እርስ በራስ የተገዳደሉት አባትና ልጅ ….
በደቡብ ኦሞ ዞን ጂንካ ከተማ አርክሻ ቀበሌ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰአት የ27 አመቱ ወጣት ማንነቱ ባልታወቀ ሰዉ ሁለት ቦታዉ በስለት ተወግቶ እራሱን ስቶ መንገድ ላይ ወድቆ ይገኛል።
መረጃ የደረሰዉ የጂንካ ከተማ ፖሊስ የተጎጂዉን ህይወት ለማትረፍ ወደ ሆስፒታል ቢያደርስም ሊተርፍ አልቻለም፡፡
ፖሊስ መረጃ አሰባስቦ የሟቹ ወላጆች ቤት ሲገባ የወጣቱ ወላጅ አባትም በተመሳሳይ ሁለት ቦታ ላይ በስለት ተወግቶ ህይወቱ አልፎ ነበር የተገኘዉ።
የአባትና ልጅን የአሟሟት ሚስጥር ለማወቅ ፖሊስ ባደረገዉ ማጣራት ልጅ አባቱን ከዚህ በፊትም በጦር ወግቶት ታክሞ መዳኑን አረጋግጧል።
በዕለቱ ሊያግባባቸዉ ያልቻለ ግጭት በመሀከላቸዉ በመፈጠሩ አባት ከዚህ በፊት ልጁ በስለት ወግቶ ጉዳት አድርሶበታልና ሳይቀድመኝ ልቅደመዉ በሚል እሳቤ አባት ጨክኖ ልጁን ሁለት ጊዜ በጦር ወግቶት ጦሩን ሳይነቅልለት ዘወር ይላል።
ከዚያም አባት የልጁን መሞትና በህይወት መኖር ሊያረጋግጥ ወደ ተጎጂዉ ጠጋ ሲል ልጅ ከወደቀበት ብድግ ይልና የተሰካበትን ጦር ነቅሎ ወላጅ አባቱን ሁለት ቦታዉ ይወጋዉና መዉደቁን ሲያረጋግጥ ከቤት ወጥቶ በመሮጥ ላይ ሳለ መንገድ ላይ እራሱን ስቶ ወድቆ መገኘቱ ነዉ ፖሊስ የገለፀዉ።
መረጃው የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ነው
16.9K views10:26