Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 174.61K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 399

2022-05-13 21:56:09
የኢትዮጲያ አየር መንገድ በ አውሮፕላን አብራሪነት ሞያ ዘርፍ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ማስታወቅያ አውጥቷል

ከ 12 ኛ ክፍል መመዝገብ ይቻላል ? የመመዝጋቢያ መስፈርቶች ; የትምህርት ደረጃ እና ሌሎችን ዝርዝር መረጃዎችን ከስር ባለው ቪዲዮ ይመልከቱ

https://corporate.ethiopianairlines.com/eaa/announcement/application-announcement
20.3K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:51:40
ቱርክ ፤ የፊንላንድ እና ስውዲን NATOን መቀላቀል እንደማትደግፍ አስታወቀች።

የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፤ ሀገራቸው ስዊድን እና ፊንላንድን NATOን በአባልነት የመቀላቀል እቅድ እንደማትደግፍ ገልፀዋል።

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በግልፅ ባያብራሩም የኖርዲክ ሀገራት የብዙ አሸባሪ ድርጅቶች መገኛ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ዛሬ አንካራ ውስጥ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ኤርዶጋን ፥ " ስዊድን እና ፊንላንድን በሚመለከት ያለውን ሂደት እየተከታተልን ነው ፤ ነገር ግን በጉዳዩ ላይ አዎንታዊ አመለካከት የለንም " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም NATO ግሪክን በአባልነት መቀበሉ ስህተት ነበር ሲሉም ተደምጠዋል። " እንደ ቱርክ ተመሳሳይ ስህተቶችን መድገም አንፈልግም " ሲሉ አክለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በዝርዝር ባያብራሩም " የስካንዲኔቪያ አገሮች የአሸባሪ ድርጅቶች ማረፊያ ናቸው " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን ፤ " እንደውም በአንዳንድ ሀገራት የፓርላማ አባላት ናቸው ፤ እኛ ደጋፊ መሆን አንችልም (NATOን የመቀላቀል ጉዳይ) " ብለዋል።

ቱርክ ስውዲንን እና ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራትን አሸባሪ ስትል የፈረጀቻቸውን እንደ ኩርዲሽ ሚሊሻ ቡድን PKK እና YPG ፤ እንዲሁም በአሜሪካ መቀመጫቸውን ያደረጉትን የፈቱላህ ጉለንን ተከታዮች ይደግፋሉ/ያስተናግዳሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ይደመጣል።

አንካራ ጉሌኒስቶች እ.ኤ.አ. በ2016 መፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገዋል ስትል የምትከስ ሲሆን ጉለን እና ደጋፊዎቹ ክሱን አይቀበሉትም።
19.3K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:47:16 መድፍ ተኩሶ ወደኃላ መሮጥ
18.5K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:58:04 ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ እና ጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ይሁን - የአማራ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት

ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንዲሆን የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንዲሆን የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ሰጥቷል።

የምክር ቤቱ መግለጫ ቀጥሎ ቀርቧል:-

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታው ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በዝርዝር ገምግሟል፡፡ የወያኔ ወራሪ ቡድን በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት እያነሳሳ በአማራ ክልል ላይ ዳግም ጦርነት አውጇል፡፡ ይህን አደገኛ ቅዠቱን ለመመከትና ለመቀልበስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የክልሉ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት በአንክሮ ተወያይቶበታል፡፡ የጸጥታ ምክር ቤቱ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በሌላ በኩል በየደረጃው በተደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች ላይ ጎልተው ከወጡ ወሳኝ ጉዳዮች መካከል አንዱ የሕግ ማስከበር ሥራ መላላት ተጠቃሽ መሆኑን የጸጥታ ምክር ቤቱ በጥልቀት አንስቷል፡፡

በቅርብ ጊዜ ደግሞ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የአማራን የውስጥ አንድነት ለማዳከም፣ ሕዝብ ከሕዝብ በማጋጨትና በማጋደል ላይ ተሰማርተው ለጠላት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየሠሩ ያሉ የተደራጁና ያልተደራጁ ኃይሎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ተጨባጭ የፀጥታ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን በዝርዝር ተወያይቶበታል፡፡

