Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_moe — Ministry of Education Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81.50K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-12-16 08:16:14
የትምህርት ሚኒስትሩ አዲስ ከተሾሙት የኒካራጓ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
....................................................
ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ከአዲሱ የኒካራጓ አምባሳደር ማውሪሲዮ ላውታሮ ሳንዲኖ ሞንቴስ ጋር ተወያዩ።

በቆይታቸውም በትምህርት ዘርፍ በሁለቱ አገሮች መካከል በሚኖሩ የትብብር ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የትምህርት ትብብር ለማሳደግ ሁለቱም ወገኖች የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው አረጋግጠዋል።

Nicaragua’s Ambassador to Ethiopia paid a courtesy visit to H.E Berhanu Nega (Prof), Minister of the FDRE Ministry of Education
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
H.E Mauricio Lautaro Sandino Montes, Nicaragua Ambassador to Ethiopia, paid a courtesy visit to H.E Berhanu Nega (Prof), Minister of the FDRE Ministry of Education.

During the courtesy visit, they discussed about the south-south cooperation in the field of education between the two countries.

They also conferred mutual interest in further promotion of cooperation in Education.
14.1K views05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-14 13:04:17
የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) እና ’HUWAWEI’ ለትምህርት ሚኒስቴር የ ICT መሳሪያዎች ድጋፍ አደረጉ
----------------------------//-------------------------
ታህሳስ 4/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) ዩኔስኮ-ሁዋዌ ቴክኖሎጂ ለአይሲቲ መሠረተ ልማት ማጎልበቻ የሚሆን ከ16 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ለትምህርት ሚኒስቴር አስረክቧል፡፡

በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የአይሲቲ መሳሪያ ልገሳው ተማሪዎች ለትምህርታቸው ግብዓት ለማግኘት፣ እውቀታቸውን ከመማሪያ መጽሀፍት በላይ ለማስፋት እና ሰፊ ከሆነው አለም አቀፍ የመረጃ እና የመማር ልምድ ጋር እንዲገናኙ ያስችላቸዋል ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም ተማሪዎች መሳሪያዎቹን በሃላፊነት በመጠቀም በቴክኖሎጂ ታግዘው ችግር ፈቺዎች እና የነገ መሪዎች እንዲሆኑ የሚያስችላቸው ትምህርት ላይ ማተኮር እንደሚገባቸውም ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዋ እንደ ሀገር ካለው የተማሪ ቁጥርና የትምህርት ቤቶች ብዛት አንጻር ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0278e5bCHaBR87kqfBmpvRtmX6ekBXyPBD94XHepZMmS2mPzU3SbkjdUwWTub8mvByl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
18.1K views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-12 09:16:03
የኢፊዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከጣሊያን አቻው ጋር የትብብር መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ታህሳስ 2/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና የጣሊያን የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርትና ስልጠና መስክ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የትብብር መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡

በሁለቱ ወገኖች የተፈረመው የትብብር ስምምነት ሰነድ በሀገራቱ መካከል የሚደረገውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ስምምነቱን የኢፌዲሪ ትምህርት ሚንስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የጣሊያኑ አቻቸው ክቡር ጉሴፔ ቫልዳይታራ የፈረሙ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት መካከል ስትራቴጂክ የሆነ የትምህርትና ሥልጠና ትብብር እንዲኖር ያስችላል ተብሏል፡፡

የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በፊርማ ስነ ስረዓቱ ላይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን ያብራሩ ሲሆን በተለይም ለሁሉም ዜጋ ያለምንም የኢኮኖሚ ደረጃ ልዩነት ፍትሃዊና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማቅረብ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አብራርተዋል፡፡

የጣሊያኑ የትምህርት ሚኒስትር ክቡር ጉሴፔ ቫልዳይታራ በበኩላቸው ሀገራቸው በቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና፣በቋንቋና ባህል እንዲሁም በተማሪዎችና መምህራን ልውውጥ ላይ ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ገልፀገልፀል።


ሙሉ ዜናው ttps://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02ShLCdD4eRN8pEP3zqh8ryQ5bSJpHzWE3q3uv5Mk4tGtysWn3gCJfDKmSoewf3GCal&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
17.5K views06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-09 17:16:44
"በትብብርና አለም አቀፍ ተሳትፎ የሀገራችንን የአካዳሚክ ጉዳዮች ማስተዋወቅ ይገባል" ዶ/ር ሀብታሙ አበበ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት
.............................................

