Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.49K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-05-01 13:44:17 ትህነግ የጓዳ ውሉን ይፋ አደረገው!

ትህነግ በጀኔራል ታደሰ ወረደ በኩል የጓዳ ውሉን በማያሻማ መልኩ ይፋ አድርጓል። ብልፅግና ጠለምትና ራያን በቅርቡ፣ ከዛም ወልቃይትን አሳልፎ ለመስጠት የተዋዋለበትን በይፋ ተናግሯል። ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን በትህነግ ታጣቂ ከራያ የተፈናቀሉት በጓዳ ውሉ መሰረት እንደሆነ ይታወቃል። አማራ እየተወረረ ያለው በጓዳ ውሉ መሰረት ነው።

የብልፅግና አመራሮች ስለ ትህነግ ትጥቁን መፍታት ወዘተ ሲያወሩ "ውሸታቸውን ነው" የምንለው በምክንያት ነው። ጦርነት የሚፈልግ ኃይል ወዘተ እያለ የሚያወግዙ የሚመስሉት ውሸት ነው። የአማራን ግዛቶች አሳልፈው ለመስጠት የተዋዋሉት በወረራ መሆኑ ይፋ ወጥቷል። ታደሰ ወረደ ብልፅግና አማራን በኃይል እንዲይዙ የሰጣቸውን ድጋፍና ፈቃድ በሚዲያ ወጥቶ ሲገልፅ ይህ ሁለተኛ ጊዜው ነው። እነ ተመስገን ጥሩነህ "ያፈነገጠ ወዘተ" እያሉ ሀሰት ሲናገሩ፣ ጀኔራል ታደሰ በይፋ መጥቶ ከብልፅግና ጋር የተዋዋሉት የጓዳ ውል መሆኑን እየገለፀ ነው።

አማራን በትህነግ እያስወረረ የሚገኘው ብልፅግና ነው። ትህነግ ባለፈው በጌታቸው ረዳና ታደሰ ወረደ፣ ዛሬም በታደሰ ወረደ በኩል ወረራው ከብልፅግና ጋር በተስማሙት መሰረት የተደረገ እንደሆነና እንደሚቀጥል ሲገልፅ ብልፅግና ትንፍሽ አላለም። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደሮች ናቸው ወረራው በስምምነት የተፈፀመ መሆኑን የሚናገሩት። ያፈነገጠ ወዘተ የሚባለው ነጭ ውሸት ነው። ማዘናጊያ ነው። የጓዳ ውሉን ማድበስበሻ ነው!
15.7K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 10:38:39 ሬዲዮው የትህነግ/ህወሓት ባትሪ ሳይጎርስ!
13.3K views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 09:18:16
14.6K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 09:18:07 የእስር ሰለባው ጋዜጠኛ ለምክክር ኮምሽኑ ያነሳቸው ወሳኝ ጥያቄዎች

ሞኝን እብባ ሁለት ጊዜ ነደፈው፤ አማራስ ሁለት ጊዜ ይነደፍ ይሆን! በፍጹም!

(ዳዊት በጋሻው ከቃሊቲ እስር ቤት)

