Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.66K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2024-02-28 02:20:27
የጨረታ መክፈቻው ተራዘመ

ኮርፖሬሽኑ ፤ ከሕብረተሰቡ መጣልኝ ባለው ጥያቄ መነሻነት የጨረታ መክፈቻ ጊዜው ለ10 ቀናት የተራዘመ መሆኑ አሳውቋል።

በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች እስከ መጋቢት 02/2016 ዓ/ም ድረስ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ምሽቱ 1፡30 እንዲሁም እሁድ ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ቀኑ 6፡00 በሁሉም ክፍለከተሞች ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በአካል በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላል ተብሏል።
14.3K views23:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-27 22:23:09
የጨረታ መክፈቻው ተራዘመ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ ጋር በመተባበር ያስገነቧቸውን 3,452 የመኖሪያና የንግድ ቤቶችን በሽያጭ ለማስተላለፍ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ ይገኛል።

ኮርፖሬሽኑ ፤ ከሕብረተሰቡ መጣልኝ ባለው ጥያቄ መነሻነት የጨረታ መክፈቻ ጊዜው ለ10 ቀናት የተራዘመ መሆኑ አሳውቋል።

በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች እስከ መጋቢት 02/2016 ዓ/ም ድረስ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ምሽቱ 1፡30 እንዲሁም እሁድ ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ቀኑ 6፡00 በሁሉም ክፍለከተሞች ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በአካል በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላል ተብሏል።
15.0K views19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-27 13:47:44
አራዳ ፒያሳ መስከረም 1983 ዓ.ም
Elias Yemane
17.2K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-27 03:12:33 አዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት ያገኘችው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር በ41 በመቶ ብልጫ አሳይቷል ተባለ

በጊዜው 74 ቢሊዮን ብር መገኘቱ ተሰምቷል፡፡

http://tinyurl.com/2sxt5mdb

ያሬድ እንዳሻው
18.3K views00:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-25 21:50:58
የቤቶች ልማትን በተመለከተ በግማሽ ዓመቱ የተከናወኑ ሪፖርት

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከቤቶች ልማት አንጻር በበጀት ዓመቱ ግንባታቸውን ለማስጀመር ከታቀደው 120 ሺህ ቤቶች መካከል 99 ሺህ 113 ቤቶች ማልማትጠመቻሉን ገልፀዋል፡፡

ከተማ አስተዳደር ከቤቶች ልማት አንጻር በአቃቂ ክፍለ ከተማ 60,185፣ በቦሌ 14 ሺህ፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶ 10 ሺህ፣ በልደታ 8,600፣ በቂርቆስ 6,156፣ በጉለሌ 172 በድምሩ 99 ሺህ 113 ቤቶች ማልማት መቻሉን ከንቲባ አዳነች በሪፖርታቸው ገልፀዋል።

ከተማ አሰተዳደሩ በዘንድሮ በጀት ዓመት የ111 ሺህ ቤቶች መገንባት የሚያስችል የአጋርነት ውል እና የመሬት ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪ በመንግት በጀት የተገነቡ 4200፣ በበጐ አድራጎት የተሰሩ 5023 ፣ በግለሰብ እና በሪልስቴት ከ10,000 አጠቃላይ 19,223 ቤቶች ተገንብቶዋል ብለዋል፡፡
ከቤቶች ግንባታ በተጨማሪ በመንግስትና በግል አጋርነት ፕሮግራም እየተገነባ የሚገኘው ለሚ ፓርክ ግንባታው 60 በመቶ ደርሷል ሲሉም ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም ከቤቶች ልማት አኳያ 149,892 የመንግስት ቤቶች እና 126,734 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መረጃን በዘመናዊ ሶፍትዌር ማደራጀት ተችሏል፣

125ሺህ 764 የቤት ፈላጊዎችን መረጃ እና 307 ሺህ 726 የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎች መረጃ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደራጅቷል ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል፡፡
21.2K views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-25 19:57:09
ለመምህራን በብድር የኤሌክትሪክ መኪና የመስጠት ኘሮጀክት ይፋ ሆነ

ጤግሮስ ትሬዲንግ ከፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ስራ ማኀበር ጋር በመሆን ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል ለመምህራን በብድር የኤሌክትሪክ መኪና ለማቅረብ የሚያስችላቸውን ኘሮጀክት ይፋ አደረገ። የአባልነት መስፈርታቸውን ላሟሉ እና ቁጠባቸውን ለአጠናቀቁ መምህራን እና የትምህርት አመራሮች የመጀመሪያ ዙር ዘመናዊ የኤሌትሪክ መኪኖች ብድር የመስጠት ፕሮጀክት ከፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/ህ/ስ/ማኅበር እንዲሁም ከበላይነህ ክንዴ ጄነራል ትሬዲንግ ጋር በተደረገ ስምምነት መስጠት የተጀመረ እና በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ 11 ክፍለ ከተሞች በተደረገው ምዝገባ ከ2500 በላይ መምህራን እና የትምህርት ባለሙያዎች የኤሌክትሪክ መኪና በብድር ለመውሰድ ፍላጎት ማሳየታቸውን የገለጹ ሲሆን ሁለተኛው ዙር ምዝገባ መጋቢት 5 ቀን 2016ዓ.ም እንደሚጀመር ገልጸዋል።