ህዳር 28/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የከፍተኛ ትምህርት የኮሙዩኒኬሽንና አለም አቀፍ ግንኙነት አመራሮች በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮሙኒኬተሮች ፎረም እያካሄዱ ነው።

በፎረሙ ላይ የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ ይህ መድረክ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ልምድ ለመለዋወጥ ያግዛል ብለዋል።

በተለይም በአለም አቀፍ የአካዳሚክ ምህዳር ላይ የትብብር ድልድይ ለመገንባት የህዝብ ግንኙነትና አለም አቀፍ ክፍሎች ሚና የጎላ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ሀገራችንን በአካዳሚክ ጉዳዮች በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ የተጠናከረ ህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።

በተጨማሪም ይህ መድረክ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ተሞክሮና አዳዲስ ስልቶች ላይ እርስ በርስ ልምድ ለመለዋወጥ እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴርን የሪፎርም አጀንዳዎች በሚገባ በመረዳት ለማህበረሰቡ የምናስተዋውቅበትን እድል ይፈጥራልም ብለዋል።

ሙሉ ዜናው

።https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0gQpNhitnjifce9LQgK76YR4wocLdrzV5XQTAguMzUG7WCCZeJs9RrJ3QwDFHLVZKl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
16.9K views14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-08 03:46:21
ማስታወቂያ

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማራቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ (Letter of proficiency) እንዲጻፍላቸው ለሚፈልጉ ተገልጋዮች ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ሲመጡ ማሟላት የሚጠበቅባቸው መሥፈርቶች: -
1. አሥራ ሁለተኛ ክፍል ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ ኦሪጅናል ሰርተፊኬትና የማይመለስ አንድ ኮፒ፣
2. በቀድሞው የትምህርት ፖሊሲ 10ኛ ክፍል አጠናቀው የመሰናዶ ትምህርት (ፕሪፓራቶሪ) ያላጠናቀቁ ከሆነ 10ኛ ክፍል ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ ኦሪጅናል ሰርተፊኬትና የማይመለስ አንድ ኮፒ፣
3. አመልካቾች ማንነታቸውን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ ከማይመለስ አንድ ኮፒ ጋር ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን አገልግሎቱ የሚሰጥባቸው ቀናት ሰኞ እና ሐሙስ በሥራ ሰዓት መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር
18.0K views00:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-06 19:14:11
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ
……………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………….

ህዳር 26/2016 ዓ/ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ።

በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበዓሉ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን የኢትዮጵያዊነት ሚዛንን በጠበቀና የአንድነታችንን ገመድ ባጠናከረ ሁኔታ ሊከበር ይገባል ብለዋል።

የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች መብትና እኩልነታቸው ህገ መንግስታዊ እውቅና እና ጥበቃ ያገኘበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን ጠቅሰው ራስን ማስተዳደር መብትን ጨምሮ ባህልና ቋንቋቸው በማሳደግ ሰፊ ርቀት መጓዝ መቻላቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

“ብዝሀነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት “ በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ሰይድ በህገ መንግስትና በህብረብሄራዊ ፌዴራሊዝም ላይ ያተኮረ የመወያያ ሰነድ አቅርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
19.5K views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-28 14:16:45
17.5K views11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-28 13:53:27
በእውቀት የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ብዙ መሥራት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስገነዘቡ
..................................................................................