ሚያዚያ 13 እና 14 2016 ዓ.ም በትጥቅ ትግል ላይ የሚገኙ ኃይሎች ወደ ምክክር እንዲመጡና ለዚህም ከለላ እንደሚደረግ የሚገልፀ ዜና ተመለከትኩ፡፡ ይህንን ያሉት የሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሞሽነር ሂሩት ገ/ስላሴ ናቸው፡፡ ወቅቱ አሰቃቂ የጭንቅ ጊዜ ሆነ እንጅ ንግግራቸው ሙሉ የኮሜዲ ይዘት ያለው ነው፡፡ ግለሰቧ ይህንን በተናገሩበት ወቅት የአማራ ልጆች በማንነታቸው ብቻ እየተመረጡ የሀገሪቱን እስርቤቶች ሞልተዋል፡፡ የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ እና በሌላው የሀገሪቱክፍሎች በሀሠት እየተከሰሱ ፤ እንደ አዋሽ አርባ ባሉ የማሰቃያ ቦታዎች መከራቸውን እያ ባለበት ወቅት ከለላ እናደርጋን እንመካከር እያሉ ማውራት ህሊና ቢስነት ነው፡፡ በታሪክ ፊትም ተጠያቂ ያደርጋል፡፡ የአማራ ልጆች የዕድሜ ፣የሙያ የፆታ፣ የእምነት፣ የት/ት ደረጃ ልዩነት ሳይኖር በጅምላ እየታሰሩ ነው፡፡ በሀገሪቱ ያሉ እስር ቤቶች በመሙላታቸው የብልፀሸግና ፓርቲ አመራሮች በኦሮምያና በአፋ አማራ የሚታጎርባቸው ወህኒ ቤቶች በአጭር ጊዜ እንዲሰሩ ማዘዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው እንግዲህ ስለምክክርና ስለከለላ ዋስትና እየተወራ ያለው፡፡ እስኪ ለኮሚሽኑ አባላት በተለይም ለዋናና ለምክትላቸው እነዚህን ጥያቄዎች ላንሳ፡-

1. በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ማጥፋትወንጀል እያያችሁና በዚህም ላይ ምንም ሳትሉ ስለምክክር ስታወሩ ህሊናችሁ ምን ይላችኋል?

2. በአስቸኳይ አዋጅ ሰበብ ንፁሀንን በድሮን እየተጨፈጨፉ እናንተ እንመካከር ስትሉ ህዝቡ ምን የሚል ይመስላችኋል?

3. ፖሊስና ደህንነት የነቁ አማሮችንበመላው ሀገሪቱ እያሳደዱ ባሉበት ሁኔታ እናንተን አምኖ ጠረንጴዛ የሚስብ ያለ ይመስላችኋል?

4. እናንተ ከለላ እንስጣችሁ የምትሏቸው የአማራ ህዝብ የትግል መሪዎች በፍትህ ሞኒስቴር ተከሰው በጋዜጣ ተጠርተዋል፡፡በአንድ በኩል የወንጀል ክስ ከፍቶ በሌላ በኩል ከለላ ልስጥ ማለት አይጋጭም ወይ?

በመሰረቱ እኔ ጥያቄን ባሳደገኝ ህዝብ ጨዋነት ልክ በትህትና ላቅርብ ብዬ እንጅ ስለ 11ዱም ኮሚሽነሮችመረጃም ማስረጃም አለኝ፡፡

ለምሳሌ ያህል ስለ ፕ/ር መስፍን አርአያ ፣ መሐመድ ድፈር፣ ዮናስ አዳዬ፣ ዘገዬ አስፋው በደንብ መናገር ይቻላል፡፡
የምክክር ኮሚሽኑ አባል አቶ ዘገዬ አስፋው የኦነግ ስራ አስፈጻሚ መሆን በሽግግሩ ወቅት የአማራ ህዝብን አስጨፍጭፏል፡፡ ይህ ተራ አሉባልታ ሳይሆን በሰነድ የተቀመጠ ሀቅ ነው፡፡በመሆኑም በወቅቱ የግብርና ሚኒስትር ነበር፡፡ በጥቅሉ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመና ያስፈፀመ በመሆኑ ህዝብ በወንጀል ይፈልገዋል ፡፡ በተጨማሪም የአማራ ልጆች በአዲስ አበባ ዙርያ ቤታቸው ፈርሶ፣ ተፈናቅለው በስቃይ ላይ ሆነው ፤ለንብረታቸውና ለህይወታቸው ምንም ይቅርታና ዋስትና ሳይደረግ በማን አለብኝነት ሸገር ከተማ ብሎ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከተማ ሲያስመርቅ አቶ ዘገየ አስፋው የድግሱ ተካፋይ ነበር፡፡ ስለሌሎችም ሙሉ ማስረጃ አለ፡፡ የኮሚሽኑ ገለልተኛነት እዚህ ድረስ ነው፡፡ ለማንኛውም ለአፍና ለይምሰል እንኳን እነዚህን ጥያቄዎች ለማንሳት ሞክሩ፡-