እነዚህ ኃይሎች በእምነት፣ በፖለቲካ፣ በብሔር ሕዝባችን እየከፋፈሉ የአማራን የውስጥ አንድነት በማዳከም ለጥቃት ተጋላጭ እንዲሆን የሚያደርጉት ሙከራ በአጭር ካልተቀጨ በሕዝባችንና በክልላችን ሰላምና ደኅንነት ላይ ዘላቂ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡

የሕገ-ወጥ ንግድን በማስፋፋት ካለው ሀገራዊ የምርት እጥረት በተጨማሪ ሰው ሠራሽ የምርት እጥረት በመፍጠር የኑሮ ውድነት የሚያባብሱ፣ ምርትን ለጠላት በኮንትሮባንድ አሳልፈው የሚልኩ፣ የሕዝብን ሃብት የሚዘርፉ፣ የዜጎችን ነጻ እንቅስቃሴ የሚገድቡ ድርጊቶች በየአካባቢው እያቆጠቆጡ መጥተው ለክልሉ የፀጥታ ስጋት መሆናቸውን ጸጥታ ምክርቤቱ ለይቷል፡፡ ከዚህም በላይ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር የክልሉን ሰላምና ደኅንነት ስጋት ውስጥ እየጣለ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም መሳሪያን ለመሞከር በሚል በሐዘንና በደስታ ላይ በግዴለሽነት በሚተኮስ ጥይት የንጹሐንን ህይወት እየቀጨ እና የሕዝባችን የፀጥታ ስጋትና የሐዘን ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ጸጥታ ምክር ቤቱ በአንክሮ ተመልክቷል፡፡

ሕገ-ወጥነትና ሥርዓት አልበኝነት ሥር እየሰደደ በመምጣቱ ሕገ-ወጥ ታጣቂዎች በሚያደርጉት ያልተገባ እንቅስቃሴ የክልሉን ልማቶች እያዳከመ፤ የዜጎችን ነጻ እንቅስቃሴ እየገደበ ፤ የኢንቨስትመንት እድሎችን እየዘጋ፣ የተፈጠረውን የሥራ ዕድል እያጠፋ፣ ለቀጣይ ልማትም እንቅፋት በመሆንና በአጠቃላይ የአማራን ክልል ልማት በአደገኛ ሁኔታ እየተፈታተነ እንደሚገኝ አጽንኦት ሰጥቶ ተመልክቷል፡፡

እነዚህ ሕገ-ወጥ ተግባራት በከተማም ሆነ በገጠር በአጭር ጊዜ ማረም ካልተቻለ የአማራ ክልል ልማት የሚያስቀጥል ሳይሆን የነበረውንም የሚያመክን የሕገ-ወጥነትና የሥርዓት አልበኝነት መናኸሪያ የሚያደርግ መሆኑን በመረዳት ለሕዝብ ሰላምና ደኅንነት ሲባል መልክ መያዝ እንዳለባቸው ታምኖበታል፡፡ በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖቻችንም በአግባቡ ምግብ እንዲያገኙ አድርጎ ወደ ቀያቸው ጊዜ መመለስ ካልተቻለ የፀጥታና ሰብዓዊ ቀውስ እንደሚያስከትል ፀጥታ ምክር ቤቱ ተወያይቶበታል፡፡

ከዚህ አንጻር መንግሥት በየደረጃው ሕግ የማስከበር ሥራውን በጥብቅ በመፈጸም የሕዝቡን ሰላምና ደኅንነት ማስከበር አለበት በማለት ሕዝቡ በተለያዩ መድረኮች ያነሳቸውን ጥያቄዎች መርምሮ ትክክለኛ ጥያቄ መሆኑን አስምሮበታል፡፡

ስለሆነም የክልሉ ጸጥታ ምክር ቤት የአማራ ክልል ያለበትን የፀጥታ ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም የወያኔን ዳግም ወረራ ለመቀልበስና ለመከላከል የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ሰላምና ደኅንነትን መጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብሎ ያምናል። ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ፣ ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በመሆኑም በአንድ በኩል ከፌደራል የጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት ከወያኔ የሚሰነዘርብንን ጥቃት ለመከላከል በተጠንቀቅና በዝግጁነት መቆም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በውስጣችን ለወያኔ ሴራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩትን ሕገ-ወጦችንና ሥርዓት አልበኞችን በመቆጣጠር የክልላችን ሰላምና ደኅንነት ማስጠበቅ ግንባር ቀደም የትኩረት አቅጣጫ እንዲሆኑ ወስኗል፡፡

