Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.49K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-02-26 07:09:14 ሚስጥሩ ከተደራዳሪው አንደበት

"በመሃላችን ችግር ነበር"


ምዕራባውያን ዝምታን የመረጡበት ምክንያት



27.0K views04:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-25 16:13:34 ሰበር ዜና!


ተደራዳሪዎቹ ዝምታቸውን ሰበሩ

ስለወልቃይትና ራያ  የተወሰነው  ይፋ ሆነ

"ህወሓት ወልቃይትና ራያን  አልጠየቀም"



15.8K viewsedited  13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-24 13:14:14 የበረከት ስምኦን ራዲዮ ባትሪ እንደሞላህለት ነው። የጎረቤት ጠብ ኖሮህ፣ "ሰው ምን ይለኛል? እኔ ከዚህ ጋር አልሰዳደብም። ለእሱ እኩያውን አላጣለትም" ካልክ ይህ ራዲዮ አለልህ። ባትሪውን ትሞላለህ። መክፈት ነው ከዛ እስከመጨረሻው። ጎረቤትህ ደህና ባትሪ ከሞላለት ደግሞ ተመልሶ አንተው ላይ ይጮሃል!
16.6K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-23 20:23:53

17.5K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-23 15:25:17 በኤርሚያስ በኩል የሚስተጋባው የግድያና የወ*ረ*ራ ዝግጅት!

ደብረፅዮን የሰላም ስምምነቱን ህወሓት አያውቀውም ብሏል። ደብረፅዮን ይህን መግለጫ የሰጠው ከብልፅግና ጋር ያደረጉት የድብቅ ስምምነት ባሰቡት መልኩ ስላልሄደላቸው ነው። ስለሆነም ራያ ላይ ተደጋጋሚ ትንኮሳ አድርገዋል። በወልቃይት ወ*ረ*ራ ለመፈፀም ዝግጅት ማድረጋቸውን የራሳቸው አክቲቪስቶች ጭምር እየፃፉት ነው። ለዚህ ሲባል ቀድሞ ፕሮፖጋንዳ መስራት አስፈልጓደዋል። አንደኛው አማራውን መነጣጠል ነው።

ትህነግ/ህወሓት በራያ ትንኮሳ ከመፈፀሙ በፊት የፀጥታና ሌሎች አመራሮችን ገድሏል። በአካባቢው ሰው በሀሰት ስማቸው እንዲነሳ በማድረግ ጭምር ከአምስት በላይ አመራሮች ተገድለዋል። በቀጣይ ወልቃይት ከዛም አልፎ ጎንደር ላይ አስበዋል። ለዚህም በእነ ኤርሚያስ በኩል በሀሰት ስም ማጥፋት ፕሮፖጋንዳ ቀጥለውበታል።

በሁለት አመቱ ጦርነት ወቅት ትህነግ/ህወሓት በእነ ኤርሚያስ በኩል "ስኳድ" የሚል ሰነድ ሰርተው በትነው ነበር። ወቅቱ የትህነግ/ህወሓት ጎንደርን እይዛለሁ ብሎ የሚለፋቨየሚለፋበት ወቅት ነበር። በጦርነቱም በፕሮፖጋንዳውም አልተሳካላቸውም።

ትህነግ/ህወሓት ከ60 ቀን ግምገማው በኋላ ለኤርሚያስ ትዕዛዝ ሰጥቶ በየሚዲያው አንዳንዴ በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ ሳይቀር ራሱ የሰራውን ሰነድ ህዝብን ለመከፋፈያነት ሲጠቀምበት ይውላል። ዋናው ትህነግ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት አንዳንድ ግለሰቦችን ለማስገደል፣ ወረራም ለመፈፀም የሚያደርገው ቅድመ ዝግጅት ሲሆን ኤርሚያስ TMH፣ ማሪያማዊት የምትባል የህወሓት አባልና ሌሎች ሚዲያዎች ላይ እየተመላለሰ እየሰራበት ነው። የዚህ ነውረኛ ውሸታው የግድያና ጦርነት ቅስቀሳ በህግ ጭምር የሚያዝ ስለሆነ ወደፊት እመለስበታለሁ።