1) መንግስት የምትሉት አካል ተኪስ እንዲያቆምና የዘር ፍጅቱን እንዲተው

2) አዋጅ ተብዬው መግደያና ማሳደጃ እንዲቀርና ለዚህም ተጠያቂ እንዲሆን

3) በመላው ሀገሪቱ ያለውን የንፁሀን ግድያ እንዲያቆም በተደጋጋሚ ብትናገሩ ለይምሰል እንኳን የተሸለ ይሆናል፡፡

በመሰረቱ ዐቢይ አህመድ ምክክር ኮሚሽንና ሽግግር ፍትህ እያለ ያለው፦

1. በነዚህ ተቋማት ሰበብ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት

2. ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ይሄው ላወያይ ነው ለማለትና ስልጣንን ለማራዘም ነው፡፡ ያም ሆነ ይሕ ግን ከዚህ በኋላ የአማራን ህዝብ ለዓመታት አይደለም ለቀናት መሸወድ ወይም በሽመልስ አብዲሳ አገላለፅ (ኮንቪንስና ኮንፊውዝ) ማድረግ በፍፁም አይቻልም፡፡ ከዚህ በኋላ ጥቅም ላይ የሚውል አይደለም፡፡

ለማንኛውም ለይምሰል የሚደረግ የትኛውም ድርጊት ከህዝብ አያመልጥም፡፡
መንግስቱ ሀይለማርያም በስተርጅና ለስደትና ለውርደት፤ መለስ ዜናዊን በህዝብ ፊት ለውርደት ብሎም ለሞት የዳረጓቸው ሁኔታዎች እልህና ይምሰል ናቸው ( የፈጣሪን ሀያልነት ረስቼ አይደለም)፡፡ ያም ሆነ ይህ አማራን እያሳደዱ መመካከር፤ ማስነገር ጊዜው አልፎበታል፡፡ የአማራ ህዝብ ከዚህ በፊት በወለጋ፣ በመተከል፣ በሀረርጌ፣ በአርሲ፣ …. ሲጨፈጨፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ጭፍጨፋው ቤቱ በር ላይ ነው፤ይ የማንክደው ሀቅ ነው፡፡ ለህልውና መታገል ደግሞ ፈጣሪም ዓለም አቀፍ ማህበረሰብም የሚደግፈው ነው፡፡
ሕዝብ ማሸነው አይቻልም
የአማራ ህዝብ ትግል ለእውነት፣ ለፍህ፣ ለለውጥ ነው፡፡
14.4K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 13:48:11
15.6K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 13:48:04 የትህነግ ታጣቂ ራያ ላይ እየፈፀመው ያለው ሰቆቃ በገለልተኛ ሚዲያ እይታ!

ከስር ያለው መረጃ ዓል አይን አማርኛ የትህነግ ታጣቂ እየፈፀመው ያለውን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃ በወረራ ስር ያሉትን ነዋሪዎች አናግሮ ከዘገበው የተወሰደ ነው።

#የትግራይ ታጣቂዎች ከመጡበት ዕለት አንስቶ ንብረታችን እየተነጠቀ ነው፡፡ ለገበያ የደረሰ ሀብ ሀብ አትክልቴን በልተውብኛል ሲጠግቡ ደግሞ በያዙት ጦር መሳሪያ በሰደፉ እና በአፈሙዙ እየመቱብኝ ነው”

#በቀበሌያችን ከገቡበት ከሰኞ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በገበሬው ቤት እየገቡ እየደበደቡን ነው። አርሶ አደር ጦር መሳሪያ አምጡ እያሉ እኛ ገበሬዎች ነን ፖለቲካ አናውቅም ብንልም ሊተውን አልቻሉም"

