የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
81.50K
የሰርጥ መግለጫ
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
3
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4
2024-02-03 12:26:07
የትምህርት ዘርፉን ሪፎርሞች ለማሳካት የትምህርት ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ
-------------------------//-----------------
ጥር 25/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃጸምን አስመልክቶ ምክክር ከክልልና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮዎች ጋር አካሂዷል ::
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ፤ የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመቅረፍና የትምህርት ተደራሽነትን፣ ተሳትፎንና ፍትሃዊነትን ለማሳደግ የተለያዩ የለውጥ መርሃ- ግብሮች ተቀይሰው ወደ ትግበራ መገባቱን ገልጸዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ እንደገለጹት የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመማሪያ መጻህፍት ህትመትና ስርጭት እንዲሁም የመምህራንና ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ ችግሮቹን ለመቅረፍ እየተሰራ ሲሆን ቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል::
ክብርት ወ/ሮ አየለች አክለውም የጀመርናቸውን የለውጥ መርሃ-ግብሮች ውጤታማ ማድረግ የሚቻለው ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲያደርጉና የድርሻቸውን እንዲወጡ ማስተባበር ስንችል ነው ብለዋል::
ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0iqwx3jhxUoV4DFe5ksu1siwUtSTpNA6Hk24Bgr55e5cKFU1GbkA3Njyksu3danHEl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
19.0K views09:26
2024-02-02 10:40:58
ማስታወቂያ
ረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጋበዝ
የትምህርት ሚኒስቴር: -
1. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣
2. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣
3. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ ምምህራን ምልመላና መረጣ የአፈጻጸም መመሪያ፣ የሚሉ 3 መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።
መመሪያዎቹ በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አስተያየት ሰጥተውባቸው የዳበሩ ሲሆን የፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ክፍል 2 ንዑስ ክፍል 2 አንቀጽ 10 መሰረት የሚዘጋጁ መመሪያዎች ከመጽደቃቸው በፊት ማንኛውም ሰው የሚሳተፍበት የውይይት መድረክ ማዘጋጀትና ግብዓት መሰብሰብ እንዳለበት ስለሚደነግግ ሚኒስቴሩ የውይይት መድረከ አዘጋጀቷል።
በዚህም መሰረት ጥር 30/2016 ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ለባለድርሻ አካላት የገለጻና የውይይት መድረክ ስለተዘጋጀ በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ በመገኘት አስተያየት እንድትሰጡ ተጋብዛችኋል።
16.9K views07:40
2024-01-24 12:51:49
#ማ ስ ታ ወ ቂ ያ
የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ 20/2016ዓ.ም መራዘሙን ስለማሳወቅ
በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመፈተን የምዝገባ ጊዜው ጥር 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 15/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ መጠቀሱ የሚታወሰ ነው።
ይሁን እንጂ በተፈታኞች ጥያቄ መሰረት የምዝገባ ጊዜው እስከ ጥር 20/2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ሌሎች ሁኔታዎች ግን ቀደም ሲል በተገለጸው አግባብ የሚከናወኑ መሆኑን እናሳውቃለን።
======================
የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለምትፈተኑ አመልካቾች በሙሉ
ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ሙሉ ማስታወቂያው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02fonYtnk7WiKJxmE5jhrbK6D4Hwx6rkrQTTR62bUdWGMebLHHc369kutmGZkENvPyl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
21.5K views09:51
2024-01-23 16:05:36
የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ለመገንባት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
======================
ጥር 14/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ መምህራን እና የትምህርት ቤት የአመራሮችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግን ኢላማ አድርገው በዓለም ባንክ እገዛ የተገዙ 3,790 ታብሌቶች ርክክብ ተደረጓል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመምህራንና ትምህርት አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተሰራጩት ታብሌቶች የትምህርት ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በኩል ትልቅ እገዛ እንዳላቸው ገለጸዋል።
ዶ/ር ሙሉቀን አክለዉም ታብሌቶቹ በተመረጡ ጉድኝት ማእከላት ትምህርት ቤቶች በኩል 18,000 የሚሆኑ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ተደራሽ እንደሚያደርጉ ጠቅሰው ለታለመለት ዓላማና ተግባር ብቻ እንዲውሉ አሳስበዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመምህራንና ትምህርት አመራር ዴስክ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ አሰግድ መሬሳ በበኩላቸው የታብሌቶቹ ስጦታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማሻሻል መምህራን የመማር ማስተማር ተግባርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አስደግፈው አንዲሰጡ ለማስቻል፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮች አጫጭር የስራ ላይ አቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማገዝና አጠቃላይ የመምህራን ስልጠና ስርዓትን ዲጅታላይዝ ለመድረግ ያለመ ነው ብለዋል።
በርክክቡ ወቅትም ስራው ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑንና በ2015 ዓ.ም 47 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን ማእከል ያደረገ 1000 ታብሌቶች ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተሰራጩ መሆኑ ተገልጿል፡፡
13.5K views13:05
2024-01-19 21:20:40
13.2K views18:20
2024-01-11 11:21:49
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከኮሪያ ጋር በትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብር ላይ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ ፡፡
..................................... // ...............................
ጥር 2/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከኮሪያ ጊዮንግሳንግቡክ-ዶ (Geongsangbuk-do) ትምህርት ቢሮ ጋር በትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የትብብር መግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የትብብር ስምምነቱ በሁለቱ ሃገራት መካከል ከ20016-2017 ዓ.ም የሚደረገውን የትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብርን የተመለከተ ነው።
ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን የወዳጅነትና ድጋፍ ከማጠናከሩ ባሻገር በዲጂታል የትምህርት ስትራቴጂና የማስፈጸሚያ ዕቅድ አተገባበር እንዲዳብር ለማበረታታት ያስችላል ተብሏል፡፡
በትብብር ስምምነት ሰነዱ ላይ የአይሲቲ መሳሪያዎችን ማቅረብና ለተመረጡ መምህራን ከትምህርታዊ መረጃ አሰጣጥ ጋር የተያያዘ ስልጠና መስጠት የኮሪያ መንግስትን የሚመለከቱ መሆኑና የስልጠና ተሳታፊዎችን መምረጥን በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴርን የሚመለከቱ መሆናቸውን ተካተውበታል፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ እና የጊዮንግሳንግቡክ-ዶ ቢሮ የትምህርት ዘርፍ አስተዳዳሪ ሊም ጆንግ-ሲክ በእለቱ ተገኝተው ስምምነቱን ፈርመዋል፡፡
14.6K views08:21
2024-01-09 17:16:28
17.6K views14:16
2024-01-06 16:52:32
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና የትምህርቱ ማህበረሰብ እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆን እንመኛለን።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ሚኒስትር
25.6K views13:52
2024-01-03 11:03:23
15.0K views08:03