ለማነፃፀሪያ እንዲሆን ግን አብይን እየተከላከለ፣ በረከትን እየተከላከለ፣ በይፋ በፓርቲ የመጣውን ኩሽኩን እየተከላከለ፣ የጎንደር ህዝብ እያለ የሚነዛውን ጥላቻ ተመልከቱት! ኤርሚያስ የሀሰት ሰነዱን ለማስረፅ ሶስት አመት ሙሉ ሰርቶበታል። ምክንያቱ ደግም ትህነግ/ህወሓት አማራን ነጣጥሎ፣ መጀመሪያ ጎንደርን መትቸ ወደሌላው አቀናለሁ የሚለውን የወ*ረ*ራ አላማ ለማስፈፀም ነው።

"ህወሓት ሲባል የትግራይን ህዝብ ማለታቸው ነው" እያለ የሚያስተባብለው ኤርሚያስ፣ "ኦህዴድ ሲሉ ኦሮሞን ነው" የሚለው የበረከት ስምኦን ልጅ፣ ጎንደር እያለ ግን አደረጃጀት ብቻ ሳይሆን ህዝብን እንደ ህዝብ እየዘመተበት ያለው በትህነግ ቀጣይ የወ*ረ*ራ እቅድ መሰረት ነው።

(በዚሁ አጋጣሚ መሰል የሀሰትና ጥላቻ ቅስቀሳ ቪዲዮዎች ያሏችሁ ወገኖች ከስር እንድታያይዙ ትጠየቃላችሁ)
18.7K viewsedited  12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-22 21:45:17
20.7K views18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-22 21:45:08 ሲ ፒ ጄ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ዘርፉ አስቸኳይ ህክምና እንዲያገኙ ጠይቋል። ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ዘርፉ የታሰሩበት አዋሽ እስር ቤት በንፋስና ጎርፍ በደረሰበት ጉዳት ለአደጋ መጋለጣቸውን ገልፆ በአስቸኳይ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ጠይቋል።

እነ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸው ተደርገው "የኢትዮጵያው ጓንታናሞ" እየተባለ በሚጠራው ክፉ እስር ቤት ከታጎሩ ወራት አልፈዋል። ከጋዜጠኞቹ በተጨማሪ ፖለቲከኞችና ሌሎች ንፁሃን በአማራነታቸው በዚህ የግፍ እስር ቤት እየተሰቃዩ ነው።
21.1K views18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-19 11:00:00 "ፋኖ ጦርነቱን ያቁምልን" መከላከያ፣

የኤርትራው ደህንነት ስለኢትዮ ፎረም፣


"አማራ አስቸገረን" ሬድዋን


የወልቃይት ጉዳይ



31.4K viewsedited  08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-18 11:02:56
29.0K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-18 11:02:47 አንድ ዜና! በርካታ አጀንዳዎች!

አጀንዳ 1፦

የትግራይ ርሃብን ጉዳይ ለማጣጣል ብልፅግና ከፍ አድርጌ ሰቀልኩት ያለው አጀንዳ ነው። "እርዳታ እየላክን ነው። ከእርዳታ አልፎ የልማት ስራ ላይ ተሰማርተናል። እንደ ሌሎች ክልሎች ትግራይ የገበታ ለሀገር ..ተጠቃሚ ሆናለች" እያሏቸው ነው።

አጀንዳ 2፦

ጌታቸው ረዳ ሲያጣጥለው የነበረውን "ገበታ ለሀገር" ወዘተ ደስ ብሎት ሊያስተዋውቅ አይችልም። ጉብኝት ብለው የተገኙት መከላከያ ሚኒስትሩና ደህንነት ሚኒስትሩ ናቸው። ሬድዋን የደቡብ አፍሪካው ስምምነት ለትህነግ/ህወሓት በሚጠቅም መልኩ እንዲተገበር ሲሰራ የቆየ ሰው ነው። ጌታቸው ረዳ ደግሞ ከስምምነቱ ውጭ ራያና ወልቃይትን እንሰጣችኋለን ተብሎ የተገባለት ቃል ስለዘገየ በትግራይ ፖለቲካ እየተንገበገበ ነው። ጌታቸው ረዳን "ሎጅ እንጎብኝ ብለን እናውራ" ብለውታል። በየቦታው የሚከተለው ደብረፅዮን ሳይሰማ ያደረጉት ነው። ጌታቸው ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በቀጥታ ከአዲስ አበባ የተደረገ ጉዞ ነው። የደህንነት ሚኒስትሩ፣ መከላከያ ሚኒስትሩ ሎጅ ሲጎበኙ የሎጅ ዜና ብቻ እንዲመስል ፈልገው ነው። ጌታቸው ረዳ ለእነ ደብረፅዮን "ራያና ወልቃይትን አሳልፈው ሊሰጡን ነው" ብሎ ሪፖርት ያደርጋል። ደብረፅዮን በእሱ ላይም እንደሚያወሩ ቢገባውም ለጌታቸው ሰበቡ በቂ ነው።