#ከዚህ በፊት አብረውን ይኖሩ የነበሩ ነገር ግን በስጋት ምክንያት ወደ ትግራይ ተፈናቅለው የነበሩ ሰዎች ካሳለፍነው ሰኔ እና ግንቦት ወር ጀምሮ እየገቡ መኖር ጀምረዋል፣ ሳይገቡ የቀሩት ከዚህ በፊት በነበረው አስተዳድር ጊዜ ህዝብን ሲያንገላቱ እና ሲያማርሩ የነበሩት ብቻ ቀርተው ነበር"

#ታጣቂዎች ሲቪል እየለበሱ ወደ ከተማዋ ነዋሪ መስለው እየገቡ ነው፣ የመንግስት ተቋማትን እየዘረፉ እና ፋይሎችን እያወደሙ የከተማዋ ነዋሪዎችንም ፍርሃት ውስጥ እንዲገባ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ነው። በከተማዋ ያለው የፌደራል የጸጥታ ሀይል ቢኖርም ነዋሪውን ከመሰደድ አልታደገውም"

#የፌደራል መንግስት ለራያ እና አላማጣ ጉዳይ ዘለቄታዊ መፍትሔ ይሰጠዋል ብለን እየጠበቅን ለትግራይ ታጣቂዎች አሳልፎ ሰጥቶናል።

#በሰሌን ውሃ ቀበሌ የሚኖረው ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በበኩሉ የትግራይ ታጣቂዎች የራያ እና አላማጣ የገጠር ቀበሌዎችን ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መቆጣጠራቸውን፣ በየቀኑ አዳዲስ እና ተጨማሪ ታጣቂዎች ወደ አካባቢዎቹ እየገቡ መሆኑን አክሏል፡፡
ታጣቂዎቹ በየሰው ቤት እየገቡ የልጆችን ምግብ ሳይቀር እየበሉ እንደሆነ፣ ለባሏ የምሳ እቃ ለማድረስ ወደ እርሻ ቦታ እየሄደች ያለችን እናት ለአማራ ታጣቂ ልትሰጪ ነው በሚል እያንገላቱ ነው ያሉት እኝህ አስተያየት ሰጪ ታጣቂዎቹ ይህን ሲያደርጉም የፌደራል የጸጥታ ሀይሎች እያዩ የማስቆም ፍላጎት እንደሌላቸውም ነግሮናል፡፡

#ከዚህ በፊት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ወደ መቀሌ እና ሽሬ የሄዱ ነዋሪዎች ወደ ቀድሞ ቤታቸው ተመልሰው አብረን በጋራ እያረስን እና እየኖርን ቢሆንም ታጣቂዎቹ በድንገት መጥተው ለእንግልት እንደዳረጓቸውም አክሏል፡፡

#ታጣቂዎቹ በየጊዜው እየሰበሰቡም ከእንግዲህ እምናስተዳድራችሁ እኛ ነን፣ የያዛችሁትም የአማራ ክልል የነዋሪነት መታወቂያ ከእንግዲህ አይጠቅማችሁም፣ ልጆቻችሁን አምጡ እና ለአማራ ታጣቂዎች ድጋፍ እያደረጋችሁ ነው የሚሉ ወከባዎችን እያደረሱባቸው እንደሆነም እኝህ አስተያየት ሰጪ ተናግረዋል፡፡

#ወቅቱ የሚያዚያ ወር አዝመራ የምናዘምርበት ቢሆንም እርሻችንን ትተን በየቀኑ ምን እንሆን ይሆን የሚል ስቃይ ውስጥ ነን"
16.2K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 09:43:57
14.1K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 09:43:47 ተፈናቃይ ብለው የሚያስገቡት ይህንን ዘራፊ ኃይል ነው!