"የእውቀት ባለቤት ውለታ እንመልስ" በሚል መሪ ቃል ለሀገር ባለውለታ ለሆኑ መምህራን ቁጠባና ብድርን መሰረት ያደረገ "ደራሽ" የተሰኘ የኤሌክትሪክ መኪና ግዥ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐግብር ላይ 10 ለሚሆኑ መምህራን እና የትምህርት ባለሙያዎች በበላይነህ ክንዴ የመኪና መገጣጠሚያ የተመረቱ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ቁልፍ ተበርክተዋል።

በቀጣይ የጤና ፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የኪነጥበብ ባለሙያዎችን የመኪና እና የቤት አቅርቦትን በብድር ተደራሽ ለማድረግ ዝርዝር ጥናቶች እየተከናወኑ ነው።

በመርሐግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የበላይነህ ክንዴ ጄነራል ትሬዲንግ ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ ለመምህራን ማድረግ የሚገባንን ድጋፍ በቀጣይ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
22.0K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-25 12:37:58
ገበሬው ቲማቲም ለነጋዴው በ3 ብር ይሸጣል፣ ነጋዴው ለሸማቹ በ80 ብር

ይሄ የሀገሪቱ ቀውስ ውጤት ነው!!
21.0K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-25 09:17:35
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመዲናዋ 4 ዋና ዋና የመንገድ ኮሪደሮች እንዲለሙ ውሳኔ አሳለፈ

ካቢኔው አዲስ አበባ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የመንገድ ኮሪደሮች ልማት ለማከናወን የሚያስችል ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።

በዚህም የከተማዋን አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን እና ዘመናዊነት እንዲሁም የትራንስፖርት ፍሰት ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሳድጉ የሚችሉ የመንገድ ኮሪደር እና የአካባቢ ልማቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

በውሳኔው መሠረት የሚለሙት የመንገድ ኮሪደሮች የሚከተሉት መሆናቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፦

• ከአራት ኪሎ በመስቀል አደባባይ እስከ ቦሌ ድልድይ (7 ኪ. ሜትር)
• ከቦሌ አየር መንገድ እስከ መገናኛ ዳያስፖራ አደባባይ (4.9 ኪ. ሜትር)
• ከመገናኛ ዳያስፖራ አደባባይ በአራት ኪሎ በኩል የዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ ድረስ (6.4 ኪ. ሜትር)
• ከፒያሳ አድዋ ድል መታሰቢያ ዙርያ በለገ-ሃር፣ ሜክሲኮ፣ ሳርቤት በኩል እስከ ወሎ ሰፈር (10 ኪ. ሜትር)

እነዚህ የመንገድ ኮሪደር ልማቶች ዘመናዊ ከመሆናቸውም በላይ ዓለም አቀፍ የስማርት ሲቲ ስታንዳርድን በማሟላት የከተማዋን ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ ናቸው ተብሏል።

የመንገድ ኮሪደር ፕሮጀክቶቹ አዋሳኝ የወንዝ ተፋሰሶችን ያቀፉ፣ ለሳይክልና ሞተር አልባ ትራንስፖርትም አገልግሎት የሚሰጡ እንደሚሆኑ ተጠቅሷል።
21.5K views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-11 12:22:21
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም

በአዲስ አበባ ፒያሳ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ዛሬ ይመረቃል።

በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ሙዚየም የኢትዮጵያውያን ጀግኖች ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራት የሆነ ተጋድሏቸውን የሚዘክሩ ስራዎችን ይዟል።

በሙዚየሙ ውስጥ የዓድዋ ድል የክተት አዋጅ የታወጀበት ነጋሪት በነሐስ ተሰርቶ ይገኛሉ።

ሙዚየሙ ከምድር በታች ያለውን ሁለት ደረጃዎችን ጨምሮ 5 ወለሎች ያሉት ሲሆን፥ ከ1 ሺህ በላይ የመኪና ማቆሚያዎችን ጨምሮ በርካታ አዳራሾችንም አካቷል።
13.3K viewsedited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-11 01:54:44
"አድዋ-00 ሙዚየም"
15.3K views22:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