቀጥታ ከመንግስት ለማስፋፊያም ሆነ ለአዲስ ፕሮጀክት መሬት የማግኘት ዕድል እየሰፋ መምጣቱ

በ ደሳለኝ ከበደ።
ሲቪል መሀንዲስ፣ ሪል ስቴት አማካሪ፣
16.9K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 21:44:33
15.8K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 07:06:43 የብልፅግና ፓርላማ ትላንት ከዚህ በኋላ የቤት ኪራይ (ለግዜው የመኖሪያ ቤት) ዋጋ የሚተመነው ጥሮ ግሮ ባገኘው ገንዘብ ቤቱን በሰራው ሰውዬ ሳይሆን፣ ቤቱ ሲሰራ ድንቡሎ ያላዋጣ፣ ቢሮ ቁጭ ያለ የሆነ ባለስልጣን (መንግስት) ነው የሚል አዋጅ አፅድቋል።

በነገራችን ላይ የንብረት ባለቤትነት መብት የመብቶች ሁሉ ቁንጮ ነው፣ የሰው ልጅ በህይወት መኖር የሚችለው ደክሞ ያፈራውን ሀብት በነፃነት መጠቀም ሲችል ነው። ስለዚህ የንብረት መብትህ ተጣሰ ማለት በህይወት የመኖር መብትህ ተጣሰ ማለት ነው። ካልተሳሳትኩ አዋጁ በህገ መንግስቱ ከተቀመጠው የንብረት መብት ጋር ሁሉ ይጣረሳል።ይሄን ለህግ ሰዎች ትተን እኛ ወደ ኢኮኖሚክሳችን እንሂድ።

መቼም ፈርዶብኝ ኤንጂ ስለ ዋጋ ተመንና ውጤቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማብራራት አይጠበቅብኝም ነበር። ምክንያቱም ውጤቱን በሲሚንቶ፣ በዘይት፣ በስኳር ወዘተ በአይኑ በብረቱ አይቶታልና። (ተመሳሳይ ነገር እየሰራ የተለየ ውጤት የሚጠብቅ ሰው ነሆለል ነው ያለው ማን ነበር?)

ሲጀመር የቤት ኪራይ ያሳየው ጭማሪ ከሌላው ሸቀጥና አገልግሎት የተለየ አይደለም፣ ለምሳሌ የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ኩንታል ጤፍ ስድስት ሺ ብር ሲሸጥ፣ እኔ ያለሁበት አከባቢ የባለ ሁለት መኝታ ቤት ኮንዶሚኒየም ዋጋ ዘጠኝ ሺ ብር ገደማ ነበር። አሁን ጤፉ አስራ ሶስት ሺ ብር ሲሆን ቤቱ ደግሞ ሀያ ሺ ብር ገብቷል። ቤቱን በዘጠኝ ሺ ብር አከራይቶ ጤፍ ሸምቶ በተረፈው ሌላ ሸቀጥ ይገዛ የነበረ ሰው አሁንም በሀያ ሺ ብሩ መሸመት የሚችለው ተመሳሳይ ነገር ነው። የጨመረው ሲሸጥ ይቀበልና ሲገዛ ይሰጥ የነበረው የገንዘብ መጠን ብቻ ነው፣ ያገኘው አዲስ የመግዛት አቅም የለም። ከእያንዳንዱ ልውውጥ ውስጥ በዚህ መልኩ ብሩን እያወጣን እቃን በእቃ እየመዘንን ብናየው ውጤቱ ተመሳሳይ ነው።

የጨመረው የእቃው ዋጋ ሳይሆን የልውውጥ አማካኙ (የወረቀት ብሩ) መጠን ነው፣ ይሄ ማለት ችግሩን እየፈጠረ ያለው ባለ ብሩ ነው ማለት ነው። የሆነ አካል ባዶ ወረቀት ይዞ ገበያ እየመጣ እሴት ባለው ነገር ለውጦ ወደቤቱ ይሄዳል ማለት ነው።ብር የማተም ብቸኛ ስልጣን ያለው ማን እንደሆነ ደግሞ ይታወቃል። በሚገርም ሁኔታ ችግሩን የፈጠረው አካል ችግሩን የፈጠራችሁት እናንተ ናችሁ፣ እናንተ ለፈጠራችሁት ችግር መፍትሄ አመንጪ ደግሞ እኔ ነኝ ባይ ነው።

