ለመምህራን በእጣ የተላለፉ ቤቶችን የተመለከተ ማስታወቂያ ለመምህራን የተላለፉ 435 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውል የመፈፀም ሂደት ነገ በ12/08/16 ዓ.ም ይጀመራል የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ እና ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ6/07/2016 ዓ.ም በተለያየ ምክንያት ሳይተላለፋ የቀሩ 435 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ለመምህራን በእጣ መተላለፋቸው ይታወሳል። በመሆኑም የቤት እድለኛ የሆናችሁ መምህራን ከሀሙስ ማለትም ከ12/08/16 ዓ.ም ጀምራችሁ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ውል መፈፀም የሚያስችል ሂደት እንድትጀምሩ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ይገልፃል። ተዋዋዮችም በአለቱ የታደሰ መታወቂያ ፣ በተጨማሪም መምህር/ት መሆናችሁን የሚያሳይ ማስረጃ የት/ቤት መታወቂያና ከትምህርት ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ ይዛችሁ መገኘት አለባችሁ በማለት ኮርፖሬሽኑ እያሳሰበ በዉክልና ለመስተናገድ የምትመጡ አካላት በቂ ማስረጃ መያዛችሁን አትዘንጉ። ማሳሰቢያ - በ60 ቀናት ዉስጥ ቀርቦ ዉል ያልፈጸመ እድሉን እንደተወ ተቆጥሮ ተጠባባቂዎች በቅድመ ተከተል እንደሚስተናገዱ እናሳስባለን! - ተዋዋዮች ለመዋዋል ስትመጡ ከታች የተቀመጠውን መስፈርት ታሳቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን! የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን 15.6K views21:24