በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች ገዳይ ዘላቂነት ባለው መልክ እልባት ለመስጠት የሁለቱን ክልሎች የበላይ አመራር ተወካዮችን ያሳተፈው ብሔራዊ ኮሚቴ ተሰብስቦ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ከ8 ወራት በፊት ተቀምጦ የነበረው አቅጣጫ የተስተጓጎለበት ምክንያት ገምግሞ ተገቢ ግልፅነት ከተፈጠረ በኋላ አጠር ባለ ጊዜ የሚፈፀምበትን መርሃ ግብር አዘጋጅቶ ለመተግበር በመስማማት ሁለቱም ክልሎች ከመከላከያ ከተመደቡ አመራሮች ጋር ሆኖ የሚያስተገብር የኦፕሬሽናል ቡድን አባላትን እንዲወክሉ መግባባት ላይ ደርሷል።የእስካሁን አፈፃፀሞችን በመገምገም የወደፊት አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል። 36.4K views13:24