በነገራችን ላይ በዚህ አዋጅ የመጀመሪያው ገፈት ቀማሽ ተከራይ ነው( ገፈት ግን ምንድነው ጎበዝ)። ምናልባት ለተወሰነ ግዜ በአዋጁ ኢንጆይ ያደርግ ይሆናል።መጪው ግዜ ግን ለእርሱ ድቅድቅ ጨለማ ነው። ምክንያቱም ሰው በገዛ ገንዘቡ በሰራው ነገር ላይ አዛዥ፣ ባለቤትና ተጠቃሚ የማይሆን ከሆነ የግዜ ጉዳይ ነው እንጂ ብሩን(ካፒታሉን) ሌላ መንግስት ወደማይቆጣጠረው ስራ ያዛውረዋል።ስለዚህ ከጥቂት ግዜ በኋላ የቤት አቅርቦት ይቀንሳል፣ አቅርቦት ይቀንሳል ማለት ደግሞ ዋጋ ይጨምራል ማለት ነው።የአቅርቦትና ፍላጎትን ህግ ተከትሎ የሚፈጠረውን ዋጋ ደግሞ በአዋጅ አታቆመው፣ በፓሊስ አታቆመው፣ በታንክ አታቆመው፣ በድሮን አታቆመው።

የቤት ኪራይን ችግር መንግስት የምር መቅረፍ ከፈለገ ማድረግ የሚገባው ሁለት ነገር ነው። አንደኛ በየግዜው ዋጋ እየጨመረ ያለው በግሽበት ምክንያት ስለሆነ ኪራይ እንዳይጨምር ግሽበቱን ማቆም። ሁለተኛ የቤት እጥረት የተከሰተው መሬቱ በመንግስት ተቀፍድዶ በመያዙ ስለሆነ አቅርቱቦት እንዲጨምር መሬቱን የግል ማድረግ ነው። ከዛ ውጭ ያለው ሙከራ ከንቱ ድካም ነው።

Mekoya Kebede
20.1K views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 07:06:40
19.0K views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 07:48:19 https://vm.tiktok.com/ZMMuvcEwy/
20.7K views04:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 20:42:05
19.1K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 15:45:18
የኪራይ ገቢ ግብር ማስከፈያ ምጣኔ

በድርጅቶች የሚከፈለው የኪራይ ገቢ ግብር ምጣኔ 30% (ሰላሳ በመቶ)ነው::

የቤት ኪራይ ገቢ ግብር እንዴት ይሰላል?
*****
• ግብር የሚከፈልበት የኪራይ ገቢ የሚባለው፤ በግብር ዓመቱ ግብር ከፋዩ ቤት በማከራየት ካገኘው ጠቅላላ ዓመታዊ ገቢ ላይ ለግብር ከፋዩ የተፈቀደው ጠቅላላ ወጪ ተቀናሽ ተደርጎ የሚቀረው ገቢ ላይ ነው፡፡

• የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ያገኘው ግብር የሚከፈልበት ገቢ ነው የሚባለው፤ የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ከተቀበለው ጠቅላላ የኪራይ ገቢ ላይ ለዋናው አከራይ የሚከፍለው ኪራይ እንዲሁም ገቢውን ለማግኘት ያወጣቸው ሌሎች ወጪዎች ከተቀነሱ በኋላ የሚቀረው ገንዘብ ነው፡፡

• ተከራይ የተከራየውን ቤት መልሶ እንዲያከራይ የሚፈቅድ የቤት ባለቤት፤ ተከራዩ ግብሩን ሳይከፍል ቢቀር ስለእርሱ ሆኖ ግብሩን የመክፈል ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡

ምንጭ፡- የገቢዎች ሚኒስቴር
16.0K viewsedited  12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 15:39:19
ለጋራ መኖሪያ ቤቶች የትራንስፎርመር አቅም ማሻሻያ ስራ እየተከናወነ ነው

ለኮዬ ፈጬ ሁለት የጋራ መኖሪያ ቤት ሳይቶች ለነዋሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ ትራንስፎርመሮች አቅም ማሻሻያ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ከተገነቡት ግዙፍ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል የኮዬ ፈጬ ሳይት አንዱ ሲሆን ነዋሪዎቹ የመደበኛው የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እስኪጠናቀቅ ድረስ በጊዜዊነት የኤሌክትሪክ የአገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉ ይታወቃል፡፡

በአሁኑ ወቅት ለነዋሪዎቹ እየቀረበ ያለውን አገልግሎት በቂና አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችል የትራንስፎርመር አቅም ማሻሻያ ስራ በመከናወን ላይ ሲሆን የማሻሻያ ስራው የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግና አጋዥ ትራንስፎርመር መትከልን የሚያካትት ነው፡፡

እንዲሻሻሉ በጥናት ከተለዩ 30 ትራንስፎርመሮች መካከል በአሁኑ ወቅት የ10 ትራንስፎርመሮች የማሻሻያ ስራ በመከናወን ላይ ሲሆን በቀጣይም የቀሪዎቹ የማሻሻያ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡

የትራንስፎር ማሻሻያ ስራው 60 ሚሊዮን 583 ሺ 168 ብር ወጪ በመከናወን ላይ ሲሆን የማሻሻያ ስራው ሲጠናቀቅ ነዋሪዎቹ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
15.9K views12:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