ትህነግ በወረራው ወቅት አማራና አፋርን መዝረፍን ጀብዱ አድርጎ ለወጣቱ አስተማረው። አትክልትና ፍራፍሬ ጭምር "ከአማራ ክልል የመጣ" እየተባለ በሞንታርቦ እየተጮኸ ሲሸጥ ነበር። የአማራ ክልል ታርጋን አንስተው ታርጋ አልባ መኪና የሚነዱት "አምጥቶ ነው" እየተባሉ በጀብድ ተነገረላቸው። እርጉዝ ሳይቀር ለዘረፋ መጥታ አማራ ወልዳ ተይዛለች። ወጣቱ "እኔም ይህን አምጥቻለሁ" እያለ በጀግንነት እንዲያወራ ተደረገ። ከጦርነቱ በኋላ ግን ዘረፋውን ትግራይ ውስጥ ቀጠሉት። አማራ ላይ ጀግና የተባሉበት ነዋ! የቀራቸው ነገር የለም። ፍርድ ቤት ስላልቻለ እንደ ድሮው በአደባባይ በዚህ መልክ መቅጣት ጀምረዋል።

ታዲያ ወደ ራያ የላኩት ይህን ዘራፊ ኃይል ነው። አዲስ ልብስና ጫማ ሳይቀር እያስወለቀ ሲወስድ የሚታወቅ ዘራፊ ራያን እያራቆተ ነው። በወረራው ወቅት ሲዘርፍ ጀግና ያሉትና ከወረራ በኋላ ትግራይን ያስመረረውን ነው ወደ ራያ የላኩት። ወደ ጠለምትና ወልቃይትም ለማስገባት የወሰኑት ይህ ሰው በላ የሆነን ኃይል ነው።
13.4K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-27 17:40:00
15.2K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-27 17:39:51 አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም! ማፈናቀል ነው! እየተተገበረ ያለው የጓዳ ውል እንጅ የሰላም ስምምነት አይደለም!

ተፈናቃይ በመመለስ ሰበብ ከ50 ሺህ በላይ ንፁሃን አፈናቅለዋል። ድሮም ይህ ነው የሚባል ተፈናቃይ አልነበረው። ወደራያ አካባቢዎች የገባው የትህነግ ገዳይና ዘራፊ ታጣቂ፣ ትግራይ ውስጥ በወንጀል ያስቸገራቸው ዘርፎ እንዲሄድ የተደረገ ኃይልና የትህነግ መዋቅር ነው። ሁሉም ከመግደል፣ ከመዝረፍና ከማፈናቀል ውጭ መጀመሪያ የተባለውን ተፈናቃይ መመለስ ሲናገሩ አይሰሙም! አላማቸውም በቀል፣ ዝርፊያና ርስት መቀማት እንጅ ተፈናቃይ መመለስ አይደለም።

እንደ አንድ ጠላት ብለው እንደፈረጁት አካባቢ መግደል፣ መዝረፍና ማሳደድ ነው የተያያዙት። የያዙት አካባቢ ሀብትና ንብረት ወደ ትግራይ እየተጫነ፣ መጫን ያልቻሉትን እያወደሙ ነው። አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። ማፈናቀል ነው። ትህነግ በቀሉን ይወጣል። አብይ ለምዕራባውያኑ "የአማራን ግዛት ሰጥቻቸዋለሁ" ብሎ እርዳታ ይለምናል።

አላማው የጓዳው ውል ማስፈፀም እንጅ በአደባባይ በመግለጫ የሚነግሩን ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። አብይ በአማካሪዎቹ በኩል በአንድ ስልክ ትዕዛዝ ፀጥ ረጭ የሚያደርገው ብአዴን ደግሞ ይህ ሁሉ እየተፈፀመ እንዳላየ ዝም ብሏል። አንድ ቀን የሰጣት መግለጫ እንኳን ቁጣ አስተናግዳበት ከዛ በኋላ ይህ ሁሉ ህዝብ ሲፈናቀል ትንፍሽ አላለም።
15.1K views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