ስለሆነም የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በየደረጃው የጸጥታ ግብረ ኃይል አቋቁሞ ሕገወጥነትን ለመቆጣጠርና ሕግን ለማስከበር ተገቢ ነው ያላቸውን ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በመሆኑም የክልላችን ሕዝብ፣ ወጣቶች፣ የገጠርና የከተማ ነዋሪዎች ሰላምና ደኅንነታችን ለመጠበቅ እና የውስጥ አንድነታችን ለማጠናከር የፀጥታ መዋቅሩ በሚወስደው እርምጃ ሁሉ ተባባሪ እንድትሆኑ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት

ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓ.ም

ባሕር ዳር
8.7K views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:48:43
#AddisAbaba

የፓርኪንግ ብቃት ማረጋገጫ በወሰዱ ከ200 በላይ የህንፃ ስር ፓርኪን አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ፍተሻ ተካሄደ።

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ የህንፃ ስር ተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ስፍራውን ለታለመለት አላማ ማዋለቸውን ለመለየት በ214 ህንጻዎች ላይ ፍተሻ አድርጓል።

በተካሄደው ፍተሻ ከ214 ህንፃዎች ውስጥ ፦

86 (40.2%) የህንፃ ስር ፓርኪንግ አገልግሎት ስፍራውን ለታለመለት አላማ ማዋላቸው ተረጋግጧል።

74 (34.6) ህንፃዎች ከታለመለት ዓለማ ውጭ በከፊል ለሌሎች አገልግሎቶች ማዋላቸው ተረጋግጧል።

54ቱ (25.2%) ህንፃዎች ለምን አላማ እንዳዋሉ ማወቅ አልተቻለም ተብሏል።

የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታውን በከፊል ለሌላ አገልግሎት የቀየሩት ፦

ለውኃ ታንከርና ጀነሬተር ማስቀመጫ፣
ለእቃ ማከማቻ፣
ለቢሮ አገልግሎት፣
ለንግድ ስራ፣
ለቆሻሻ ማጠራቀሚያ እና ተረፈ ምርት ማከማቻ እና ለሌሎች ያልታወቁ አገልግሎት የዋሉ መሆናቸው ተረጋግጧል።

በ11ዱም ክ/ ከተማዎች የህንፃ ስር ፓርኪንግ ብቃት ማረጋገጫ ተሰጥቷቸው ለሌላ አገልግሎት ያዋሉ ተቋማት ላ እርምጃ ለመውሰድ ኤጀንሲው እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
10.1K views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:20:29

12.5K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 18:34:33 ግንቦት 05/2014 ዓ/ም

ከወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
***
ወራሪዉ የትግራይ አሸባሪ መንጋ ኃይል ወልቃይት ጠገዴንና አከባቢውን ከ16 ዓመት ታዳጊ ጀምሮ እስከ 70 ዓመት አዛውንት የሆነ ማንኛውንም ትግራዋይ፤ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብን እንዲወር የክተት አዋጅ አውጇል።

ማንነታችን እንደ ወንጀል ተቆጥሮ የአማራ ተወላጅ የሆነ ሁሉ በየሄደበት እንደ ዶሮ አፍኖ በመሰወር፣ በመግደል፣ አካልን በማጉደል፣ ከሰማይ በታች ከመሬት በላይ አለ የሚባል ግፍ ሁሉ ተፈፅሞብናል። በሺዎች የሚቆጠሩ ታሪክ አዋቂዎች፣ ስለ ህዝብ መብት ተከራካሪ የሆኑትን የሀይማኖት አባቶችን የት እንደደረሱ ሳይታወቅ ደብዛቸው ጠፍቷል።

ስለሆነም በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፣ በአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እንዲሁም ሚሊሻና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጥምር ተጋድሎ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማህበረሰብ ነፃ ወጥቷል። ይህ የትናንት አኩሪ ገድላችን ነው።

መላው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ ሆይ!!

ወራሪውና ተስፋፊው የትግራይ ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ህልውናህን ሊያጠፋ ቆርጦ ተነስቷል። በመሆኑም በጠላት ዝግጅት መጠን ልክ በተጠንቀቅ እንድትቆም የወቅቱ አስገዳጅ ሁኔታ ሆኗል።

የተከበርከው የአማራ ህዝብ ሆይ!!

በህብረት፣ በአንድነት፣ በፅናት ስለታገልክ የስርዐት ለውጥ አምጥተኃል። ነፃነትም አግኝተኃል። ይሁን እንጂ ድጋሚ ህልውናህን ሊያጠፋ ከመላ ትግራይ የከተተ ወራሪ ኃይል በይፋ ጦርነት አውጆብኃል።

የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!!
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የትግራይ ተስፋፊ ኃይል ባወጀው ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብቷል። ከአሁን በፊት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ስቃዩ ስቃዬ፣ በደሉ በደሌ ነው ብለህ ከፍተኛ ዋጋ ከፍለኃል። ይህን የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ያደንቃል እውቅናም ይሰጣል። ኃብት ማፍራት ይሁን በህይወት መኖር መኖርም አገር ሲኖር ነውና፤ ይህንን አገር አጥፊ ወራሪ ቡድን ለመመከት በምናደርገው ተጋድሎ ከጎናችን እንድትቆም ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

ይህንን የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ጥሪ ተቀብያለሁ የሚል ሁሉ የአንድ ወር ስንቅ በማዘጋጀት በየቤቱና በየቀበሌው ሆኖ ለምናቀርበው የፈጥነህ ድረስ ጥሪ ዝግጁ ሆኖ እንዲጠብቅ ሲል ኮሚቴው መልዕክቱን ያስተላልፋል።

''ከአማራነታችን ዝቅ የሚያደርገን ምድራዊ ኃይል የለም!!''

የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ አየለ
17.9K views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 16:41:53
ትግስት ተስማ የተባች ልጃችን ትምህርትቤት እንደወጣች አልተመስችም
እባካችሁ ያያችሁት በሉዕል እግዚአብሔር ስም በዚህ ስልክ አሳውቁን ወረታውን እንከፍላለን ቤተሰቦቻ
0910988234
0911865666
0911699034
ቄራ አካባቢ ቀን 03/9/14
3.4K views13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 15:57:26
አንድ የውጪ ሃገር ዜግነት ባለው ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላር እና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በብርበራው ከ71 ሺህ ብር በላይ የኢትዮጵያ ብር መያዙንም ነው ያስታወቀው።
ግለሰቡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንዶሚኒየም ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለ 3 ወለል ፎቅ ተከራይቶ የሚኖር መሆኑን ገልጿል።
 
ተጠርጣሪው ግለሰብ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ አገር ዜጎችን እየተቀበለ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራትን ሲፈጽም እንደነበር ከህብረተሰቡ ጥቆማ ማግኘቱንም ነው የገለጸው።
ጥቆማውን መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ተቀናጅተው ባደረጉት ክትትል ግንቦት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በግለሰቡ መኖሪያ ቤት በተደረገ ፍተሻ በመኝታ ክፍል ውስጥ የተገኘ 5 ሺህ 335 የአሜሪካ ዶላር፣ 380 ዩሮ፣ 1 ሺህ 435 የቻይና የን እና ሌሎች የተለያዩ ሃገራት ገንዘቦችን ጨምሮ 71 ሺህ 635 የኢትዮጵያ ብር መያዙን ከአዲስ አበባ ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
10.9K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 15:40:59
በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ ስርቆት በፈፀሙና ጉዳት ባደረሱ ግለሰቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ ስርቆት በፈፀሙና ጉዳት ባደረሱ 20 ግለሰቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ በአገልግሎቱ የሕግ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ ተስፋ÷ 20 ተከሳሾች ጥፋተኝነታቸው ተረጋግጦ ከ6 ወር እስከ 12 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑንና ቀሪዎቹ ክሶች በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የቅጣት ውሳኔ…

https://www.fanabc.com/በኤሌክትሪክ-መሠረተ-ልማት-ላይ-ስርቆት-በ/
12.4K views12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