አጀንዳ 3፦

በሎጅ ስም ስለራያና ወልቃይት ብቻ አይወራም። የትህነግ/ህወሓት የውስጥ ጉዳይም አለበት። ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ የተገኘው ደብረፅዮን ቀርቶ ጌታቸው ረዳና አብርሃም በላይ ከፊት የሆኑበት መቀሌ ላይ ሲታኘክ እንደሚውል ግልፅ ነው።

አጀንዳ 4፦

በርሃብ ሰው ሞተብኝ፣ እርዳታ የለም እያለ መግለጫ ሲሰጥ የከረመው ጌታቸው ረዳ ነው። የሎጅ ስራንም ተራ ማጭበርበሪያ ሲል ከርሟል። ስብሃት ነጋ "የሲ አይ ኤ ወኪል ነው" እያለ የወረፈው ጌታቸው ረዳ "አሜሪካ" የሚል ቲሸርት ለብሶ የአብይን ፕሮጀክት በማስተዋወቁ ቤተ መንግስት አካባቢ "ከፊት አድርገን የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አስተዋዋቂ አደረግነው" ሲባል ይውላል። ወደ ትግራይ ይህን አጀንዳ ይዞ መሄድ የሚችለው ጌታቸው ረዳ ነው።

አጀንዳ 5፦

የአገራትና የተቋማት መሪዎች "የሰላም ስምምነቱ እየተተገበረ አይደለም። ወደ ግጭት ልትገቡ ነው" እያሉ ስጋት እየገለፁ ነው። ሰሞነኛ መግለጫዎች በአሜሪካና ሌሎች ዘንድ "ስጋት" ተብሎ ይገለፃል። ወደ መቀሌ ሲመላለሱ የከረሙት ዲፕሎማቶች በሙሉ ስጋት ይገልፃሉ። እነ አብይ ደግሞ "እጅና ጓንት ሆነን ልማት እየሰራን" ይሏቸዋል።

አጀንዳ 6፦

ትህነግ/ህወሓት ትግራይ በጦርነት ወደመች የሚለው ብልፅግና እኔ ተጠያቂ አይደለሁም ባይ ነው። ትግራይን የማውደም አላማ ቢኖረኝ ጦርነት እንደቆመ ሎጅ አልሰራልህም ነበር ይለዋል። በጦርነቱ ተፈፀመ ስለሚባለው ምርመራ እንዲደረግ ቢባልም አብይና ህወሓት በስምምነት አስቁመውታል። ይች ደግሞ መቀሌን እንደ በሻሻ አድርገናታል ለሚለው ማርከሻ ሆና በየጊዜው ዜና ትሆናለች።

አጀንዳ 7፦

ሀይማኖታዊ አጀንዳ አለው። እነ አብይ ለኦርቶዶክስ ሰራን ስለሚሉት ወይንስ ከእነ አብይ ጀርባ ያለው ወደ ትግራይ መግቢያ ጥሩ ፕሮጀክት ነው ስለማለታቸው ልፃፍ? ሰፊ ነው። ሌላ ቀን እመለስበታለሁ።

የደህንነት መስሪያ ቤቱ ኃላፊ፣ የመከላከያ ኃላፊ እንደ ቱሪዝም መስሪያ ቤት ኃላፊ "ሎጅ ጎበኙ" ተብሎ የተሰራው አንድ ዜና ቢሆንም በርካታ አጀንዳ ያለው ነው። ቁማሩ ብዙ ነው።
28.1K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