ህዳር 18/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) 32ኛው አገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዕውቀት የሚጎለብተው በከፍተኛ ትብብርና መደጋገፍ ነው።

በመሆኑም ዕውቀት የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንደአገር ገና ብዙ መሥራት እንደሚገባ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስገንዝበዋል።

አሁን ባለው ሁኔታ መቀጠል እንደማይቻል የጠቆሙት ሚኒስትሩ ለሚቀጥለው ትውልድ የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስችል ዕውቀት መስጠት ይገባል ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም የትምህርት ጉባዔው የተዘጋጀው ለሥራ ፣ለዕውቀት ፣ አብሮ ለመኖርና ለመሣሰሉት ያለንን አመለካከት ለመቀየር መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።
ሙሉ ዜናውን

https://www.facebook.com/100064682287722/posts/pfbid02smZknTxfdvCUr1ZQPHAvU9YtRJhmG98W6VLK8CGg6FxYi41XN2d4a8B6m6hTCQZMl/?mibextid=9R9pXO

የትምህርት ሚኒስቴር ዜናዎችን

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
18.0K views10:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-27 15:09:01
የስራና ተግባር ትምህርት በቀጣይ ዓመት ወደ ትግበራ ለመግባት ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑ ተገለፀ።
.............................................
ህዳር 17/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒሰቴር ) 32ኛው የትምህርት ጠቅላላ ጉባኤ አካል የሆነው የዘርፎች ትይዩ ጉባኤ በሶማሌ ብሄራዊ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የጉባኤው ዋና አላማ በእቅድ ትግበራ ወቅት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና ባጋጠሙ ችግሮች ላይ የመፍትሄ አማራጮችን ለመቀየስ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ወደ ሙሉ ትግበራ የተገባ መሆኑ እና የስራና ተግባር ትምህርት በቀጣይ ዓመት ወደ ትግበራ ለመግባት ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል፡፡

የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመቅረፍ የተለያዩ የለውጥ መርሃ-ግብሮች ተቀይሰው ወደ ተግባር መግባታቸውንም ጠቁመዋል።

የበጀት እጥረት፣ የስምሪትና መልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ያለመሆን፣የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ መሆኑ እና የመሳሰሉት ችግሮች የትምህርት ስርዓቱ የወቅቱ ፈተናዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

በመድረኩ የሶማሌ ብሄራዊ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱላሂ አብዲ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid08Ni8hmbg2MDHq2WXLz93LB4d4FuYSJzG2yFdruADXku2jMPAEeTgsCEAy2GowF7Gl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
19.6K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-27 14:27:09
በቀጣይ ሁለት ዓመታት በተልዕኮና ትኩረት መስካቸው የተለዩ 9 ዩኒቨርስቲዎችን ወደ ራስ ገዝ ደረጃ ለማሻገር እየተሰራ ነው:- ትምህርት ሚኒስቴር
...............................................................................
ህዳር 17/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ
እንደገለጹት በቀጣይ ሁለት ዓመታት 9 ዩኒቨርስቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

በ32ኛው የትምህርት ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ትይዩ መድረክ መክፈቻ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ቴክኖሎጁ የሚጠቀም ፣ የሚመራመርና በሥነምግባር የታነጸ ዜጋ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።

የጉባዔው ዓላማ በከፍተኛ ትምህርቱ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት በቀጣይ ስለሚወሰዱ የእርምትና የለውጥ እርምጃዎች ላይ የጋራ ግንዛቤና አቋም ለመያዝ መሆኑን ጠቁመዋል።

የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በአፕላይድ ዩነቨርስቲ የተልዕኮና ትኩረት መስክ ለይቶ በተፈጥሮ ሀብት እርብቶአደርና እንስሳት ልማት እንዲሁም በምግብ ዋስትና ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ መስክ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02S887Ytq9QQBn55bzT54gyCDpavzUk6oBsQKyC5N9AwS293A1Wm6HGZU7cVGqsCjzl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
18.7K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